• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዓለም ባንክ የ400 ሚሊዮን ዶላር የፋይናንስ ድጋፍ ለኢትዮጵያ ሰጠ

July 27, 2023 10:06 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያ ከዓለምአቀፍ ተቋማት ምንም ዓይነት ብርድም ሆን ድጋፍ እንዳታገኝ ከአገር ውስጥ የራሷ ልጆችና ከውጭ ውድቀቷን የሚመኙ አገራት የተለያየ ተጽዕኖ ሲያደርሱባት ቆይተዋል። የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ትህነግ) ኢትዮጵያን የአንድ ቤተሰብ ጥቅም ማስጠበቂያ አድርጓት በነበረበት ጊዜ ከበጀት ድጎማ ጀምሮ ማንኛውንም ዓይነት ብድር፣ ዕርዳታ፣ ድጋፍ ወዘተ ለአጋዚ ጦር ደመወዝ የሚከፍለው ጭምር ዓለምአቀፋዊ የገንዘብ ተቋማት ድጎማ ሲደርግለት መቆየቱ የሚታወስ ነው።

ትህነግ ከአራት ኪሎ ከለቀቀ ወዲህ ግን እሹሩሩ ሲሉት የነበሩት ዓለምአቀፋዊ የገንዘብ ተቋማት የተለያየ ምክንያት በመሰጠት ተገቢው ድጋፍ አቁመዋል፤ ብድር ለማግኘት እንኳን ትህነግ ሲዘርፍ የኖረውን ብድር እንደ ምክንያት በመጥቀስ ለዓቅመ ብድር አልደረሳችሁም እያሉ ኢትዮጵያን ለማዳከም ብዙ ጥረዋል። በውጪ ያሉት ኃይላትም ምንም ዓይነት እርዳታ ለኢትዮጵያ እንዳይደረግ ብዙ ሠርተዋል። ይህንን ሁሉ ከተለያየ አቅጣጫ የተሰነዘረ ጥቃት ኢትዮጵያ መክታ ለዛሬው የድጋፍ ስምምነት መድረሷ በጦር ሜዳ ከሚገኝ ድል የማይተናነስ በፋይናንሱ ዐውድ የተገኘ ታላቅ ድል ሊባል ይችላል በማለት ለገንዘብ ሚኒስቴር ቅርበት ያላቸው ከፍተኛ ሹም ለጎልጉል ተናግረዋል። ኢዜአ ያጠናቀረው የዜና ዘገባ ከዚህ በታች ይገኛል።

ኢትዮጵያና የአለም ባንክ ለሰው ሀብት ልማት አገልግሎት የሚውል የ400 ሚሊዮን ዶላር (የ21 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር) የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነት በበይነ መረብ በተካሄደ ስነ-ስርዓት ተፈራረሙ፡፡

በስምምነቱ ከተፈረመው 400 ሚሊዮን ዶላር ውስጥ 350 ሚሊዮን ዶላር የልማት ድጋፍ ሲሆን 50 ሚሊዮን ዶላር ደግሞ ብድር መሆኑ ታውቋል፡፡

የፋይናንስ ድጋፉ ለሰው ሀብት ልማት ማለትም የትምህርትን ጥራትና ውጤታማነትን ለማሻሻልና የስርዓተ ምግብን አገልግሎት ለማጎልበት የሚውል ሲሆን ከአገልግሎቱም በመላ አገሪቱ የሚገኙ ልጃገረዶችና ታዳጊ ወጣቶች ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡

የሰው ሀብት ልማት አገልግሎቱ በግጭትና በድርቅ የተጎዱ አካባቢዎችን የሚያካትት ሲሆን የማህበራዊ አገልግሎቶች አሰጣጥን ለማጠናከርና ተጠያቂነትን ለማስፈንም አስተዋጽኦ እንዳለው ታውቋል፡፡

የፋይናንስ ድጋፉ ውጤታማ የመማር ማስተማር ሂደትን ለማረጋጋጥ የሚያግዝ ከመሆኑም በላይ በተመረጡ ወረዳዎች የስርዓተ ምግብ አገልግሎትን በማጎልበት የህጻናት መቀንጨርን ለመከላከል እንደሚረዳ ታምኖበታል፡፡

የገንዘብ ድጋፉ ጥራት ያለው የማህበራዊ አገልግሎትን ለማህበረሰቡ ለማዳረስ በሚደረገው ጥረት ሂደቱን በዘርፉ ለተሰማሩ አስፈጻሚዎችና ባለሙያዎች ቴክኒካዊ የአቅም ግንባታ ድጋፍ በማድረግም ውጤታማነትን ለማረጋገጥ እንደሚሰራ ታውቋል፡፡

የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነቱን በኢትዮጵያ በኩል የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሺዴ የፈረሙ ሲሆን በዓለም ባንክ በኩል በአለም ባንክ የኢትዮጵያ፣ የኤርትራ፣ የሱዳንና የደቡብ ሱዳን ተጠሪ ኦስማን ዲዮን ፈርመዋል፡፡ (ኢዜአ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist, world bank

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule