• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የመቀሌ አየር ድብደባዎች ዒላማቸውን የመቱ ናቸው

October 20, 2021 11:04 am by Editor 1 Comment

የመከላከያ ሠራዊት ያካሄዳቸው የአየር ድብደባዎች ዒላማ ያደረጉት የህወሓት የጦር መሣሪያ ማምረቻ እና የጦር ትጥቅ ጥገና ጣቢያዎች ላይ ብቻ እንደሆነና ኢላማቸውን የመቱ መሆናቸው ተገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ መረጃ ማጣሪያ ገጽ ባወጣው መግለጫ፤ የመከላከያ ሠራዊት ያካሄዳቸውን የአየር ድብደባዎች በተመለከተ የተዛባ ግንዛቤ ቢኖርም፣ በተቃራኒው ጥቃቶቹ ዒላማ ያደረጉት የህወሓት የጦር መሣሪያ ማምረቻ እና የጦር ትጥቅ ጥገና ጣቢያዎችን ብቻ ነው ብሏል። 

የመከላከያ ሠራዊት የሚያከውናቸው እነዚህ ሥራዎች የሽብር ድርጅቱ ከባድ የጦር መሣሪያዎችን እና ሌሎች ሕገወጥ የጦር መሣሪያዎችን ለመሸሸግ የሚጠቀምባቸውን እና ወደ ወታደራዊ መገልገያነት የቀየራቸውን የተወሰኑ ቦታዎች ከጥቅም ውጭ ለማድረግ ያለመ ነው ሲልም አስታውቋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: endf, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, terrorism, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 22, 2021 12:00 pm at 12:00 pm

    እናንተ ይህን የድብደባ ዜና ስታናፍሱ ሌላም ድግግሞሽ ድብደባ መፈጸሙን እየሰማን ነው። የሚገርመው እብደታችን ሰማይ ጠቀስ በመሆኑ የገነባነውን መልስን የምናወድም ጅላ ጅሎች ነን። ግን ወያኔ ሃርነት ትግራይ ለትግራይ ህዝብ ነው እያለ ሰውና ሰው እንዲጫረስ ማድረጉ ምን ያህል የፓለቲካ ሰካራሞች እንደሆኑ ያረጋግጣል። ሰው በጦር መሳሪያ ሌላውን አስጎብሶ ለዘለቄታ መኖር አይችልም። ቢሞከርም ዘላቂነት የለውም። የሞከሩትም የሮም አወዳደቅን ሲወድቁ አይተናል። ለምን ይሆን ግን ከዘመን ዘመን ሰላም አጥተን ሁሌ ስንናቆር የምንኖረው? ወንድምና እህቱን ገድሎ የሚፎክር በአለም ላይ ያለ ወያኔ ሌላ ፍጥረት አይገኝም። አሁን ማን ይሙት የአማራና የአፋር ህዝብ ለትግራይ ህዝብ ጠላቱ ነው? የትግራይ ህዝብ ለእነዚህ ወገኖች ጠላት ነው? ይህ የውሸት ፓለቲካ የፈጠረው መርዝ እንጂ ሌላ አይደለም። አንድ ቤተሰብ 9 ልጆች ከወለድ በህዋላ ሳያስቡት ሌላ ተረገዘና ሰፈር ሁሉ ጉድ ሲል እናት ስም አውጭለት ትባላለች። ስሙንም በዛብኝ አለችው። እረ ይህ ስም ይቀየር ሲባል አይቻልም ከአባቱ ስም ጋር ስለሚገጣጠም ችግሬንም ሁሉንም የሚያሳይ ነው በማለት የልጅ ስም በዛብኝ በቀኑ ተባለ። አሁንም የሃበሻው ሃበሳና መከራ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ ነው። የጨነቀው እርጉዝ ያገባል አይነት። ይገርማል እንዴት ባለ ሂሳብ ነው ሌላው የለፋበትን ሃብትና ንብረት ወያኔ እያጨደና እየዘረፈ ወደ ትግራይ የሚያጓጉዘው? ይህ የታመመ ጭንቅላት አይደለም ለሚሉ ሁሉ እውነት ትመስክርላቸው።
    ወያኔ ጊንጥ ነው በአየር ይሁን በምድር ተደበደበ በህዝብ መካከል በመደበቅና ለአለም ህዝብ የውሸትና የፈጠራ ዜናን በማሰራጨት ድረሱልኝ ማለቱ እሙን ነው። ወያኔን የሚያገለግለው የአሜሪካው CNN and BBC Online እንዲሁም ሌሎች ንፋስ ዘግነው ማእበል አመንጪ የውሸት የወሬ አውታሮች በኢትዮጵያ መንግስት የአየር ድብደባ አንዲት ነፍሰ ጡር ሴት ተገደለች በማለት አናፈሱ። ይህች ያልታደለች ፍጥሩ ተጎድታ ሊሆን ይችላል። የሚገርመው ግን የኢትዮጵያ መንግስት የተከለከለ መርዝ ነክ መሳሪያ ተጠቀመ ብለውም የዘገቡም ነበሩ። ያው ወንዝ ላይ ወያኔ የጣላቸው አስከሬኖች አይነት ፓለቲካ። የሚገርመኝ ሰው ይህን ሁሉ ግፍ እያደረገ ቁጭ ብሎ እንጀራ ቆርሶ መብላቱ ነው። ከዘረኝነት የጠራ ጭንቅላት ያለው ሰው ወይ ያብዳል ወይም ይመንናል። በሰው አስከሬንና ሞት መሳለቅ የራስን አፈር መሆን መዘንጋት ነው።
    ባጭሩ የሃበሻው ፓለቲካ እንደ ደ/አፍሪቃው የነጭ የዘር ፓለቲካ አፓርታይድ ነው። በክልሉ ብቻ ተወስኖ የሚኖር ከብት ብቻ ነው። የሰው ልጅ በፈለገው ተዘዋውሮ ሰርቶ ኑሮውን ያሸንፋል። የሃበሻው የዘር ፓለቲካ ሽፍላ እንደሆነ ዋናው ማሳያው ለዘራቸውና ለቋንቋቸው የሚያቀነቅኑ ሰዎች እግሬ አውጭኝ በማለት ወይም በልዪ ልዪ ብልሃት ውጭ ሃገር ወጥተው የሚኖሩት ከዝንቅና ነጻ ከሆነ ሃገርና ህዝብ ጋር ነው። በሰውኛ መለኪያ ሰውን እንደመለካት ወንዝ በማያሻግር ቋንቋ ራስን ሽፍኖ ሰውን በዘርና በጎሳ በመለየት ማሰቃየት አውሬነት ነው። አሁን በሰሜኑ የሃገራችን ክፍሎችና በሌሎችም ክልሎች የምናየው እኛ ብቻ ለእኛ ብቻ የሚል አብሮ መኖርን የገፈተረ አፓርታይድን የሚያሰፍን ጭፍን አስተሳሰብና ድርጊት ነው። ከዘመናት በፊት ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህን እሳት ወይ አበባ በተሰኘው ግጥሙ አንድ ክፍል ውስጥ እንዲህ ይለናል።
    እኔው ከእኔው ስከራከር
    ተጨብጨ የማብላላው
    ያው መቼም እኔም እንደ ሰው
    የሃቅ ረሃብ ነፍሴን ሲያውከው
    ልቤን ልቤ ሲሞግተው
    እውነትስ ምንትስ ማን ነው?
    እያለ ነው።

    የእኔም ጥያቄ “እውነትስ ምንትስ ማን ነው”? መቼ ነው ከመገዳደልና መሰደድ፤ ተራብን ድረሱልን ከማለት ምድሪቱ የምታርፈው? ጠብቀን እንይ። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule