• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከጥቅምት ወር ጀምሮ ለትግራይ የበጀት ገንዘብ አይለቀቅም

October 14, 2020 12:01 am by Editor 1 Comment

ከትግራይ ክልል ጋር በተያያዘ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በክልሉ የሚገኙ የካቢኔ አባላት ህጋዊ ባልሆነ ምርጫ ተመርጠናል በሚል የሀገሪቱን ህገ መንግሥት በመጣሳቸው አሁን ባለው ሁኔታ የገንዘብ ሚኒስቴር ለትግራይ ክልል መንግሥት በጀት እንደማይለቅ የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ተናገሩ።

በትግራይ ክልል ለሚገኙ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት በወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደሮች በኩል በተጠና ሁኔታ እንዲደርሳቸው ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።

ይህ ለሁለተኛው ሩብ ዓመት (ጥቅምት-ህዳር-ታህሣሥ) ከፌዴራል ለክልሎች የሚለቀቅ በጀት እንደሆነ ይታወቃል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Politics, Right Column Tagged With: tigray tplf election, tplf fake election

Reader Interactions

Comments

  1. ዘረ-ያዕቖብ says

    October 20, 2020 07:02 am at 7:02 am

    ገና TPLF ከኣሽዓነት ወደ ህወሓትነት የሽግግር ስዓታት ላይ በምትገኝበት ጊዝያቶች ላይ የዓድዋን ገጠሮችንና እንዲሁም እንደነ እንትጮ አይነት ትናንሽ ወደ ከተማነትን የሚከጅላቸው ቦታዎች ዘንዳ እጅን አሸልኮ ንብረትን ስቦ ወደኪስ የማግባት መንገዶች በነበሯት ስዓታት ላይ፣ ደርግ ለነይሓ ከተማ ልሁን ባዮች አይነቶች ቦታዎችን እንትጮ ውስጥ እህል ማከፋፈያ ካምፕ አቁሞ ለህዝበ ገጠር ዓድዋ፣ እንትጮ ሄዳችሁ እህል ውሰዱ ይላል:: ከኣሽዓነት ወደ ህወሓትነት ሽግግር ስዓታት ላይ የምትገኘዋ ወያነም፣ የደርግ የእህል ማከፋፈያ ካምፕ ውስጥ፣ ውስጥ ውስጡን በመለመለቻቸው ተባባሪ ካድሬዎችዋ በኩል አድርጋ ከካምፑ ከፍተኛውን የእህል ክፋል ወደ ራስዋው መሳብን ታበዛና ለተራበው ህዝብ የሚደርሰው እህል እየቀነሰ መምጣቱን የታዘቡ ይሓዎች፣ የእህል ማደያው ካምፕ ወደ ዓድዋ ከተማ እንዲዟዟርና (ዓድዋን ገና ደርግ ነበር የሚቆጣጠረው) የእንትጮ ማከፋፈያ እንደማሻቸው ይናገራሉ:: እንዲህ ብለው ሃሳብ ያቀረቡትን ሰዎች ገና አሽዓዋ TPLF በሌሊት ጭለማን ተከናንባ ወደየቤታቸው ዘልቃ ትገባና ግማሽ ሃብታቸውን፣ ድመትና ውሻም ሳይቀር ትከፍልና የቤት አባወራዎቹን እስከነ ግማሽ ንብረታቸ under hostage አስገብታ (ጠለፋ አካሂዳ) ወደ ሽረ ጉድጓድ እስር ቤቷ ኮብኩባ ትነዳና፣ ንብረታቸውን ለራስዋ ገቢ አድርጋ አባወራዎቹን ደግሞ በጭለማ ጉድጓድ እስር ቤቷ ውስጥ ፀሃይንም ሳያዩ ለሰባት ዓመታት ታስራለች:: ጤነኞችና እስከነ ጥቁር ፀጉራቸው ወደ ሽረ ጉድጓድ የተወሰዱት አባወራዎቹ ከሰባት አመታት በኋላ ከጭለማ እስር ሲለቀቁ ከግራ በኩል ሆነው ሲያነግሯቸው በቀኝ በኩል የሆነ ድምፅ ይሰማቸውና ወደ ቀኝ በኩል ዞር ብለው ምን አልከኝ የሚሉና፣ ፀጉራቸው በመላው እስከነ ቅንድባቸውም ሳይቀር ሸበቶ ብቻ ሆነው ይወጣሉ:: አባወራዎቹ እስከነ ግማሽ ሃብታቸው ከገዛ ግቢያቸው ተነድተው በሚኮበኮቡበት ጊዜ፣ ሚስቶቻቸው ንብረቴን አትውሰዱብኝ የልጆቼ ማሳደግያ ነው፣ ባለቤቴንም አትውሰዱብኝ ልጆቼን ብቻዬን ለማሳደግ ይከብደኝልና ብለው በጨለማ ስዓታት ላይ ድምፃቸውን ለማሰማት ሞክረው ነበር:: የወያነ መልስ ግን ጨከን ያለና፣ ባለቤትዎ እህል ዓድዋ ይከፋፈለን የሚል ሃጥያት ስለተናገሩ ይታሰራሉ፣ ከንብረታችሁም የእርሳቸውን ከፊል ግማሹ ንብረታችሁ ይወረሳል፣ ስለሆነም አሁን አፍዎን ይያዙ የሚለውን ቃል ወርውረውባቸ ባሎችንና ግማሽ ንብረትን ይዘው ሄዱ:: ታድያ አሁን “በትግራይ ክልል ለሚገኙ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት በወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደሮች በኩል በተጠና ሁኔታ እንዲደርሳቸው ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።” የሚለውን አረፍተ ነገር ሳይ፣ የጥንቱ ጭካኔ ትዝ አለኝና ጭካኔው አሁንም እንዳይደገም ጥናቱ እንድያውጠነጥነው ለማሳሰብ ያህል አባባላችንን ሰነዘርን እንጂ፣ ገና ጅቦች አሉ ተብሎ ጠቅላላ ህዝቡን ከሁሉም ጥቅም ላለመቁረጥ የሚደረገውን ጥረት ሳናደንቅ አናልፍም:: የተሻለ ቀን ያምጣ፣ unity in diversity!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule