• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ውዝግቡን በሐዋሪያት መንገድ ለመፍታት ስምምነት ላይ ተደርሷል

February 10, 2023 09:06 am by Editor 1 Comment

በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የተፈጠረውን መከፋፈልና ችግር በሐሃዋሪያት መንገድ መፍትሄ እንዲፈለግለት ወደ ስምምነት መደረሱ ተሰማ። ይህ የተሰማው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከሲኖዶስ አመራሮች ጋር መወያየት መጀመራቸውን ተከትሎ ነው።

የቤተክርስቲያኗ አባቶች ዛሬ ረፋዱ ላይ ከመንግሥት ከፍተኛ አመራሮችና ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር በቤተመንግሥት እየመከሩ ነው። ለስብሰባው ቅርብ የሆኑ ክፍሎችን ጠቅሰው ለአዲስ አበባ ተባባሪ ዘጋቢያችን ፍንጭ የሰጡ እንዳሉት፣ ችግሩን ከጣልቃ ገቦች አሳብ ነጥሎ በሐዋሪያት አግባብ ለመፍታት የመስማማት ፍንጭ አለ።

በቡራኬ የተጀመረው ውይይት ላይ ሽምግልናውን ከሚመሩት ወገኖችና ከአባቶቹ መካከል አሳብ ሲሰጡ ያለቀሱ እንዳሉና ግልጽ ውይይት እየተደረገ መሆኑን፣ ዕረፍት ላይ ከመጀመሪያው የተለየ ስሜት መታየቱንም እነዚሁ ክፍሎች አስታውቀዋል። የአገርን ሉዓላዊነት አደጋ ላይ በሚጥል የተሄደበት መንገድ እጅግ ያሳዘናቸው ወገኖች ሐቅን የተመረኮዘና ራስን ወደ መመርመር የሚመራ ግልጽ ነገር በስብሰባው ላይ ማሰማታቸው ተነግሯል።

አቡነ ማቲያስንና አስራ አምስት የሚሆኑ ሊቀነ ጳጳሳት ኢትዮጵያን በሚወዱ የተግባር ሰዎች አማካይነት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ውይይት መጀመራቸው ሲገለጽ ”ክህደት ተጀመረ” በሚል እሁድ ቤተ መንግሥትን እንዲወረርና የአፍሪካ ኀብረት ስብሰባ እንዲታወክ ያቀዱ ክፍሎች ተቃውሞ ጎን ለጎን ማሰማት ጀምረዋል።

ስብሰባ ላይ ነን በሚል ከሕዝብ ግንኙነት በተሰጠው መግለጫ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በክብር ስማቸው መጠራቱ እጅግ ያናደዳቸው ዐመጽ ናፋቂዎች ሲኖዶሱ መለሳለስ እያሳየ ነው የሚል ዘመቻ ወዲያውኑ ነው የጀመሩት።

ከስምምነቱ በኋላ በሲኖዶሱ በኩል የሚወጣው መግለጫ ጥንቃቄ የተሞላበትና ሰላም ፈላጊዎችን የሚያስደስት ብቻ ሳይሆን ጽንፈኞችና ግጭት ናፋቂዎች ጭምር ውሳኔውን እንዲቀበሉት በሚያደርግ መልኩ እንደሚዘጋጅ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ለሃይማኖታቸው ተቆርቋሪ የሆኑት በቤተክርስቲያን ላይ የደረሰው አሳዝኗቸው መልካም ምላሽ የሚፈልጉ ቢሆንም በዚህ ውዝግብ ሰበብ ከግጭት ለማትረፍና ከተቻለም የቤተመንግሥት ወረራ ለማድረግ ለተዘጋጁት ዛሬ ከሲኖዶሱ የሚሰማው ወሬ ብዙም የሚያስደስታቸው እንደማይሆን ይጠበቃል።

ክልሎች ከሰላማዊ ውይይት በስተቀር በእምነት ስም የሚደረገውን መንግሥትን የመናድ አካሄድ እንደማይቀበሉ እያስታወቁ ባለበትና ውይይት ብቻ መፍትሄ እንደሚሆን እያስታወቁ ባለበት ሰዓት የተሰማው ዜና ለተጨነቁ ዕረፍት እንደሚሆን የዜናው ሰዎች አስታውቀዋል።

በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ውስጥ የተፈጠረውን ችግር ተከትሎ በርካታ የፖለቲካ ፍላጎት ያላቸው ተጠራርተው በተጠናና ቅንጅት ባለው መልኩ ዘመቻቸውን በጥድፊያ እያካሄዱና ”ቤተ መንግሥት ውረሩ፣ ይህ አጋጣሚ ከተበላሸ ሌላ አጋጣሚ አይገኝም፣ ብረት እንደጋለ ነው መቀጥቀጥ” ሲሉ የነበሩ ውይይቱን ተከትሎ ማምሻውን እርግማን እና ሽንፈት የተሞላበት ማብራሪያና ትንተና ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። ተጨማሪ የትግል አቅጣጫ ሊቀይሱ እንደሚችሉም ይጠበቃል።

“የቅዱስ ሲኖዶስ የሰማዕትነት ጥሪ” ሲሉ የእሁዱን ሰልፍ ”የጠቅላይ ጨዋታ ነው” ያሉት ወገኖች ”መንግሥት አጀንዳ ለማስቀየር እና አማራን ለማስወረር በዋግ ኽምራ ዞን በግብጽ በኩል ወያኔን እየደገፈ ጦርነት አስጀምሯል” የሚል የጎንዮሽ ቅስቀሳም እያሰራጩ ነበር። ይህ ሁሉ ቢባልም መንግሥት ትናንት ከክልልና ከፌደራል የፓርቲው አመራሮች ጋር ከተወያየ በኋላ ክልሎች አቋማቸውን ሕገመንግሥት ጠቅሰው ማስታወቃቸው የፈጠረው ስሜት እስካሁን ብዙም አልተባለለትም።

መንግሥት ከሕገ መንግሥቱ አግባብ ውጭ ምላሽ መስጠት እንደማይችል በማሳሰብ ክልሎች መግለጫ እያወጡ ሳለ የተሰማው የስምምነት ዜና ለሕዝብ በገሃድ እንደሚገለጽ መረጃውን ያካፈሉን አስታውቀዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: abiy ahmed, Abune Mathias, Ethiopian Orthodox Church, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    February 10, 2023 09:48 am at 9:48 am

    ማለፊያ ነው ነገር በስምምነት ለመጨረስ መወሰኑ። ግን የኦሮሞ ክልላዊ መንግስት ያወጣውን መግለጫ ተመልክተዋል? ለሰላም ሳይሆን ለጦርነት የክተት ጥሪ የመሰለ ነገር ነው እየተሰራጨ ያለው። የቀድሞ ሥርዓት ናፋቂዎች፤ ትግስቴ አልቋል፤ እርምጃ እወስዳለሁ ነው የሚለው። ትግሥቱ ማለቅ የነበረበት ቤቱ በእሳት የሚጋየው፤ የሚገደለው፤ የሚፈናቀለው በዘርና በቋንቋው ተለይቶ በአደባባይ እየተዋረደ ያለው ህዝብ መሆን ሲገባው ጅራፍ ራሱ ገርፎ ይጮህ እንዲሉ ይህን ያህል ዲስኩር ከኦሮሞ ክልል ሊሰማ ባልተገባም ነበር። በወያኔ አለቅጥ መገፍተር የልብ ልብ የተሰማቸው የኦሮሞ ጠባብ ብሄርተኞችና ሃገር ገንጣይ ሃይሎች አሁንም እሳት እየለኮሱ ለሌላው እሳት ከማቀበል አላረፉም። እኔ ግን የማይገባኝ አሁን ሃገሪቱ ተንኮታኩታ ኦሮሚያ የሚባል ነገር ቢመሰረት ሰላም ይኖራል ብለው ያምናሉ? የማይሆን ነገር ለሚስትህ አትንገር እንዲሉ ብቻ ነው።
    ሰው ተደናብሷል።
    አሁን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ላይ የተጀመረው ዘመቻ የኦሮሞ ቄሶችና ዲያቆኖች የሚመሩት ብቻ ሳይሆን በበላይነት የፓለቲካ ዘርፉ የሚቆጣጠረው ነው። ችግሩም በቋንቋ የማምለክ ጥያቄ አይደለም። በቋንቋቸው እንዳያመልኩ የሚከለክል ምንም ሃይል የለምና! ግን ቄሳውስቱና ጳጳሶቹ ለፓለቲካ ክንፉ ታዛዥ ናቸው። ሳይቃጠል በቅጠል በማለት ገና ይህ ሁሉ መከራና ሰቆቃ ሳይደርስ እንደማስቆም ጠ/ሚ አንዴ የውጭ ጉብኝት አለብኝ ሌላ ጊዜ በሃይማኖት ጉዳይ መንግስት አይገባም መባሉ የፓለቲካውን የቅጥፈት አካሄድ አጉልቶ ያሳያል። የሃበሻ ፓለቲካ በሸፍ፤ በመካካድ፤ በመገዳደል የተመረዘ የጅሎች ስብስብ ነው። ሃገር ስትፈርስ፤ ሰው ሲገደልና ንብረት ሲቃጠል፤ ቆሞ እኛን አይነካንም የሚል ዘረኛ የጭንቅላት በሽታ ያለው ከሰው ስብዕና የወጣ የፓለቲካ እንስሳ ነው። ባጭሩ የገደለ፤ ያስገደለ፤ መንገድ የመራ፤ ያስመራ፤ የዘረፈ ሁሉ በጊዜው ዋጋውን ያገኛል። የሰው ደም አፍሶ በሰላም ማንቀላፋት የት አለና!
    የመቀሌዎቹ ጳጳሳትና ቀሳውስትም ራሳችን ችለን በራሳችን ነው የምናመልከው በሃሳብም በሥጋም ከጠላቶቻችን ተገንጥለናል ባሉበት አፋቸው አሁንም የሰላሙ ጉዳይ ከተፈረመ በህዋላ ለብቻ መሆናቸውን ደግመውታል። ይህ ደግሞ የወያኔ መልካም ፈቃድ የታከለበት መገንጠል እንጂ ወያኔ አይሆንም ቢል ጠመጠመ አልጠመጠመ ለወያኔ ግድ አይሰጠውም። በነገራቸው እጅ ባይኖርበት ወይ ዘብጥያ ያወርዳቸዋል ካልሆነም ወደ እማይቀሩበት አለም ይሸኛቸው ነበር። ግን ሆን ብሎ የሚሰራው ተንኮል በመሆኑ መገንጠላቸው ለወደፊት የእነርሱ የፓለቲካ ስልት መንገድ ከፋች በመሆኑ አበረታቱቷቸው ይኸው የትግራይ ቲቭ ላይ ቀርበው ለፍልፈው ወርደዋል። የሚገርመው በኦሮሚያ ክልል ስለ ተፈጠረው የኦርቶዶክስ ቤ/ክ መሳደድ ምንም አለማለታቸው ነው። እምነት ይሉሃል ይሄ ነው። ለራስ ብቻ። በአፍንጫዬ ይውጣ!
    የፓለቲካ እብደቱ በሃበሻ ብቻ ላይ አይደለም። በቅርቡ ወደ ኬኒያ ያቀኑት የኤርትራው መሪ ከስመ ጋዜጠኞች የቀረበላቸውን ጥያቄዎች ልብ ብሎ ለተመለከተ ወያኔ ጽፎ ጠይቁልኝ ብሎ የሰጣቸው ነው የሚመስለው። በእኔ እምነት ኤርትራዊው መሪ እድሜ እያበሰላቸው አሁን ላይ በቀጠናው ሰላም እንዲሆን ብዙ ነገሮችን እየሰሩ እንደሆነ ነው የምረዳው። ታዲያ በዚህ ሁኔታ ላይ የሚገኝን የሃገር መሪ የኤርትራ ወታደሮች በትግራይ፤ የስልጣን ዘመናቸውን ወዘተ እያነሱ በተደጋጋሚ ሲጠይቁ መስማት ምን ያህል የጋዜጠኛ ቅጥረኞች እንደተበራከቱ ያሳያል። ግን የዓለም ፓለቲካ ደስ የሚለው እርስ በእርሳችን ስንናከስ በዚሁ ሰበብ ተርበንና ተጠምተን ሲመጸውቱን ከጎን ቆመው ፎቶና ፊልም በመነሳት ለዓለም በጎ ሥራ ያሉትን እያሳዪ መመጻደቅ ነው። እሳቱን ከህዋላና ከፊት ሆነው የሚያነድት እነርሱ መሆናቸውን ለማያውቅ የቀን ስራው ፋታ ለማይሰጠው ህዝብ የማታ ወሬ ይሆነዋል የስንዴ ችሮታው።
    በመጨረሻም አሁን ተደረሰ የተባለው የቤ/ክ ሰላም ዘላቂ አይደለም። የኦሮሞ የክልል ፓለቲከኞች የሚደሰኩሩትንና የሚጽፉትን ስሙ። ግባቸው ገና ረጅምና ጠመዝማዛ በመርዝ የተለወሰ ነው። በትግራይ የሚደረገውም ሽር ጉድና የቤ/ክ ተገንጥላ የትግራይ ቤ/ክ ማቋቆሟ ከዚሁ ከኦሮሞው የፓለቲካ ሸር ጋር የተጣመረ ነው። ግን እስከ መቼ ነው ንጽሃን እየሞቱና እየተዘረፉ ለዚሁ ግፍና መከራ ምክንያት የሆኑት ፓለቲከኞቹ ያለምንም ተጠያቂነት ከክፋት ወደ ክፋት እየተሸጋገሩ ህዝብን እንዳሸበሩ የሚኖሩት? መልሱን ቆይተን ማየት ነው። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule