• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የህወሓት “መከላከያ ሰራዊት” በበቃኝ ጥያቄ ተወጥሯል፤ ጄኔራሎች አሉበት!

August 2, 2017 10:52 pm by Editor 5 Comments

ኢትዮጵያን እየገዛ ያለው ህወሓት የሚመካበትን የታጠቀ ሰራዊት የሚመሩ ከፍተኛ መኮንኖችና ጄኔራሎች በጡረታ ለመሰናበት ጥያቄ ማቅረባቸው ተሰማ። የአስቸኳይ አዋጁ ሲነሳ መልስ እንደሚያገኙ ቃል የተገባላቸው እንዳሉም ታውቋል።

የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ለደህንነት ሲባል መረጃውን ያገኘበትን ሳይገለጽ እንደጠቆመው “መከላከያ ሰራዊት” የሚባለውን የህወሓት ሥልጣን አስጠባቂ የታጠቀ ኃይል ከሚመሩት ጄኔራሎች መካከል “በቃኝ” ያሉት ጄኔራሎች ከሰባት በላይ ሲሆኑ፣ በከፍተኛ መኮንን ደረጃ ያሉት ግን ቁጥራቸው በርከት ያለ ነው።

ጄኔራሎቹ ሰራዊቱን ለመሰናበት ያቀረቡትን ዋና ምክንያት የመረጃ ሰዎቹ ቃል በቃል ይፋ ባያደርጉም፣ ከሰራዊቱ ጋር ላለመቀጠል ዕድሜ፣ ጤና፣ ጋብቻና ተያያዥነት ያላቸው ጥያቄዎችን እንደ ምክንያት አቅርበዋል። መልቀቂያ ያስገቡት ብቻ ሳይሆኑ በርካቶች ተመሳሳይ ፍላጎት እንዳላቸውም ጠቁመዋል። የዚህም ምክንያቱ ሥርዓቱ አያያዙና አሁን የደረሰበት ደረጃ ለራሳቸውና ለቤተሰቦቻቸው ሰላም አስጊ በመሆኑ ነው።

በህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ውስጥ ባለው የኃይል አሰላለፍ ስጋት ውስጥ የገቡና ችግሩ ሊወሳሰብ እንደሚችል በማሰብ አድፍጠው በመጠባበቅ ላይ ያሉ ከፍተኛ የሰራዊቱ አመራሮች ሲሰናበቱ አገር ውስጥ የመኖር ዕቅድ እንደሌላቸውና ለዚሁም አስቀድመው የጉዞ ዝግጅት ያደረጉ እንዳሉም ተጠቁሟል።

ጥያቄውን የተቀበለው ውሳኔ ሰጪ አካል ለጊዜው የሰጠው ቁርጥ ያለ መልስ የለም። በአስቸኳይ አዋጁ ምክንያት ሰራዊቱን የመልቀቅ ጥያቄ በመመሪያ በመታገዱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን መነሳት ተከትሎ ውሳኔ ሰጪዎች ምን እንደሚመለሱ ሊታወቅ እንደሚችል የመረጃው ሰዎች ለጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ነገረዋል።

በሰራዊቱ ውስጥ በሚታየው መረን የወጣ አድልዎ የተማረሩና የተሰላቹ ከፍተኛና መካከለኛ የመስመር መኮንኖችን ጨምሮ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የሰራዊቱ አባላት ስንብት እንደሚፈልጉ በመረጋገጡ በወታደራዊ ውሳኔ ሰጪዎችና ፖሊሲ አውጪዎች ዘንድ ስጋት ፈጥሯል።

በዚህም የተነሳ የአገልግሎት ጊዜያቸውን ጠቅሰው ስንብት የጠየቁ በከፍተኛ ደረጃ ክትትል እየተደረገባቸው መሆኑ ታውቋል። “አገሪቱ አሁን ባለችበት ችግር ውስጥ፣ አስቸኳይ ጊዜ ላይ እያለን እንዴት ስንብት ለመጠየቅ አሰብህ” በሚል እንደሚገመገሙም ከመረጃው ሰዎች ለመረዳት ተችሏል።

በሰራዊቱ ውስጥ ያለውን የ“በቃኝ” ህገ መንግስታዊ ጥያቄ በአስቸኳይ አዋጁ ስም አንቀው የያዙት ወሳኔ ሰጪዎች፣ ሰራዊቱን ፍልሰት እንዳያርደው ፍርሃቻ ስለገባቸው ከወዲሁ የአዳዲስ ሃይል ምልመላ ሲያካሂዱ እንደነበር ለመረዳት ተችሏል። ከዚህም በላይ በየክልሉ ያለውን የልዩ ሃይል ከአስችኳይ ጊዜ መነሳት በኋላም በአንድ ዕዝ ውስጥ የማስገባት ስራ እንደሚሰራ ታውቋል።

እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የሰራዊቱ አባላት የመሰናበት ፍላጎታቸውን አፍኖ መዝለቅ ስለማይቻል “ከጥልቅ ተሃድሶ በኋላ” በየክልሉ አዳዲስ ታጣቂ የማስፈለፈሉ ስራ እየተሰራ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል። አሁን ባለው አሰራር ከመከላከያ መሰናበት የሚችለው በጋብቻ ወደ ውጪ አገር የሚሄድ ወይም ቀደም ሲል በማመልከት የትምህርት ዕድል ያገኘ ብቻ እንደሆነና ይህ መመሪያ መቼ እንደሚነሳ በግልጽ የተቀመጠ ነገር እንደሌለ የመረጃው ምንጮች ተናገረዋል።

የኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያምን አገዛዝ ወደ ፍጻሜው ለማምጣት እንዲረዳ “በመፈንቅለ መንግሥት” ሙከራ ሳቢያ በርካታ ጄኔራሎች ከሠራዊቱ ተወግደው ነበር። ይህ የተቀነባበረ ድርጊት ለህወሓት ወደ አዲስ አበባ መግባት ዕንቅፋት ይሆናሉ ተብለው የታሰቡን በቀላሉ “ከመንገድ የጠረገ” እንደነበር የሚታወስ ነው። አገር ውስጥ ባሉ የውስጥ አርበኞችና በውጭ አገራት የለውጥ ፈላጊ ሆነው በቀረቡ “ከሃዲዎች” ቅንብር ሳይካሄድ የከሸፈው መፈንቅለ መንግሥት የሚጠርገውን ጠራርጎ ካለፈ በኋላ ኮ/ሎ መንግሥቱ ከሥልጣን የመወገዳቸው ጉዳይ “የቀናት” ብቻ እንደሆነ “ያበሰረ” እንደነበር ብዙዎች የሚያስታውሱት ነው።

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ሰበብ አድርጎ የታፈነው የህወሓት ጄኔራሎች “የበቃኝ” ጥያቄ አስቀድሞ ከሥልጣናቸው የተለዩትን፣ በተለያዩ የሃብት መሰብሰብ ተግባራት የተሰማሩትንና ወደፊታቸውን የሰበሰቡትን ሃብት እየበሉ ለመኖር ባሰቡት ዘንድ እንዲሁም በሥልጣን ለመቆየት በሚያስቡት ጭምር የተደበላለቀ ስሜትን ፈጥሯል። ሆኖም የጄኔራሎቹ “የበቃኝ” ጥያቄ መነሻ ምክንያት ከላይ የተጠቀሱት ብቻ ይሁኑ ወይም ሌሎች ያልተጠቀሱ መነሾዎች ይኑራቸው ለጊዜው የታወቀ ነገር የለም። (ፎቶው “የበቃኝ” ጥያቄ ካቀረቡት ጋር ግንኙንት የለውም)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Ras Dejen says

    August 23, 2017 11:28 am at 11:28 am

    TPLF is a bunch of Ethiopian wrong births appointed by aliens to destroy their own heritage and identity. Fighting TPLF is beyond a local/African war/dispute:
    https://www.youtube.com/watch?v=pvP7vVQ8NGU

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    August 28, 2017 08:54 pm at 8:54 pm

    Golgul!!!! you are distributing phony news just as fake money. Please, have a commonsense

    Reply
    • Editor says

      August 28, 2017 09:37 pm at 9:37 pm

      Mulugeta Andargie – you never quit spitting your venom. Don’t you think “phony news” is much better than a “Box Jellyfish” venom of yours? Don’t worry – keep spitting and we will publish it for the record so that you will be hold accountable when the time comes.

      Editor.

      Reply
  3. Mulugeta Andargie says

    September 10, 2017 11:06 pm at 11:06 pm

    አይ ያገሬ ሰው! ያሞኙ ተላላ!
    የደገፈህ ቀርቶ እንኩሮህ ተብላላ!

    ድሮም ይታወቃል! ሰው ነው ካንደበቱ
    አንተ ግን ቀባጠርክ አንደበተ ብርቱ

    ግብሬን ካላየሀው ካልጣመህ ጭራሹን
    ባፍማ መደለል እየኝ አመሻሹን!
    ስድብ ያደልባል ያወፍራል ቢሉ
    አንተን አዘዘልኝ ያጣጥመው አሉ!!!

    Reply
  4. mamed says

    February 26, 2020 11:38 am at 11:38 am

    Ishee!! your news is rubbish. it is senseless.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
Copyright © 2026 · Goolgule