• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

❝አላህ ይፍረደኝ የልጆቼን አባት አንገላተው ገደሉት፤ ጅብ አስበሉት ብጥስጣሽ ልብሱ ውርማ ተገኘ❞ ወ/ሮ ጦይባ

September 11, 2021 10:08 pm by Editor Leave a Comment

አሸባሪው የትህነግ ቡድን መግደል ብቻ ሳይሆን የቤተሰቦቻችንን አስክሬን ጅብ አስበልቶ የግፍ ግፍ ፈጽሞብናል ሲሉ የወረባቦ ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ።

አሸባሪው የትህነግ ቡድን በወረባቦ ወረዳ ህጻናትን፣ ሴቶችን፣ አርሶአደሮችን በግፍ ገድሏል፤ ሃብትና ንብረት ዘርፏል ብሎም አውድሟል።

በወረባቦ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ካሊድ ሙሐመድ የተመራ ልዑክ አሸባሪው ትህነግ በወረዳው ጥቃት ያደረሰባቸውን፣ ንብረታቸው የተዘረፈባቸውንና የወደመባቸውን ወገኖች ተመልክቷል፡፡

በሰው ደም የሰከረው ሽብርተኛው የትህነግ ቡድን በየደረሰበት ሁሉ የጥፋት ሰይፉን እየመዘዘ ንጹሐንን ገድሏል። ለአማራ ያለውን ስር የሰደደ ጥላቻ በሚፈጽመው እኩይ ድርጊት እያሳየ ይገኛል።

በሁሉም ግንባሮች ከፍተኛ ሽንፈት ሲደርስበት ኀይሉን አሰባስቦ ደሴ፣ ሐይቅና ኮምቦልቻን መዳረሻዎቹ ሊያደርግ በደቡበ ወሎ በወረባቦ በኩል ጦርነት ከፍቶ የነበረው አሸባሪው ትህነግ የወረባቦ ወረዳን በወረረበት ወቅት ግለሰቦችን በግፍ ገድሏል፣ ንብረት ዘርፏል፤ አውድሟል።

ሽብርተኛው የትህነግ ቡድን ወረራ ከፈጸመባችው የወረባቦ ቀበሌዎች መካከል 018 ቁኖ ቀበሌ አንዱ ሲሆን ቡድኑ በዚህ ቀበሌ ንጹሐንን በአሰቃቂ ሁኔታ መግደሉን አሚኮ ከቦታው ድረስ በመሄድና የተጎጅ ቤተሰቦችን በማነጋገር አረጋግጧል።

ወይዘሮ ጦይባ ሙሐመድ የ4 ልጆች እናት ናቸው። የ30 ዓመት የትዳር አጋራቸው አሊ ዘገየ በአረም ሥራ ላይ እያሉ በግፍ ተገድለውባቸዋል። የሞቀ ጎጇቸውም አሸባሪ ቡድኑ በሐዘን አደፍርሶታል።

❝አላህ ይፍረደኝ የልጆቼን አባት አንገላተው ገደሉብኝ፤ ጌታ ይፍረደኝ በወጉ ሳልቀብር ጅብ አስበሉብኝ ብጥስጣሽ ልብሱ ውርማ ተገኘ❞ ብለዋል ሐዘን ባከሰለው ፊታቸው ላይ እንባ እየወረደ ።

ሌላኛዋ የተጎጅ ቤተሰብ ወይዘሮ አንሻ ሰይድ የ65 ዓመት እናታቸውን እንደገደሉባቸው ገልጸዋል። የእናታቸው አስክሬን በጅብ ተበልቶ ለምልክት ብቻ መገኘቱን ነው የገለጹት።

የሽብርተኛው የትህነግ ጀሌ የወገን ጦርን ብርቱ ክንድ መቋቋም ሲሳነው አፈሙዙን ወደ ንጹሐን አዙሮ እየጨፈጨፈ ከመፈርጠጡ ባሻገር የነዋሪዎችን ሀብት ዘርፏል፣ አውድሟል።

አሸባሪው ትህነግ በደቡብ ወሎ ዞን የወረባቦ ወረዳን በወረረበት ወቅት ንጹሐንን በግፍ ከመግደል ባለፈ፣ የአርሶ አደሮችን ቤትና ንብረት ዘርፏል፤ እንስሳትን ገድሏል። በማሳ ላይ የነበረ ያልደረሰ ሰብል ሳይቀር አውድሟል ነው ያሉት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ካሊድ ሙሐመድ፡፡

በሽብር ቡድኑ የንብረት ዘረፋና ውድመት የተፈጸመባችው፣ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉትና ከሞት የተረፉት ወገኖች ችግር ላይ በመሆናቸው ድጋፍን ይሻሉ ብለዋል።

ተጎጅዎችን የጎበኙት አቶ ካሊድ አሸባሪ ቡድኑ ያደረሰዉ ጥፋት እንዳሳዘናቸዉ ገልጸዋል። ሕዝቡን በማስተባበር እንዲቋቋሙ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሠራም ገልጸዋል፡፡

አሸባሪው የትህነግ ቡድን ሰው ገድሎ የማይረካና አማራን ለማጥፋት የተነሳ በመሆኑ ሁሉም በአንድነት በመቆም ሊመክትና ቡድኑን ሊያጠፋ ይገባል።(አሚኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column, Social Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule