• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስምና ገመድ!!

September 14, 2013 03:55 am by Editor 4 Comments

በተለያዩ ምክንያቶች ለረጅም ጊዜ አቋርጠነው የነበረውን የግጥም ጨዋታ እንደገና ጀምረናል፡፡ ከዚህ በፊት እናደርገው እንደነበረው አንባቢያን ይህንን ግጥም አንብባችሁ አስተያየታችሁን በግጥም እንድትሰጡና ጨዋታውን እንድታደምቁት እንጋብዛለን፡፡ ለዛሬ የመረጥነውን ግጥም ከነፎቶግራፉ ያገኘነው ከደመቀ ከበደ የፌስቡክ ገጽ ላይ ነው፡፡ገጣሚ ደመቀ ከበደን ለግጥሙና ለፎቶው ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡

ስምና ገመድ!!

አዝማሪ እንዲህ አለ፤
“ሰው ሰበበኛ ነው – ምክንያት አያጣም
እንኳን ዝናብ ዘንቦ – ሲዳምን አይወጣም፤”
እኔ ግን እላለሁ፤
አተተ በተተ
ወዘተ ወዘተ
በሚል አርቲ ቡርቲ – ዕድሜ ከምንጨርስ
ህይወት ከምናጣ
ፋይዳ ላለው ነገር – ቁልቁለት እንውረድ
አቀበት እንውጣ፤

ያኔ

አላስወርድ ካለህ – ወይም አላስወጣ
ማሰሪያ ከሆነህ – አሊያም ጋሬጣ
ያኔ አይንህን አውጣ
ወይ ሆ! ብለህ ውጣ፤

ያለዚያ

ቀብድ በበላች ሀገር – በድህነት ቁና
ሀብታምነት ከንቱ – ዝነኝነት መና፤
ነው እንጂ ነውና
በስም የሚከብሩ
በስም የሚከስሩ
በስም የሚወጡ
በስም የሚወርዱ
በስም የሚያለቅሱ
በስም የሚያብሱ
በስም የሚጥሉ
በስም የሚያነሱ
በሞላባት አገር – በስም ለታጠረች
ስምህ ገመድህ ነች
ድንገት ታስርሀለች – ወይም ታንቅሃለች፤
‹‹ከስብስም ይሸታል!›› – ብላ እየተረተች
ስምህ ሁሉን ሆና
ወይ ትጥልሃለች – ወይ ታነሳሃለች፤

ስለዚህ

በስም ከፍታ ላይ – እላይ እንድትወጣ
ጫፉን እንድትረግጥ
ዘዴ ዘይድና – ወይ ገመዱን ፍታ
ወይ ገመዱን ቁረጥ!!
(ደመቀ ከበደ – ጣና ዳር)

ከዚህ በፊት ያቀረብናቸው የግጥም ጨዋታዎች ላይ ትሳተፉ የነበራችሁ ሁሉ በድጋሚ እንድትሳተፉ፤ አዲሶችም እንዲሁ በጨዋታው እንድትገቡ ታድማችኋል፡፡ ምናልባት የበፊቶቹ ጨዋታዎች ምን ይመስሉ ነበር የሚለውን ለመመልከት ከዚህ በፊት ያቀረብናቸውን እንደሚከተለው አቅርበናል፡፡ ርዕሶቹ ላይ በመጫን ማንበብ ይቻላል፡፡

ሽ – ሽ – ት …! (አብዲ ሰኢድ)

በሳቅ ፍርስ አሉ (የካናዳው ከበደ)

ህልመኛው (ቃልኪዳን)

እኔ ምን አገባኝ? (ኑረዲን ዒሳ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው! says

    September 14, 2013 07:46 pm at 7:46 pm

    አውራ ድሮ!..ኪ ኪ..ኪ በለው! ኩኩሉ ቀረ ማለት ነው?
    ********************
    እናንት ምክንያተኞች ሰበብ ያሰራችሁ
    አትፈቱ አታስፈቱ ምነው ተተባተባችሁ ?

    ያኔ….
    “የዶሮ ልብ! ፈሪ!” ስትተርቱብኝ ኑሮ አስጠልቶኝ
    ይኼው ተመልከቱ የሠው ልብ እንዳለኝ
    ነፃነቴን መረጥኩ ገመድን አስፈታኝ
    ዘመን ተቀይሮ የሚገዛኝ የለ ኑሮ አስወደደኝ።

    አሁንማ..
    እርስ በእርስ ታስራችሁ በዝቶ ሰቆቃ ግፋችሁ
    ጠዋት ነቅቼ ንቁ !በቃ !ተነሱ !ብላችሁ
    ገና ሆ! ሳትሉ ደክሟችሁ ተኛችሁ ።

    ታዲያ…
    በመንቀሳቀስ መብቴ በእኔ ማፌዛችሁ ለነጻነት ስጠር
    ተናጋሪ እንስሳ ህዝብ ነኝ የሚል ሰው በቁሙ ሲታሠር
    እንዴት አይወደድ ዶሮ በሰው ሀገር?
    ************************
    የደመቀ ከባድ ነው በለው! ከሀገረ ካናዳ

    Reply
  2. emran says

    September 14, 2013 09:07 pm at 9:07 pm

    ስምን መገንባት ነው
    በጠንካራ አለት ላይ
    ኖሮ ለመታየት
    ከላይኞቹ ላይ
    ሞቶ ለመታወስ
    ከመቃብር በላይ

    Reply
  3. ወለላዬ says

    September 15, 2013 12:40 am at 12:40 am

    ከላይ ስመለከት መጀመሪያ ሳነብ
    መረዳት ችያለሁ ስው መውደዱን ሰበብ
    በዚሁ ጉዳይ ላይ ከሳፍኩት ግጥሞቼ
    እንካችሁ ላቅርባት አንዲቷን አውጥቼ

    “እጃችሁ ከገባ ድንገት ብታገኙት
    ሰይጣን ምናባቱ ደብድቡ ውገሩት
    ነገር ግን ጨርሶ አይገባም መግደል
    ጥፋት ስናተፋ ማን አሳተኝ እንበል”
    ግጥም ወለላዬ

    እውነት ነው በማለት ይሄን እንለፈው
    ውስት ገባ ብለን ሌላውን እንየው
    ሀብት ዝነኝነት መሞገስ መከበር
    ፍላጎቱም ቢሆን የሰው ልጅ ሲፈጠር
    ለፍቶ ብዙ ደክሞ ወይም እድል ቀንቶት
    ሁሉንም ጨብጦ ቢችልም ለማግኘት
    እስከመጨረሻው ስሙን አስከብሮ
    ካልያዘው በስተቀር ይገባል ከዜሮ
    ይሄ ነው ነገሩ ወንድሜ ደመቀ
    ለሁሉም አስረዳ ንገር ላላወቀ

    Reply
  4. YeKanadaw Kebede says

    September 17, 2013 12:31 am at 12:31 am

    አዎ…አንዱ እኔ ነኝ ሰበበኛው
    ስትጮሁ የማልሰማ፤ ስትነሱ የምተኛው
    ወሬ ስትጠርቁ
    ፀጉር ስትሰነጥቁ
    የዕምነት ገመዱ ሰለለ
    የስም ማዕረጉ ቀለለ
    ዓይናችን እያስተዋለ
    ክብራችን
    ታሪካችን
    ረከሰ…ጥምቡን-ጣለ
    ታዲያ
    ምን ቀረኝ ብየ ልውጣ
    የትኛው ቢሮ ልምጣ?
    ስትጮሁ የማልሰማ፤ ስትነሱ የምተኛው
    አዎ…አንዱ እኔ ነኝ ሰበበኛው

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule