• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የመቀሌ አየር ድብደባዎች ዒላማቸውን የመቱ ናቸው

October 20, 2021 11:04 am by Editor 1 Comment

የመከላከያ ሠራዊት ያካሄዳቸው የአየር ድብደባዎች ዒላማ ያደረጉት የህወሓት የጦር መሣሪያ ማምረቻ እና የጦር ትጥቅ ጥገና ጣቢያዎች ላይ ብቻ እንደሆነና ኢላማቸውን የመቱ መሆናቸው ተገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ መረጃ ማጣሪያ ገጽ ባወጣው መግለጫ፤ የመከላከያ ሠራዊት ያካሄዳቸውን የአየር ድብደባዎች በተመለከተ የተዛባ ግንዛቤ ቢኖርም፣ በተቃራኒው ጥቃቶቹ ዒላማ ያደረጉት የህወሓት የጦር መሣሪያ ማምረቻ እና የጦር ትጥቅ ጥገና ጣቢያዎችን ብቻ ነው ብሏል። 

የመከላከያ ሠራዊት የሚያከውናቸው እነዚህ ሥራዎች የሽብር ድርጅቱ ከባድ የጦር መሣሪያዎችን እና ሌሎች ሕገወጥ የጦር መሣሪያዎችን ለመሸሸግ የሚጠቀምባቸውን እና ወደ ወታደራዊ መገልገያነት የቀየራቸውን የተወሰኑ ቦታዎች ከጥቅም ውጭ ለማድረግ ያለመ ነው ሲልም አስታውቋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: endf, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, terrorism, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 22, 2021 12:00 pm at 12:00 pm

    እናንተ ይህን የድብደባ ዜና ስታናፍሱ ሌላም ድግግሞሽ ድብደባ መፈጸሙን እየሰማን ነው። የሚገርመው እብደታችን ሰማይ ጠቀስ በመሆኑ የገነባነውን መልስን የምናወድም ጅላ ጅሎች ነን። ግን ወያኔ ሃርነት ትግራይ ለትግራይ ህዝብ ነው እያለ ሰውና ሰው እንዲጫረስ ማድረጉ ምን ያህል የፓለቲካ ሰካራሞች እንደሆኑ ያረጋግጣል። ሰው በጦር መሳሪያ ሌላውን አስጎብሶ ለዘለቄታ መኖር አይችልም። ቢሞከርም ዘላቂነት የለውም። የሞከሩትም የሮም አወዳደቅን ሲወድቁ አይተናል። ለምን ይሆን ግን ከዘመን ዘመን ሰላም አጥተን ሁሌ ስንናቆር የምንኖረው? ወንድምና እህቱን ገድሎ የሚፎክር በአለም ላይ ያለ ወያኔ ሌላ ፍጥረት አይገኝም። አሁን ማን ይሙት የአማራና የአፋር ህዝብ ለትግራይ ህዝብ ጠላቱ ነው? የትግራይ ህዝብ ለእነዚህ ወገኖች ጠላት ነው? ይህ የውሸት ፓለቲካ የፈጠረው መርዝ እንጂ ሌላ አይደለም። አንድ ቤተሰብ 9 ልጆች ከወለድ በህዋላ ሳያስቡት ሌላ ተረገዘና ሰፈር ሁሉ ጉድ ሲል እናት ስም አውጭለት ትባላለች። ስሙንም በዛብኝ አለችው። እረ ይህ ስም ይቀየር ሲባል አይቻልም ከአባቱ ስም ጋር ስለሚገጣጠም ችግሬንም ሁሉንም የሚያሳይ ነው በማለት የልጅ ስም በዛብኝ በቀኑ ተባለ። አሁንም የሃበሻው ሃበሳና መከራ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ ነው። የጨነቀው እርጉዝ ያገባል አይነት። ይገርማል እንዴት ባለ ሂሳብ ነው ሌላው የለፋበትን ሃብትና ንብረት ወያኔ እያጨደና እየዘረፈ ወደ ትግራይ የሚያጓጉዘው? ይህ የታመመ ጭንቅላት አይደለም ለሚሉ ሁሉ እውነት ትመስክርላቸው።
    ወያኔ ጊንጥ ነው በአየር ይሁን በምድር ተደበደበ በህዝብ መካከል በመደበቅና ለአለም ህዝብ የውሸትና የፈጠራ ዜናን በማሰራጨት ድረሱልኝ ማለቱ እሙን ነው። ወያኔን የሚያገለግለው የአሜሪካው CNN and BBC Online እንዲሁም ሌሎች ንፋስ ዘግነው ማእበል አመንጪ የውሸት የወሬ አውታሮች በኢትዮጵያ መንግስት የአየር ድብደባ አንዲት ነፍሰ ጡር ሴት ተገደለች በማለት አናፈሱ። ይህች ያልታደለች ፍጥሩ ተጎድታ ሊሆን ይችላል። የሚገርመው ግን የኢትዮጵያ መንግስት የተከለከለ መርዝ ነክ መሳሪያ ተጠቀመ ብለውም የዘገቡም ነበሩ። ያው ወንዝ ላይ ወያኔ የጣላቸው አስከሬኖች አይነት ፓለቲካ። የሚገርመኝ ሰው ይህን ሁሉ ግፍ እያደረገ ቁጭ ብሎ እንጀራ ቆርሶ መብላቱ ነው። ከዘረኝነት የጠራ ጭንቅላት ያለው ሰው ወይ ያብዳል ወይም ይመንናል። በሰው አስከሬንና ሞት መሳለቅ የራስን አፈር መሆን መዘንጋት ነው።
    ባጭሩ የሃበሻው ፓለቲካ እንደ ደ/አፍሪቃው የነጭ የዘር ፓለቲካ አፓርታይድ ነው። በክልሉ ብቻ ተወስኖ የሚኖር ከብት ብቻ ነው። የሰው ልጅ በፈለገው ተዘዋውሮ ሰርቶ ኑሮውን ያሸንፋል። የሃበሻው የዘር ፓለቲካ ሽፍላ እንደሆነ ዋናው ማሳያው ለዘራቸውና ለቋንቋቸው የሚያቀነቅኑ ሰዎች እግሬ አውጭኝ በማለት ወይም በልዪ ልዪ ብልሃት ውጭ ሃገር ወጥተው የሚኖሩት ከዝንቅና ነጻ ከሆነ ሃገርና ህዝብ ጋር ነው። በሰውኛ መለኪያ ሰውን እንደመለካት ወንዝ በማያሻግር ቋንቋ ራስን ሽፍኖ ሰውን በዘርና በጎሳ በመለየት ማሰቃየት አውሬነት ነው። አሁን በሰሜኑ የሃገራችን ክፍሎችና በሌሎችም ክልሎች የምናየው እኛ ብቻ ለእኛ ብቻ የሚል አብሮ መኖርን የገፈተረ አፓርታይድን የሚያሰፍን ጭፍን አስተሳሰብና ድርጊት ነው። ከዘመናት በፊት ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህን እሳት ወይ አበባ በተሰኘው ግጥሙ አንድ ክፍል ውስጥ እንዲህ ይለናል።
    እኔው ከእኔው ስከራከር
    ተጨብጨ የማብላላው
    ያው መቼም እኔም እንደ ሰው
    የሃቅ ረሃብ ነፍሴን ሲያውከው
    ልቤን ልቤ ሲሞግተው
    እውነትስ ምንትስ ማን ነው?
    እያለ ነው።

    የእኔም ጥያቄ “እውነትስ ምንትስ ማን ነው”? መቼ ነው ከመገዳደልና መሰደድ፤ ተራብን ድረሱልን ከማለት ምድሪቱ የምታርፈው? ጠብቀን እንይ። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule