• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ

January 2, 2023 07:29 pm by Editor 1 Comment

የግሪጎርያኑን የቀን መቁጠሪያ የሚጠቀሙት የኤርትራውያን ፕሬዚዳንት በዚሁ “በነጮች አዲስ ዓመት” ተብሎ በሚጠራው ቀን ስም ”[ትህነግን] ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” ዓይነት ንግግር አሰምተዋል። ስጋት እንደሌለ ማስታወቃቸው እንደሆነ ተመልክቷል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የሚመራው ጥምር ጦር ሽሬን መቆጣጠሩን ተከትሎ ትህነግ የወሰደውና እንዲወስድ የተመከረው ምክር ከደርግ ጋር እንደሚመሳሰል ተጠቆመ።

“ቢሆንም ቅሉ፣ ይሁን እንጂ” በሚሉ መገጣጠሚያዎች አጅቦ፣ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ “ትንኮሳንና ጸብ አጫሪዎችን” ሲሉ በደፈናው አስታውቀው ሰራዊታቸው እንዳስተነፈሰ መናገራቸውን ቀድሞ የዘገበው ቢቢሲ ነው።

የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባርን (ትህነግን) በስም መጥራት ያልፈጉት ኢሳያስ ፀብ ጫሪና ተንኳሽ ኃይል መሆኑን ጠቅሰው አሁን ግን ነገሮች መቀየራቸውን አመልክተዋል። ጦራቸውን አመስግነው “አኩሪ ተግባር ፈጽሟል አስታግሶታል” ብለዋል።

“በሕዝቡ የሚሞቅ እቅፍ ውስጥ ያለው የኤርትራ መከላከያ ኃይል ወረራ ለመፈጸም ይፍጨረጨር የነበረን ኃይል በፀረ-ማጥቃት አስታግሷል። በዚህም ኩራቴ ገደብ የለሽ ነው” ሲሉ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ጦራቸውን አሞግሰዋል። የት የት ግንባር ድል እንደፈጸመ ግን አላብራሩም። ቢቢሲም አልገለጸም።

በተጠናቀቀው የነጮቹ ዓመት በአገር ውስጥም ሆነ ከአገር ውጪ ያሉ ኤርትራውያን “ንቁ ሆነው በጽኑ አቋም የሚያኮራ ትግል አድርገዋል” በሚል ለሁሉም ምስጋና ያሉት ኢሳያስ “ወረራ ለመፈጸም ሲፍጨረጨር” የነበረው ኃይል አደብ እንዲገዛ መደረጉን ገልጸዋል። ስም ባይጠሩም ትህነግን ለማለት እንደሆነ ግልጽ ነው። እርሳቸው ግን በስም መጥቀስ እንኳን ያልፈለጉበት ምክንያት አልተብራራም።

ጌታቸው ረዳ ባህር ዳር አየር ማረፊያ ላይ ሮኬት መወንጨፉን፣ ወደ ኤርትራምና ጎንደርም በተመሳሳይ መከናወኑን ሲናገሩ ኃይላቸው ጥቃቱን እንደሚቀጥል፣ የፊደራል መንግስት የጦር አውሮፕላኖች እንደሚመቱና የሮኬት ጥቃቱ እንደሚቀጥል አስታውቀው ነበር። ኤርትራም ይህን ተከትሎ “ትህነግ የደህንነቴ ስጋት ነው” በማለት በስም ባልተተቀሱ ቦታዎች ኃይሏን አሰማርታ ከኢትዮጵያ ጎን መቆሟ በተደጋጋሚ ተገልጿል። ሠራዊቱም በንብረት ማውደምና በሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ሲከሰስ ነበር።

በአሜሪካና ምዕራባዊያን ጫና የምትደቆሰው ኤርትራ በሚቀጥለው ዓመትም ተመሳሳይ ጫና ሊደርስባት እንደሚችል ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አመልክተዋል። እነዚሁ ኃይላት በተደጋጋሚ ማዕቀብና ተቃውሞ በማሰማት ኤርትራን ሲኮንኑ ነበር። አሁን ላይ የኤርትራ ሠራዊት ከትግራይ መውጣቱ በውጭ ሚዲያዎች በይፋ እየተነገረም ቢሆን እነዚሁ አገራት ጫናቸውን እንደቀጠሉ ነው። (ኢትዮ 12)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, News, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, isayas, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    January 5, 2023 12:56 pm at 12:56 pm

    የኤርትራው መሪ ፈገግታ የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው ከሚል እሳቤ እንጂ ስለ ኢትዮጵያ እንደማይገዳቸው ያለፉ ታሪኮችን ማገላበጥ በቂ መረጃ ይሰጣል። በመሰረቱ ወያኔና ሻቢያ የከተማ አለቆች ሆነው ፍቅራቸው ኮርፍዶ እንደገና በባድሜ አሳበው ከተዳቆሱ ወዲህ አስመራም ሆነ አዲስ አበባ አንድ አንድን ለመጥለፍ ያልሞከረቱ ዘዴ የለም። በተለይም ወያኔ በውጭ ሃይሎች እየተነዳና ሻቢያን እንቃወማለን የሚሉ ሃይሎችን ከአዲስ አበባ እስከ መቀሌ ድረስ በማሰማራት የኤርትራን መንግስት ከስልጣን ለማውረድና የራሱን ሰው በቦታው በሚዘውሩት እየተረዳ ለማስቀመጥ እየተንቀሳቀሰ እንደነበረ መረጃዎች ያሳያሉ። በአንጻሩ ኤርትራ በዘር ፓለቲካ ያኮረፉ በተለይም የኦነግን ሰዎች እያሰለጠነና እያስታጠቀ፤ ሌሎችም በልዪ ልዪ ስሞች ተሰልፈው ከወያኔ ጋር ስርግ ግብ እንዲገጥሙ ያመቻች እንደነበረ ግልጽ ነው።
    ጠ/ሚ አብይ ወደ ስልጣን ከመጡ በህዋላ ጫጉላ ቤት እንደገቡ ሙሽሮች መተቃቀፉና እንደ ሸማኔ መወርወሪያ አንዴ አዲስ አበባ ሌላ ጊዜ አስመራ በይፋና በስውር መመላለሱ በሁለቱ ሃገሮች መካከል የፈጠረው አንድም ለውጥ የለም። ብዙ የተባለለት የሰላምና የንግድ ልውውጥ ሁሉ ያው እንደተለመደው በሃበሻው ቢሮክራሲ ታንቆ ሁለቱ ሃገሮችን የሚያገናኘው የመንገድ ሥራም እንደቆመና በዚህም በዚያም በየምክንያቱ መቆዘምን እንሰማለን።
    ሲጀመር ወያኔና ሻቢያ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው። አሁን የተፈጠረው ጸብና ግጭት የሚያሳየው በሃበሻው ምድር የፓለቲካ ጥምረት አንድ ጀምበር የማይዘልቅ መሆኑን ነው። ሁለቱ ሃይሎች በህዝባቸው ላይ ያደረሱትንና በማድረስ ላይ የሚገኙትን ሰቆቃ የሚተምን አንድ ሃይል ቢኖር ኑሮ እንኳን በስልጣን ላይ በህይወትም መኖር የሌለባቸው እንደሆኑ ይታወቃል። ወያኔ የሰሜን ጦር ባጠቃበት ወቅት ኤርትራንና የአማራ ክልልን በሮኬት ያሽበረው በዘፈቀደ ሳይሆን በተሰላ ስልት ነው። ኤርትራና አማራ ወረሩኝ ለማለት። አሁንም ወያኔ የሚያለቅስበት በእነዚህ ሃይሎች ላይ ነው። ግን ፓለቲካ ማለት የጅሎች ስብስብ የሚጠጡት ሰንበቴ እንደ ማለት ነው። ማንህ ባለሳምንት ያስጠምድህ ባስራስምንት አይነት። እንኳን አስራ ስምንት አንድም በሬ ለሌለው የህልም ምርቃት። ያኔ ወያኔና ሻቢያ በበረሃ እያሉ እጃቸውን አንስተው ምርኮኛ ነን ያሉትን የኢትዮጵያ ወታደሮች ታንክ በላያቸው ላይ የነድ፤ በጥይት የረሸኑ፤ ገደል የከተቱ፤ የገረፉና ያሰቃዪ በባድመው ውጊያ አፍር ለብሰዋል። በዚህም በዚያም በተባራሪ ተርፈው በሃገር ቤትም ሆነ በውጭ የሚርመሰመሱት እነዚህ ደም አፍሳሾች የጣፈጠ እንቅልፍ ሳይተኙ ግማሾች የመጨረሻ እንቅልፍ ተኝተዋል፤ ቀሪዎቹ የህሊና በሽተኛና የአልጋ ቁራኛ ሆነው ይርመሰመሳሉ። ባጭሩ የሃበሻ ፓለቲካ ማለት በወረፋ መገዳደል ማለት ነው። ትላንት በደርግና በወያኔ እስር ቤቶች ሃበሳቸውን የቆጠሩ ሰዎች ዛሬ በብልጽግና (በድህነት) ፓርቲ እየታፈሱ ሲታሰሩ ማየትና መስማት የፓለቲካውን ከንቱነት አጉልቶ ያሳያል። ለዚህ ነው ኢትዮጵያ ሃገሬ ሞኝ ነሽ ተላላ የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ በማለት እንቅጩን አበው የተናገሩት። ዛሬ በወለጋ ያለውን የዘር ማጽዳት ግድያ የሚቆሰቁሱት በሃገሪቱ አንጡራ ሃብት ተምረው ዶ/ር እና ፕሮፌሰር የሚባሉት ወስላቶች ናቸው። መማር በዘር ፓለቲካ የሚያሰልፍ ከሆነ መማር ሳይሆን መደንቆር ነው። ግን አሁን ላይም ሆነ ባለፉት ዘመናት በግልጽና በስውር እየሆነ ያለው ይኸው የመጠላለፍ ፓለቲካ ነው። ችግራችን የሚመነጨው ከመሪዎቹ ሳይሆን ህዝቡ ራሱ ወስላታ ነው። አታሎ፤ ገድሎ፤ ሰውሮ፤ በዘርና በቋንቋው ተሰልፎ መኖርን ይመርጣል። ይህ ግን የሰው ባህሪ ሳይሆን የአውሬ ነው። ዛሬ በአዲስ አበባና በዙሪያዋ የሚሆነውን ልብ ብሎ ላጤነ ክፋቱ ወያኔ የሃገር መሪ እያለ ከነበረው ይከፋል። አንድን ብቻ ልጥቀስ – በጧቱ ቤታቸው በፓሊስ ይከበባል። ክፈቱ ተብሎ የቤቱ በር ይከፈታል። ከሁለት ልጆቹና ከሚስቱ ጋር ተኝቶ የነበረው የቤቱ አባወራ ምን ተገኘ ይላል መሪ ለተባለው ፓሊስ። ሚስትህን ነው የምንፈልግ ይልና ገና የሌሊት ልብሷን እንደለበሰች በካቴና እጇን ሲያስር ልጆቿ መላቀስ ይጀምራሉ። እነርሱን ዝም ለማሰኘት አባት ሲሞክር ፓሊሶች የቤት ብርበራ ይጀምራሉ። ቤቱ ፍልስልሱ ይወጣል። የሥራ ኮምፒውተር፤ የእጅ ስልኮች፤ መጽሃፍት፤ ልዪ ልዪ መዛግብት ወዘተ ይዘው ሊወጡ ሲሉ እንዴ ሚስቴን ከሆነ የምትፈልጉት የእኔ ስልክና የሥራ ኮምፒውተር ምን ያድርጋል ሲል ዝም በል አንተንም ጭምር ነው የምነዳህ ይሉትና የያዙትን ይዘው ሚስቱ ጋቢ ነገር ጣል አርጋ ይዘዋት ይፈተለካሉ። ባል ራት እና ብርድ ልብስ ሊያቀብል ሲሄድ የለችም ይባላል። እዚህ ጋ ሲሉት እዚያ ጋ እዚያ ሲጠይቅ ሌላ ስፍራ እየተባለ ሳምንት ያልፋል። ልጆች ያለቅጥ ያለቅሳሉ። በሁለት ሳምንቷ ተገኘች ይባላል። ከዚያም ዋስ ጠርታ ትውጣ ተብሎ ትለቀቃለች። ይኸው እንሆ አሁን 4ኛ ወር ነው በዋስ ከተለቀቀች። ስልኮቹ፤ የስራ ኮምፒውተሮች አልተመለሱም። ግፍ ከዚህ በላይ አለ። ፍትህ ተዛብቶ እልፎች አሁንም እንደ እንስሳ ይጎተታሉ፤ ይሰወራሉ፤ ይደበደባሉ። መደመር ይሉሃል ይህ ነው።
    ሌላው በአፋር በአማራ ክልል ወያኔ ያፍረሰው፤ ነቅሎ የወሰደው፤ ያፈናቀለው፤ የዘረፈው ባንክ፤ የህክምና ተቋም ተረስቶ አሁን አሸሸ ገዳዬው ከወያኔ ገዳይ ቡድኖች ጋር መሆኑ ምን ያህል ፓለቲካው ጠንጋራ እንደሆነ ያሳያል። የተራበው፤ የተጠማው የተፈናቀለው፤ የተዘረፈው፤ የሞተው ወዘተ የአፋርና የአማራ ህዝብ ተረስቷል። እነርሱ እየተራቡ በምድራቸው ላይ እልፍ ምግብና መድሃኒት የጫኑ ካሚዎኖች ወደ ትግራይ ማጓጓዙ የዶ/ር አብይ መንግስት ምን ያህል ከጊንጥ ጋር እንደሚጫወት ያሳያል። ወያኔ በጦርነት ተወልዶ በጦርነት የኖረ ምንም ቢደረግለት የማይሰክን ሃይል ነው። አሁን ለጊዜው ፋታ እስኪገዛ፤ መልሶ እስኪታጠቅ እንጂ ውጊያ መክፈቱ አይቀሬ ነው። ድርድር ውስጥ የገባውም የአሜሪካው ዲፕሎማት ጄፈሪ ፌልትማን እንዳሉት ወያኔ በጦርነት ስለተሸነፈ ብቻ ነው ድርድር ውስጥ የገባው። የጠ/ሚሩ ስህተት በትግራይ ጦርነት ዙሪያ ላይ እልፍ ነው። ወያኔ እቃ እየጠቀለለ ዳግመኛ ዋሻ ሊገባ ሲል ድርድር ብሎ ይኸው አሁን ትጥቅ አላወልቅም ያለ ጄኔራል አለ እያሉ ተጠባባቂ ጦራቸውን በድብቅ በማሰልጠን ላይ ይገኛሉ። ወያኔ ከጦርነት ወጥቶ በሰላም ልኑር ቢልም አይሆንለትም። የአዕላፍ ሰዎች ደም ይጮሃልና! ባጭሩ የኤርትራው መሪ ሳቅና ፈገግታ መልካምነት የሌለው ዞሮ ጥርስ ለመንከስ እንጂ ለህዝባችን አንዳች ፍሬ አያስገኝም ሊያስገኝም አይችልም። እንደ ተለመደው አንድን በአንድ አሳቦ እንደገና መላትም ሊያስከትልም ይችላል። ቆይቶ ማየት ነው። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule