• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

❝አላህ ይፍረደኝ የልጆቼን አባት አንገላተው ገደሉት፤ ጅብ አስበሉት ብጥስጣሽ ልብሱ ውርማ ተገኘ❞ ወ/ሮ ጦይባ

September 11, 2021 10:08 pm by Editor Leave a Comment

አሸባሪው የትህነግ ቡድን መግደል ብቻ ሳይሆን የቤተሰቦቻችንን አስክሬን ጅብ አስበልቶ የግፍ ግፍ ፈጽሞብናል ሲሉ የወረባቦ ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ።

አሸባሪው የትህነግ ቡድን በወረባቦ ወረዳ ህጻናትን፣ ሴቶችን፣ አርሶአደሮችን በግፍ ገድሏል፤ ሃብትና ንብረት ዘርፏል ብሎም አውድሟል።

በወረባቦ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ካሊድ ሙሐመድ የተመራ ልዑክ አሸባሪው ትህነግ በወረዳው ጥቃት ያደረሰባቸውን፣ ንብረታቸው የተዘረፈባቸውንና የወደመባቸውን ወገኖች ተመልክቷል፡፡

በሰው ደም የሰከረው ሽብርተኛው የትህነግ ቡድን በየደረሰበት ሁሉ የጥፋት ሰይፉን እየመዘዘ ንጹሐንን ገድሏል። ለአማራ ያለውን ስር የሰደደ ጥላቻ በሚፈጽመው እኩይ ድርጊት እያሳየ ይገኛል።

በሁሉም ግንባሮች ከፍተኛ ሽንፈት ሲደርስበት ኀይሉን አሰባስቦ ደሴ፣ ሐይቅና ኮምቦልቻን መዳረሻዎቹ ሊያደርግ በደቡበ ወሎ በወረባቦ በኩል ጦርነት ከፍቶ የነበረው አሸባሪው ትህነግ የወረባቦ ወረዳን በወረረበት ወቅት ግለሰቦችን በግፍ ገድሏል፣ ንብረት ዘርፏል፤ አውድሟል።

ሽብርተኛው የትህነግ ቡድን ወረራ ከፈጸመባችው የወረባቦ ቀበሌዎች መካከል 018 ቁኖ ቀበሌ አንዱ ሲሆን ቡድኑ በዚህ ቀበሌ ንጹሐንን በአሰቃቂ ሁኔታ መግደሉን አሚኮ ከቦታው ድረስ በመሄድና የተጎጅ ቤተሰቦችን በማነጋገር አረጋግጧል።

ወይዘሮ ጦይባ ሙሐመድ የ4 ልጆች እናት ናቸው። የ30 ዓመት የትዳር አጋራቸው አሊ ዘገየ በአረም ሥራ ላይ እያሉ በግፍ ተገድለውባቸዋል። የሞቀ ጎጇቸውም አሸባሪ ቡድኑ በሐዘን አደፍርሶታል።

❝አላህ ይፍረደኝ የልጆቼን አባት አንገላተው ገደሉብኝ፤ ጌታ ይፍረደኝ በወጉ ሳልቀብር ጅብ አስበሉብኝ ብጥስጣሽ ልብሱ ውርማ ተገኘ❞ ብለዋል ሐዘን ባከሰለው ፊታቸው ላይ እንባ እየወረደ ።

ሌላኛዋ የተጎጅ ቤተሰብ ወይዘሮ አንሻ ሰይድ የ65 ዓመት እናታቸውን እንደገደሉባቸው ገልጸዋል። የእናታቸው አስክሬን በጅብ ተበልቶ ለምልክት ብቻ መገኘቱን ነው የገለጹት።

የሽብርተኛው የትህነግ ጀሌ የወገን ጦርን ብርቱ ክንድ መቋቋም ሲሳነው አፈሙዙን ወደ ንጹሐን አዙሮ እየጨፈጨፈ ከመፈርጠጡ ባሻገር የነዋሪዎችን ሀብት ዘርፏል፣ አውድሟል።

አሸባሪው ትህነግ በደቡብ ወሎ ዞን የወረባቦ ወረዳን በወረረበት ወቅት ንጹሐንን በግፍ ከመግደል ባለፈ፣ የአርሶ አደሮችን ቤትና ንብረት ዘርፏል፤ እንስሳትን ገድሏል። በማሳ ላይ የነበረ ያልደረሰ ሰብል ሳይቀር አውድሟል ነው ያሉት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ካሊድ ሙሐመድ፡፡

በሽብር ቡድኑ የንብረት ዘረፋና ውድመት የተፈጸመባችው፣ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉትና ከሞት የተረፉት ወገኖች ችግር ላይ በመሆናቸው ድጋፍን ይሻሉ ብለዋል።

ተጎጅዎችን የጎበኙት አቶ ካሊድ አሸባሪ ቡድኑ ያደረሰዉ ጥፋት እንዳሳዘናቸዉ ገልጸዋል። ሕዝቡን በማስተባበር እንዲቋቋሙ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሠራም ገልጸዋል፡፡

አሸባሪው የትህነግ ቡድን ሰው ገድሎ የማይረካና አማራን ለማጥፋት የተነሳ በመሆኑ ሁሉም በአንድነት በመቆም ሊመክትና ቡድኑን ሊያጠፋ ይገባል።(አሚኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column, Social Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule