• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የመቀሌ አየር ድብደባዎች ዒላማቸውን የመቱ ናቸው

October 20, 2021 11:04 am by Editor 1 Comment

የመከላከያ ሠራዊት ያካሄዳቸው የአየር ድብደባዎች ዒላማ ያደረጉት የህወሓት የጦር መሣሪያ ማምረቻ እና የጦር ትጥቅ ጥገና ጣቢያዎች ላይ ብቻ እንደሆነና ኢላማቸውን የመቱ መሆናቸው ተገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ መረጃ ማጣሪያ ገጽ ባወጣው መግለጫ፤ የመከላከያ ሠራዊት ያካሄዳቸውን የአየር ድብደባዎች በተመለከተ የተዛባ ግንዛቤ ቢኖርም፣ በተቃራኒው ጥቃቶቹ ዒላማ ያደረጉት የህወሓት የጦር መሣሪያ ማምረቻ እና የጦር ትጥቅ ጥገና ጣቢያዎችን ብቻ ነው ብሏል። 

የመከላከያ ሠራዊት የሚያከውናቸው እነዚህ ሥራዎች የሽብር ድርጅቱ ከባድ የጦር መሣሪያዎችን እና ሌሎች ሕገወጥ የጦር መሣሪያዎችን ለመሸሸግ የሚጠቀምባቸውን እና ወደ ወታደራዊ መገልገያነት የቀየራቸውን የተወሰኑ ቦታዎች ከጥቅም ውጭ ለማድረግ ያለመ ነው ሲልም አስታውቋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: endf, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, terrorism, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 22, 2021 12:00 pm at 12:00 pm

    እናንተ ይህን የድብደባ ዜና ስታናፍሱ ሌላም ድግግሞሽ ድብደባ መፈጸሙን እየሰማን ነው። የሚገርመው እብደታችን ሰማይ ጠቀስ በመሆኑ የገነባነውን መልስን የምናወድም ጅላ ጅሎች ነን። ግን ወያኔ ሃርነት ትግራይ ለትግራይ ህዝብ ነው እያለ ሰውና ሰው እንዲጫረስ ማድረጉ ምን ያህል የፓለቲካ ሰካራሞች እንደሆኑ ያረጋግጣል። ሰው በጦር መሳሪያ ሌላውን አስጎብሶ ለዘለቄታ መኖር አይችልም። ቢሞከርም ዘላቂነት የለውም። የሞከሩትም የሮም አወዳደቅን ሲወድቁ አይተናል። ለምን ይሆን ግን ከዘመን ዘመን ሰላም አጥተን ሁሌ ስንናቆር የምንኖረው? ወንድምና እህቱን ገድሎ የሚፎክር በአለም ላይ ያለ ወያኔ ሌላ ፍጥረት አይገኝም። አሁን ማን ይሙት የአማራና የአፋር ህዝብ ለትግራይ ህዝብ ጠላቱ ነው? የትግራይ ህዝብ ለእነዚህ ወገኖች ጠላት ነው? ይህ የውሸት ፓለቲካ የፈጠረው መርዝ እንጂ ሌላ አይደለም። አንድ ቤተሰብ 9 ልጆች ከወለድ በህዋላ ሳያስቡት ሌላ ተረገዘና ሰፈር ሁሉ ጉድ ሲል እናት ስም አውጭለት ትባላለች። ስሙንም በዛብኝ አለችው። እረ ይህ ስም ይቀየር ሲባል አይቻልም ከአባቱ ስም ጋር ስለሚገጣጠም ችግሬንም ሁሉንም የሚያሳይ ነው በማለት የልጅ ስም በዛብኝ በቀኑ ተባለ። አሁንም የሃበሻው ሃበሳና መከራ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ ነው። የጨነቀው እርጉዝ ያገባል አይነት። ይገርማል እንዴት ባለ ሂሳብ ነው ሌላው የለፋበትን ሃብትና ንብረት ወያኔ እያጨደና እየዘረፈ ወደ ትግራይ የሚያጓጉዘው? ይህ የታመመ ጭንቅላት አይደለም ለሚሉ ሁሉ እውነት ትመስክርላቸው።
    ወያኔ ጊንጥ ነው በአየር ይሁን በምድር ተደበደበ በህዝብ መካከል በመደበቅና ለአለም ህዝብ የውሸትና የፈጠራ ዜናን በማሰራጨት ድረሱልኝ ማለቱ እሙን ነው። ወያኔን የሚያገለግለው የአሜሪካው CNN and BBC Online እንዲሁም ሌሎች ንፋስ ዘግነው ማእበል አመንጪ የውሸት የወሬ አውታሮች በኢትዮጵያ መንግስት የአየር ድብደባ አንዲት ነፍሰ ጡር ሴት ተገደለች በማለት አናፈሱ። ይህች ያልታደለች ፍጥሩ ተጎድታ ሊሆን ይችላል። የሚገርመው ግን የኢትዮጵያ መንግስት የተከለከለ መርዝ ነክ መሳሪያ ተጠቀመ ብለውም የዘገቡም ነበሩ። ያው ወንዝ ላይ ወያኔ የጣላቸው አስከሬኖች አይነት ፓለቲካ። የሚገርመኝ ሰው ይህን ሁሉ ግፍ እያደረገ ቁጭ ብሎ እንጀራ ቆርሶ መብላቱ ነው። ከዘረኝነት የጠራ ጭንቅላት ያለው ሰው ወይ ያብዳል ወይም ይመንናል። በሰው አስከሬንና ሞት መሳለቅ የራስን አፈር መሆን መዘንጋት ነው።
    ባጭሩ የሃበሻው ፓለቲካ እንደ ደ/አፍሪቃው የነጭ የዘር ፓለቲካ አፓርታይድ ነው። በክልሉ ብቻ ተወስኖ የሚኖር ከብት ብቻ ነው። የሰው ልጅ በፈለገው ተዘዋውሮ ሰርቶ ኑሮውን ያሸንፋል። የሃበሻው የዘር ፓለቲካ ሽፍላ እንደሆነ ዋናው ማሳያው ለዘራቸውና ለቋንቋቸው የሚያቀነቅኑ ሰዎች እግሬ አውጭኝ በማለት ወይም በልዪ ልዪ ብልሃት ውጭ ሃገር ወጥተው የሚኖሩት ከዝንቅና ነጻ ከሆነ ሃገርና ህዝብ ጋር ነው። በሰውኛ መለኪያ ሰውን እንደመለካት ወንዝ በማያሻግር ቋንቋ ራስን ሽፍኖ ሰውን በዘርና በጎሳ በመለየት ማሰቃየት አውሬነት ነው። አሁን በሰሜኑ የሃገራችን ክፍሎችና በሌሎችም ክልሎች የምናየው እኛ ብቻ ለእኛ ብቻ የሚል አብሮ መኖርን የገፈተረ አፓርታይድን የሚያሰፍን ጭፍን አስተሳሰብና ድርጊት ነው። ከዘመናት በፊት ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህን እሳት ወይ አበባ በተሰኘው ግጥሙ አንድ ክፍል ውስጥ እንዲህ ይለናል።
    እኔው ከእኔው ስከራከር
    ተጨብጨ የማብላላው
    ያው መቼም እኔም እንደ ሰው
    የሃቅ ረሃብ ነፍሴን ሲያውከው
    ልቤን ልቤ ሲሞግተው
    እውነትስ ምንትስ ማን ነው?
    እያለ ነው።

    የእኔም ጥያቄ “እውነትስ ምንትስ ማን ነው”? መቼ ነው ከመገዳደልና መሰደድ፤ ተራብን ድረሱልን ከማለት ምድሪቱ የምታርፈው? ጠብቀን እንይ። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule