• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

❝አላህ ይፍረደኝ የልጆቼን አባት አንገላተው ገደሉት፤ ጅብ አስበሉት ብጥስጣሽ ልብሱ ውርማ ተገኘ❞ ወ/ሮ ጦይባ

September 11, 2021 10:08 pm by Editor Leave a Comment

አሸባሪው የትህነግ ቡድን መግደል ብቻ ሳይሆን የቤተሰቦቻችንን አስክሬን ጅብ አስበልቶ የግፍ ግፍ ፈጽሞብናል ሲሉ የወረባቦ ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ።

አሸባሪው የትህነግ ቡድን በወረባቦ ወረዳ ህጻናትን፣ ሴቶችን፣ አርሶአደሮችን በግፍ ገድሏል፤ ሃብትና ንብረት ዘርፏል ብሎም አውድሟል።

በወረባቦ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ካሊድ ሙሐመድ የተመራ ልዑክ አሸባሪው ትህነግ በወረዳው ጥቃት ያደረሰባቸውን፣ ንብረታቸው የተዘረፈባቸውንና የወደመባቸውን ወገኖች ተመልክቷል፡፡

በሰው ደም የሰከረው ሽብርተኛው የትህነግ ቡድን በየደረሰበት ሁሉ የጥፋት ሰይፉን እየመዘዘ ንጹሐንን ገድሏል። ለአማራ ያለውን ስር የሰደደ ጥላቻ በሚፈጽመው እኩይ ድርጊት እያሳየ ይገኛል።

በሁሉም ግንባሮች ከፍተኛ ሽንፈት ሲደርስበት ኀይሉን አሰባስቦ ደሴ፣ ሐይቅና ኮምቦልቻን መዳረሻዎቹ ሊያደርግ በደቡበ ወሎ በወረባቦ በኩል ጦርነት ከፍቶ የነበረው አሸባሪው ትህነግ የወረባቦ ወረዳን በወረረበት ወቅት ግለሰቦችን በግፍ ገድሏል፣ ንብረት ዘርፏል፤ አውድሟል።

ሽብርተኛው የትህነግ ቡድን ወረራ ከፈጸመባችው የወረባቦ ቀበሌዎች መካከል 018 ቁኖ ቀበሌ አንዱ ሲሆን ቡድኑ በዚህ ቀበሌ ንጹሐንን በአሰቃቂ ሁኔታ መግደሉን አሚኮ ከቦታው ድረስ በመሄድና የተጎጅ ቤተሰቦችን በማነጋገር አረጋግጧል።

ወይዘሮ ጦይባ ሙሐመድ የ4 ልጆች እናት ናቸው። የ30 ዓመት የትዳር አጋራቸው አሊ ዘገየ በአረም ሥራ ላይ እያሉ በግፍ ተገድለውባቸዋል። የሞቀ ጎጇቸውም አሸባሪ ቡድኑ በሐዘን አደፍርሶታል።

❝አላህ ይፍረደኝ የልጆቼን አባት አንገላተው ገደሉብኝ፤ ጌታ ይፍረደኝ በወጉ ሳልቀብር ጅብ አስበሉብኝ ብጥስጣሽ ልብሱ ውርማ ተገኘ❞ ብለዋል ሐዘን ባከሰለው ፊታቸው ላይ እንባ እየወረደ ።

ሌላኛዋ የተጎጅ ቤተሰብ ወይዘሮ አንሻ ሰይድ የ65 ዓመት እናታቸውን እንደገደሉባቸው ገልጸዋል። የእናታቸው አስክሬን በጅብ ተበልቶ ለምልክት ብቻ መገኘቱን ነው የገለጹት።

የሽብርተኛው የትህነግ ጀሌ የወገን ጦርን ብርቱ ክንድ መቋቋም ሲሳነው አፈሙዙን ወደ ንጹሐን አዙሮ እየጨፈጨፈ ከመፈርጠጡ ባሻገር የነዋሪዎችን ሀብት ዘርፏል፣ አውድሟል።

አሸባሪው ትህነግ በደቡብ ወሎ ዞን የወረባቦ ወረዳን በወረረበት ወቅት ንጹሐንን በግፍ ከመግደል ባለፈ፣ የአርሶ አደሮችን ቤትና ንብረት ዘርፏል፤ እንስሳትን ገድሏል። በማሳ ላይ የነበረ ያልደረሰ ሰብል ሳይቀር አውድሟል ነው ያሉት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ካሊድ ሙሐመድ፡፡

በሽብር ቡድኑ የንብረት ዘረፋና ውድመት የተፈጸመባችው፣ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉትና ከሞት የተረፉት ወገኖች ችግር ላይ በመሆናቸው ድጋፍን ይሻሉ ብለዋል።

ተጎጅዎችን የጎበኙት አቶ ካሊድ አሸባሪ ቡድኑ ያደረሰዉ ጥፋት እንዳሳዘናቸዉ ገልጸዋል። ሕዝቡን በማስተባበር እንዲቋቋሙ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሠራም ገልጸዋል፡፡

አሸባሪው የትህነግ ቡድን ሰው ገድሎ የማይረካና አማራን ለማጥፋት የተነሳ በመሆኑ ሁሉም በአንድነት በመቆም ሊመክትና ቡድኑን ሊያጠፋ ይገባል።(አሚኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: News, Right Column, Social Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule