• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስምና ገመድ!!

September 14, 2013 03:55 am by Editor 4 Comments

በተለያዩ ምክንያቶች ለረጅም ጊዜ አቋርጠነው የነበረውን የግጥም ጨዋታ እንደገና ጀምረናል፡፡ ከዚህ በፊት እናደርገው እንደነበረው አንባቢያን ይህንን ግጥም አንብባችሁ አስተያየታችሁን በግጥም እንድትሰጡና ጨዋታውን እንድታደምቁት እንጋብዛለን፡፡ ለዛሬ የመረጥነውን ግጥም ከነፎቶግራፉ ያገኘነው ከደመቀ ከበደ የፌስቡክ ገጽ ላይ ነው፡፡ገጣሚ ደመቀ ከበደን ለግጥሙና ለፎቶው ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡

ስምና ገመድ!!

አዝማሪ እንዲህ አለ፤
“ሰው ሰበበኛ ነው – ምክንያት አያጣም
እንኳን ዝናብ ዘንቦ – ሲዳምን አይወጣም፤”
እኔ ግን እላለሁ፤
አተተ በተተ
ወዘተ ወዘተ
በሚል አርቲ ቡርቲ – ዕድሜ ከምንጨርስ
ህይወት ከምናጣ
ፋይዳ ላለው ነገር – ቁልቁለት እንውረድ
አቀበት እንውጣ፤

ያኔ

አላስወርድ ካለህ – ወይም አላስወጣ
ማሰሪያ ከሆነህ – አሊያም ጋሬጣ
ያኔ አይንህን አውጣ
ወይ ሆ! ብለህ ውጣ፤

ያለዚያ

ቀብድ በበላች ሀገር – በድህነት ቁና
ሀብታምነት ከንቱ – ዝነኝነት መና፤
ነው እንጂ ነውና
በስም የሚከብሩ
በስም የሚከስሩ
በስም የሚወጡ
በስም የሚወርዱ
በስም የሚያለቅሱ
በስም የሚያብሱ
በስም የሚጥሉ
በስም የሚያነሱ
በሞላባት አገር – በስም ለታጠረች
ስምህ ገመድህ ነች
ድንገት ታስርሀለች – ወይም ታንቅሃለች፤
‹‹ከስብስም ይሸታል!›› – ብላ እየተረተች
ስምህ ሁሉን ሆና
ወይ ትጥልሃለች – ወይ ታነሳሃለች፤

ስለዚህ

በስም ከፍታ ላይ – እላይ እንድትወጣ
ጫፉን እንድትረግጥ
ዘዴ ዘይድና – ወይ ገመዱን ፍታ
ወይ ገመዱን ቁረጥ!!
(ደመቀ ከበደ – ጣና ዳር)

ከዚህ በፊት ያቀረብናቸው የግጥም ጨዋታዎች ላይ ትሳተፉ የነበራችሁ ሁሉ በድጋሚ እንድትሳተፉ፤ አዲሶችም እንዲሁ በጨዋታው እንድትገቡ ታድማችኋል፡፡ ምናልባት የበፊቶቹ ጨዋታዎች ምን ይመስሉ ነበር የሚለውን ለመመልከት ከዚህ በፊት ያቀረብናቸውን እንደሚከተለው አቅርበናል፡፡ ርዕሶቹ ላይ በመጫን ማንበብ ይቻላል፡፡

ሽ – ሽ – ት …! (አብዲ ሰኢድ)

በሳቅ ፍርስ አሉ (የካናዳው ከበደ)

ህልመኛው (ቃልኪዳን)

እኔ ምን አገባኝ? (ኑረዲን ዒሳ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው! says

    September 14, 2013 07:46 pm at 7:46 pm

    አውራ ድሮ!..ኪ ኪ..ኪ በለው! ኩኩሉ ቀረ ማለት ነው?
    ********************
    እናንት ምክንያተኞች ሰበብ ያሰራችሁ
    አትፈቱ አታስፈቱ ምነው ተተባተባችሁ ?

    ያኔ….
    “የዶሮ ልብ! ፈሪ!” ስትተርቱብኝ ኑሮ አስጠልቶኝ
    ይኼው ተመልከቱ የሠው ልብ እንዳለኝ
    ነፃነቴን መረጥኩ ገመድን አስፈታኝ
    ዘመን ተቀይሮ የሚገዛኝ የለ ኑሮ አስወደደኝ።

    አሁንማ..
    እርስ በእርስ ታስራችሁ በዝቶ ሰቆቃ ግፋችሁ
    ጠዋት ነቅቼ ንቁ !በቃ !ተነሱ !ብላችሁ
    ገና ሆ! ሳትሉ ደክሟችሁ ተኛችሁ ።

    ታዲያ…
    በመንቀሳቀስ መብቴ በእኔ ማፌዛችሁ ለነጻነት ስጠር
    ተናጋሪ እንስሳ ህዝብ ነኝ የሚል ሰው በቁሙ ሲታሠር
    እንዴት አይወደድ ዶሮ በሰው ሀገር?
    ************************
    የደመቀ ከባድ ነው በለው! ከሀገረ ካናዳ

    Reply
  2. emran says

    September 14, 2013 09:07 pm at 9:07 pm

    ስምን መገንባት ነው
    በጠንካራ አለት ላይ
    ኖሮ ለመታየት
    ከላይኞቹ ላይ
    ሞቶ ለመታወስ
    ከመቃብር በላይ

    Reply
  3. ወለላዬ says

    September 15, 2013 12:40 am at 12:40 am

    ከላይ ስመለከት መጀመሪያ ሳነብ
    መረዳት ችያለሁ ስው መውደዱን ሰበብ
    በዚሁ ጉዳይ ላይ ከሳፍኩት ግጥሞቼ
    እንካችሁ ላቅርባት አንዲቷን አውጥቼ

    “እጃችሁ ከገባ ድንገት ብታገኙት
    ሰይጣን ምናባቱ ደብድቡ ውገሩት
    ነገር ግን ጨርሶ አይገባም መግደል
    ጥፋት ስናተፋ ማን አሳተኝ እንበል”
    ግጥም ወለላዬ

    እውነት ነው በማለት ይሄን እንለፈው
    ውስት ገባ ብለን ሌላውን እንየው
    ሀብት ዝነኝነት መሞገስ መከበር
    ፍላጎቱም ቢሆን የሰው ልጅ ሲፈጠር
    ለፍቶ ብዙ ደክሞ ወይም እድል ቀንቶት
    ሁሉንም ጨብጦ ቢችልም ለማግኘት
    እስከመጨረሻው ስሙን አስከብሮ
    ካልያዘው በስተቀር ይገባል ከዜሮ
    ይሄ ነው ነገሩ ወንድሜ ደመቀ
    ለሁሉም አስረዳ ንገር ላላወቀ

    Reply
  4. YeKanadaw Kebede says

    September 17, 2013 12:31 am at 12:31 am

    አዎ…አንዱ እኔ ነኝ ሰበበኛው
    ስትጮሁ የማልሰማ፤ ስትነሱ የምተኛው
    ወሬ ስትጠርቁ
    ፀጉር ስትሰነጥቁ
    የዕምነት ገመዱ ሰለለ
    የስም ማዕረጉ ቀለለ
    ዓይናችን እያስተዋለ
    ክብራችን
    ታሪካችን
    ረከሰ…ጥምቡን-ጣለ
    ታዲያ
    ምን ቀረኝ ብየ ልውጣ
    የትኛው ቢሮ ልምጣ?
    ስትጮሁ የማልሰማ፤ ስትነሱ የምተኛው
    አዎ…አንዱ እኔ ነኝ ሰበበኛው

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule