• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የህወሓት “መከላከያ ሰራዊት” በበቃኝ ጥያቄ ተወጥሯል፤ ጄኔራሎች አሉበት!

August 2, 2017 10:52 pm by Editor 5 Comments

ኢትዮጵያን እየገዛ ያለው ህወሓት የሚመካበትን የታጠቀ ሰራዊት የሚመሩ ከፍተኛ መኮንኖችና ጄኔራሎች በጡረታ ለመሰናበት ጥያቄ ማቅረባቸው ተሰማ። የአስቸኳይ አዋጁ ሲነሳ መልስ እንደሚያገኙ ቃል የተገባላቸው እንዳሉም ታውቋል።

የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ለደህንነት ሲባል መረጃውን ያገኘበትን ሳይገለጽ እንደጠቆመው “መከላከያ ሰራዊት” የሚባለውን የህወሓት ሥልጣን አስጠባቂ የታጠቀ ኃይል ከሚመሩት ጄኔራሎች መካከል “በቃኝ” ያሉት ጄኔራሎች ከሰባት በላይ ሲሆኑ፣ በከፍተኛ መኮንን ደረጃ ያሉት ግን ቁጥራቸው በርከት ያለ ነው።

ጄኔራሎቹ ሰራዊቱን ለመሰናበት ያቀረቡትን ዋና ምክንያት የመረጃ ሰዎቹ ቃል በቃል ይፋ ባያደርጉም፣ ከሰራዊቱ ጋር ላለመቀጠል ዕድሜ፣ ጤና፣ ጋብቻና ተያያዥነት ያላቸው ጥያቄዎችን እንደ ምክንያት አቅርበዋል። መልቀቂያ ያስገቡት ብቻ ሳይሆኑ በርካቶች ተመሳሳይ ፍላጎት እንዳላቸውም ጠቁመዋል። የዚህም ምክንያቱ ሥርዓቱ አያያዙና አሁን የደረሰበት ደረጃ ለራሳቸውና ለቤተሰቦቻቸው ሰላም አስጊ በመሆኑ ነው።

በህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ውስጥ ባለው የኃይል አሰላለፍ ስጋት ውስጥ የገቡና ችግሩ ሊወሳሰብ እንደሚችል በማሰብ አድፍጠው በመጠባበቅ ላይ ያሉ ከፍተኛ የሰራዊቱ አመራሮች ሲሰናበቱ አገር ውስጥ የመኖር ዕቅድ እንደሌላቸውና ለዚሁም አስቀድመው የጉዞ ዝግጅት ያደረጉ እንዳሉም ተጠቁሟል።

ጥያቄውን የተቀበለው ውሳኔ ሰጪ አካል ለጊዜው የሰጠው ቁርጥ ያለ መልስ የለም። በአስቸኳይ አዋጁ ምክንያት ሰራዊቱን የመልቀቅ ጥያቄ በመመሪያ በመታገዱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን መነሳት ተከትሎ ውሳኔ ሰጪዎች ምን እንደሚመለሱ ሊታወቅ እንደሚችል የመረጃው ሰዎች ለጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ነገረዋል።

በሰራዊቱ ውስጥ በሚታየው መረን የወጣ አድልዎ የተማረሩና የተሰላቹ ከፍተኛና መካከለኛ የመስመር መኮንኖችን ጨምሮ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የሰራዊቱ አባላት ስንብት እንደሚፈልጉ በመረጋገጡ በወታደራዊ ውሳኔ ሰጪዎችና ፖሊሲ አውጪዎች ዘንድ ስጋት ፈጥሯል።

በዚህም የተነሳ የአገልግሎት ጊዜያቸውን ጠቅሰው ስንብት የጠየቁ በከፍተኛ ደረጃ ክትትል እየተደረገባቸው መሆኑ ታውቋል። “አገሪቱ አሁን ባለችበት ችግር ውስጥ፣ አስቸኳይ ጊዜ ላይ እያለን እንዴት ስንብት ለመጠየቅ አሰብህ” በሚል እንደሚገመገሙም ከመረጃው ሰዎች ለመረዳት ተችሏል።

በሰራዊቱ ውስጥ ያለውን የ“በቃኝ” ህገ መንግስታዊ ጥያቄ በአስቸኳይ አዋጁ ስም አንቀው የያዙት ወሳኔ ሰጪዎች፣ ሰራዊቱን ፍልሰት እንዳያርደው ፍርሃቻ ስለገባቸው ከወዲሁ የአዳዲስ ሃይል ምልመላ ሲያካሂዱ እንደነበር ለመረዳት ተችሏል። ከዚህም በላይ በየክልሉ ያለውን የልዩ ሃይል ከአስችኳይ ጊዜ መነሳት በኋላም በአንድ ዕዝ ውስጥ የማስገባት ስራ እንደሚሰራ ታውቋል።

እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የሰራዊቱ አባላት የመሰናበት ፍላጎታቸውን አፍኖ መዝለቅ ስለማይቻል “ከጥልቅ ተሃድሶ በኋላ” በየክልሉ አዳዲስ ታጣቂ የማስፈለፈሉ ስራ እየተሰራ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል። አሁን ባለው አሰራር ከመከላከያ መሰናበት የሚችለው በጋብቻ ወደ ውጪ አገር የሚሄድ ወይም ቀደም ሲል በማመልከት የትምህርት ዕድል ያገኘ ብቻ እንደሆነና ይህ መመሪያ መቼ እንደሚነሳ በግልጽ የተቀመጠ ነገር እንደሌለ የመረጃው ምንጮች ተናገረዋል።

የኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያምን አገዛዝ ወደ ፍጻሜው ለማምጣት እንዲረዳ “በመፈንቅለ መንግሥት” ሙከራ ሳቢያ በርካታ ጄኔራሎች ከሠራዊቱ ተወግደው ነበር። ይህ የተቀነባበረ ድርጊት ለህወሓት ወደ አዲስ አበባ መግባት ዕንቅፋት ይሆናሉ ተብለው የታሰቡን በቀላሉ “ከመንገድ የጠረገ” እንደነበር የሚታወስ ነው። አገር ውስጥ ባሉ የውስጥ አርበኞችና በውጭ አገራት የለውጥ ፈላጊ ሆነው በቀረቡ “ከሃዲዎች” ቅንብር ሳይካሄድ የከሸፈው መፈንቅለ መንግሥት የሚጠርገውን ጠራርጎ ካለፈ በኋላ ኮ/ሎ መንግሥቱ ከሥልጣን የመወገዳቸው ጉዳይ “የቀናት” ብቻ እንደሆነ “ያበሰረ” እንደነበር ብዙዎች የሚያስታውሱት ነው።

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ሰበብ አድርጎ የታፈነው የህወሓት ጄኔራሎች “የበቃኝ” ጥያቄ አስቀድሞ ከሥልጣናቸው የተለዩትን፣ በተለያዩ የሃብት መሰብሰብ ተግባራት የተሰማሩትንና ወደፊታቸውን የሰበሰቡትን ሃብት እየበሉ ለመኖር ባሰቡት ዘንድ እንዲሁም በሥልጣን ለመቆየት በሚያስቡት ጭምር የተደበላለቀ ስሜትን ፈጥሯል። ሆኖም የጄኔራሎቹ “የበቃኝ” ጥያቄ መነሻ ምክንያት ከላይ የተጠቀሱት ብቻ ይሁኑ ወይም ሌሎች ያልተጠቀሱ መነሾዎች ይኑራቸው ለጊዜው የታወቀ ነገር የለም። (ፎቶው “የበቃኝ” ጥያቄ ካቀረቡት ጋር ግንኙንት የለውም)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Ras Dejen says

    August 23, 2017 11:28 am at 11:28 am

    TPLF is a bunch of Ethiopian wrong births appointed by aliens to destroy their own heritage and identity. Fighting TPLF is beyond a local/African war/dispute:
    https://www.youtube.com/watch?v=pvP7vVQ8NGU

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    August 28, 2017 08:54 pm at 8:54 pm

    Golgul!!!! you are distributing phony news just as fake money. Please, have a commonsense

    Reply
    • Editor says

      August 28, 2017 09:37 pm at 9:37 pm

      Mulugeta Andargie – you never quit spitting your venom. Don’t you think “phony news” is much better than a “Box Jellyfish” venom of yours? Don’t worry – keep spitting and we will publish it for the record so that you will be hold accountable when the time comes.

      Editor.

      Reply
  3. Mulugeta Andargie says

    September 10, 2017 11:06 pm at 11:06 pm

    አይ ያገሬ ሰው! ያሞኙ ተላላ!
    የደገፈህ ቀርቶ እንኩሮህ ተብላላ!

    ድሮም ይታወቃል! ሰው ነው ካንደበቱ
    አንተ ግን ቀባጠርክ አንደበተ ብርቱ

    ግብሬን ካላየሀው ካልጣመህ ጭራሹን
    ባፍማ መደለል እየኝ አመሻሹን!
    ስድብ ያደልባል ያወፍራል ቢሉ
    አንተን አዘዘልኝ ያጣጥመው አሉ!!!

    Reply
  4. mamed says

    February 26, 2020 11:38 am at 11:38 am

    Ishee!! your news is rubbish. it is senseless.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule