• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ነገረ ወዲ ገብረ ትንሳኤ – ”አባዬ ምን በድለን ነው ህወሃት የምትቀጣን?”

October 28, 2022 09:26 am by Editor 1 Comment

ወደ ገደለው ስንሄድ፦ የራያው ልጅ ፃድቃን ገብረ ትንሳኤ አራት ኪሎ የባዮሎጂ ተማሪ ነበረ። ከዛም ትግል ስታይሌ ነው አለና ደደቢት በረሃ ወረደ።

[ውጊያ ተለማመደ]

ወያኔ ከደርግ ጋራ ስትዋጋ ከጦር ፊታውራሪዎች አንዱ ሆነ፤ ፃድቃን ገብረትንሳኤ። ከገቡም በኋላ ለአስር አመታት ያህል፣ በሌተና ጀነራል ማዕረግ፣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የጦር ኤታማዦር ሹም (Chief of Staff) ነበረ።

ፃድቃን ቀጥተኛ፣ ቅን እና ሆደ ቡቡ ነው ይሉታል የሚያውቁት።

[አንዴ]

የካህሳይ አብርሃን ‘የአሲምባ ፍቅር’ መፅሃፍን ካነበብክ፣ ያኔ ኢህአሠ አሲምባ እንደገባ በብሄር ፌድራሊዝም ጉዳይ ኢህአፓና ህወሃት ሲከራከሩ፣ ”የብሄር ፌዴራሊዝም የታክቲክ ጉዳይ ነው። ማታገያ ነው እንጂ End አይደለም” ብሎ የሞገተ ነው። ”የትግራይ ገባር የመሬት ላራሹ ጥያቄው ስለተመለሰለት፣ አሁን መደብ ምናምን ከምንለው ጨቋኝ የአማራ መንግስት መጣብህ፣ ነፍስህን ለማዳን ተዋጋ ብንለው ይሰማናል፣ ለዛ ነው ብሄር ፌዴራሊዝምን የምናራምደው” አላቸው። ገራገሩ ፃድቃን። (ቀጥታ አማርኛው ሳይሆን አሳቡን ነው አስታውሼ የጻፍሁልህ)

[ሌላ ጊዜ ደግሞ]

ታስታውስ ከሆነ፣ ‘የዘመናት የህዝባችን ብሶት የወለደው ጅግናው የኢህአዴግ ሠራዊት’ ሸገርን ሲቆጣጠር – ኦፕሬሽኑን ሁኔታ የመራው ፃድቃን ነው።

ፃድቃን አዲስ አበባን ሲይዝ እነ መለስ ለንደን ነበሩ። ከደርጉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ዶክተር ይግለጡ አሻግሬ ጋራ ድርድር ላይ ነበሩ።

እናም ፃድቃን በለንደኑ ጉባኤ መሃል ላይ ለመለስ ደውሎ፣ ‘አዲስ አበባን ገባን እኮ’ ይለዋል።
መለስም ‘እና ቤተመንግስት ገባችሁ ወይ?’ ይለዋል
‘አይ አልገባንም’ ይለዋል።
መለስም ለምን አልገባችሁም?’ ይላል።
ፃድቃንም፣ ‘አይ ህዝቡ ስልጣን ፈልገን የመጣን እንዳይመስለው ብዬ ነው’ ይላል።
መለስም፣ ‘እና ምን ልንሰራ አዲስ አበባ ገባን?’ ብሎት ስቆ ስልኩን ይዘጋበታል።

[እንዲህ አይነት ሰው ነው፣ ፃድቃን ገብረትንሳኤ]

[ተመልከትኝ እንግዲህ]

በሶስት የጦርነት ኩርባዎች ላይ ፊታውራሪ የነበረው ፃድቃን፣ ህወሃት ሶስቴ ክዳዋለች። አዋርዳዋለች። . . . They Failed Him Big.

(1)

ኢትዮ ኤርትራ ጦርነት።

እንደዛ ፆሮና ግንባርን አቋርጦ፣ ሰንአፈን አልፎ አስመራ ካልገባው ያለው ጄኔራል ውጊያ ላይ እያለ፣ አሜሪካኖች መለስን ‘ተመለስ፣ ካልተመለስክ ኤርትራም ብትገባ ሌላ ሱማሌ ነው የምትፈጥረው፣ የመሃል አገር ስልጣንህ አይረጋም። እኛም ማእቀብ እንጥልብሃለን’ ብለው አዘዙት። መለስም ፃድቃንን ‘ተመለስ’ ብሎ አዘዘው። ፃድቃንም አኩርፎ ተመለሰ።

ሸገር ሲመለስ ህወሃት ተጣላችው። ከስራ ተባረረ። ብርና ጥቅማ ጥቅም ተነፈገ። በደህንነቱ ክንፈ አስተባባሪነት የህወሃት ሰው በሙሉ ራቀው፣ ሸሸው። እናም ያ ጉምቱ ኢታማዦር ሹም የሚቀመስ ሁላ አጥቶ ቸሰተ።

አዲስ አድማስ ላይ በሰጠው ቃለመጠይቅ፣ ‘ያ ሁሉ አጃቢና ኮብራዎች የነበሩኝ ሰውዬ፣ ልጄን ከትምህርት ቤት ላወጣ ሴንት ጆሴፍ ትምህርት ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ በታክሲ ሄድኩ። ልጄን አወጣሁትና ታክሲ ስጠብቅ ወረፋው አደነጋገረኝ። ህፃኑ ልጄም ፀሃይ ሲመታውና ግፊያ ሲያስደነግጠው፣ ”አባዬ ምን በድለን ነው ህወሃት የምትቀጣን?” አለኝ። ይሄ አባባል ልቤን ያደማው። እስከ ዘልአለም ቅስሜን የሰበረው መጥፎ ትዝታዬ ነው’ አለ።

Yes, TPLF Betrayed Him.

(2)

ከኢታማዦር ሹምነት የተባረረው ፃድቃን፣ የUN ሰላም አስከባሪ ሃይል ደቡብ ሱዳን ላይ ሃላፊ አድርጎ ቀጠረው – በጨቅ ደሞዝ። የደቡብ ሱዳን መንግስት ሲመሠረትም የጦር አማካሪያቸው ሆኖ በዶላር ሸቀለ። ሸገር ተመለሰ። ሸገር ላይ በት በት አለ። Lion Bank እና ራያ ቢራን አቋቋመ። የአራት የመንግስት የልማት ድርጅቶች የቦርድ ሰብሳቢ ሆነ። ራያ ላይ፣ ጋምቤላ ላይ ግብርና ጀመረ። ቦሌ መድሃኒያለም ሁለት ህንፃ ገነባ።

[ከበረ። ቻፒስት ሆነ]

በመሃል መለስ ዜናዊ ሞተ። መለስ ሲሞት ህወሃት በዝርፊያና በኔትዎርክ ሽቀላ በከተች። ገለማች። አረጀች። አፈጀች። አፈላች። ከስልጣን ተባረረች። . . . መቀሌ ገባች።

ድኅረ ህወሃት ያለው አካሄድ ያስፈራው ፃድቃን፣ መቀሌና አዲስ እየተመላለሰ አብይንና ህወሃትን ለማስታረቅ ሞከረ፣ አልተሳካለትም። አብይን ‘ከኛ ጋራ ከተዋጋህ አትችለንም፣ ጥይት የጥርስ መፋቂያችን ነው፣ እረፍ’ ስለው፦ ‘በStick and Carrot የማይገዛ ሕዝብ ዓለም ላይ የለም’ አለኝ። ያኔ ተስፋ ቆረጥኩ’ አለ አንዱ ቃለ መጠይቅ ላይ። ነገር ሲከርር፣ ፃድቃን ሸገር ቁጭ ብሎ ሻእቢያ እንደማይለቀው፣ የያኔውን አስቦ እንደ ሚበቀለው ተረዳ። ልክ ሃጫሉ የሞተ እለት በሌሊት ከጀነራል አበበ ተእለሃይማኖት (ጆቤ) ጋራ በሌሊት በአፋር በኩል ሲነዱ አድረው መቀሌ ገቡ።

የቀድሞው ኢታማዦር ሹም፣ የአሁኑ ኢንቨስተር ሌፍተናንት ጄነራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ፤ በህወሃት ዝቅጠትና ቅሌት ሃብት ንብረቱን፣ የተረጋጋ ህይወቱን አጣ።

Again, TPLF Failed Him.

(3)

ሂዊ መቀሌ ከሸሸች በኋላ የትግራይ Central Military Command ተቋቋመ። ከነ ወዲ ወረደ ጋራ ወታደራዊ አመራር ሆነ። አዋጊ ፊታውራሪ ሆነ።

ከሰሜን እዝ መመታት በኋላ ሻእቢያ ከላይ፣ መከላከያ ከታች፣ ፋኖ ከጎን፣ ድሮን ከሰማይ ሲያሯሩጧቸው ተቸነፉ። ያ ሁሉ ሎጂስቲክስ ደባየ። ያ የተከማቸ ያጭርና የመካከለኛ ርቀት ሚሳኤል እንዳይሰራ ሆነ። እነ ፃድቃንም ሸሽተው ተንቤን ዋሻ ገቡ።

[ከዛ]

አለ አለና አመትም ሳይቆዩ መከላከያም ሻእቢያም ከትግራይ ለቀቁ። ህወሃት መቀሌ ተመለሰች። የነሱ ሚሊታሪ ኮማንድ ሃይሉን አሰባስቦ ከመቀሌ ወጣ። በምእራብ በወልቃይት ሞከረ፣ ተቸነፈ። በምስራቅ በሚሌ ሞከረ፣ ተቸነፈ። ቁልቁል በደቡብ በራያ መስመር ሞከረ፣ አቸነፈ።

[ነኩት ወደታች]

እስከ ደብረሲና ከቆሰቆሱት በኋላ ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አራት ኪሎን ለደመቀ መኮንን አደራ ብለው ከጦር ሜዳ ወረዱ። ይሄም ለጦሩ ከፍተኛ ሞራል ሆነው። እንደ ጀነራል አበባው ቃልም፣ መከላከያ ያሰለጠናቸው ምልምል ወታደሮችም ለአቅመ ውጊያ ደረሱ። ሪፐብሊካን ጋርድም ጦሩን በሙሉ አቅሙ ተቀላቀለ። ፋኖም፣ ‘ደጀን ተራራንና ደብረታቦርን አሲዤማ አልተኛም’ ብሎ አንገት ላንገት ተናነቀ። በላዩ ላይ የቻይናው Long Range Drone፣ በላይ ነሽ አመዴ ከቻሳ አለች።

TDFም ተመታ። ተረታ። ተንገላታ። የህወሃት ጦር – ‘ምን ይዤ ልመለስ ወደ እናቴ ቤት’ የሚለውን ዘፈን እያንጎራጎረ U Turn ሠርቶ ሸከሸከው – ወደ መቀሌ።

[ሌፍተናንት ጀነራል ፃድቃን ገብረ ትንሳኤ ተቸነፈ]

ፃድቃን ግን መሸነፉን አላመነበትም። The Elephant ሜጋዚን ላይ ‘ዓዱኒያ ብላሽ ናት። ዓለም ከዳን፤ የLip Service፣ ምፅ ምፅ ብቻ ነው ያለን። . . . ‘we got words, they got weapons’ ብሎ ኢሪሪ ብሎ ፃፈ። ኢሳያስንም የአፍሪቃ ቀንድ ሚካኤል ስሁል፣ The King Maker ብሎ ከሠሠ።

[በሌላ ቃለ መጠይቅ ደግሞ]

BBC News Hour ላይ በሰጠው ቃለ መጠይቅ ላይ ግን፦ ‘ችንፈታችን በዋናነት የጦር ሜዳ ሳይሆን የፖለቲክ እና የዲፕሎማሲ ነው። የፖለቲካው ክንፍ ነው ለዚህ ሃላፊነት ሊወስድ ሚገባው’ የሚል አነጋጋሪና ህወሃትን የከፋፈለ ቃለ መጠይቅ በትግርኛ ሠጠ። ‘ለኛ ችንፈት ተጠያቂዋ TPLF ናት’ አለ።

And again TPLF Failed Tsadkan.

[ፍረድ እንግዲህ]

የሰባ አንድ አመቱ አረጋዊ። የሁለት ማስተርስ ባለቤት። የቀድሞው ኢታማዦር ሹም – ወ – ኢንቨስተር – ወ – TDF Strategist የህይወት ዘመን ጠላት ታዲያ፣ ከቶ ማን ነውን?

ሻእቢያ?

ደርግ?

ብልፅግና?

ወይንስ ህወሃት?

(እዮብ ምህረተአብ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Opinions Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf, tplf terrorist, tsadkan gebretinsae, tsadqan

Reader Interactions

Comments

  1. Alem says

    October 29, 2022 08:45 pm at 8:45 pm

    ውድ እዮብ ምህረተአብ፣
    አፃፃፍህ እና ይዘቱን ወድጄልሃለሁ። ቶሎ ቶሎ ጻፍ። አለዚያ አለቅስብሃለሁ። አለም

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule