• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እኔ ምን አገባኝ?

October 15, 2012 10:46 pm by Editor 10 Comments

እኔ ምን አገባኝ

እኔ ምን አገባኝ የምትሉት ሐረግ

እሱ ነው ሀገሬን ያረዳት እንደ በግ

የሚል ግጥም ልጽፍ

ስሜት አንዘርዝሮኝ ብድግ አልኩኝና

ምን አገባኝ ብየ ቁጭ አልኩ እንደገና::

ግጥሙ የተወሰደው ከኑረዲን ዒሳ ፌስቡክ ነው:: ባለፈው ሌባዬ በሚል ርዕስ ላወጣነው የግጥም ጨዋታ የተሳተፋችሁትን ሁሉ በተለይ ደግሞ Tsinat ፣ Gedion Adenew እና አበበ አዲስ ከልብ እናመሰግናለን:: እስቲ ለዚህኛውም አንድ ሁለት ሁላችንም እንበል!! እንደበፊቱ ሁሉ ምላሹ በግጥም ቢሆን ጨዋታዋን ሞቅ ያደርገዋል::

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. dawit says

    October 16, 2012 12:01 am at 12:01 am

    ጎልጉሎች ቀስ በቀስ የወግ ገበታ ጀመራችሁ እኮ!! ድንቅ ጦማር ናት። ግን ለምን ይዘገያል። ለምን ታሳንሱታላችሁ?

    Reply
    • Editor says

      October 16, 2012 01:41 am at 1:41 am

      ሰላም dawit
      ለመልካሙ አስተያየትዎ ከፍ ያለ ምስጋና እናቀርባለን:: በምክርዎ መሠረት ላለመዘግየት እንሞክራለን::ማነሱን በተመለከተ ምናልባት እንዲናፈቅና እንዲጣፍጥ ብለን ይሆን? 🙂

      አርታኢ/Editor
      ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ/Golgul: the Internet Newspaper
      http://www.goolgule.com
      editor@goolgule.com

      Reply
  2. Tsinat says

    October 16, 2012 12:19 am at 12:19 am

    ግጥሙን እንዳነበብኩ ብእሬን ብድግ አረግኩ
    ስላገር ልነግሮት ልሞግቶት ወሰንኩ
    ግና ምን ያደርጋል አንድ ሃረግ እንደጨረስኩ
    ምን አገባኝ ብዬ እኔም ብእሬን መለስኩ::

    Reply
  3. ሰማኸኝ says

    October 16, 2012 11:10 am at 11:10 am

    በግጥም ጨዋታው ልሳተፍ አልኩና
    ለጨዋታው የሚሆን ስንኞች ቋጥሬ
    ፖስት ላደርግ ብዬ …
    …አንድ ጊዜ …
    … ሞክሬ
    እምቢ ሲለኝ ጊዜ…
    ሃሳቤን ቀይሬ…
    … ምን አገባኝ ብዬ
    ተውኩት እንደገና::

    Reply
  4. yeKanadaw kebede says

    October 16, 2012 07:08 pm at 7:08 pm

    ምን አገባኝ ብለህ የተውከው ቁም-ነገር
    ዉሎ-አድሮ፤ ጎልብቶ መመለሱ ላይቀር
    እረፍት የሚሰጥህ ብትጨርሰው ነበር

    Reply
  5. Gedeon says

    October 16, 2012 10:03 pm at 10:03 pm

    ድፍን አገር ወገን — ‘ምን አገባኝ’ ገብቶት
    ወኔውን ተሰልቦ — ‘ነግ-በኔ’ ን ረስቶት

    ‘ምን አገባኝ?!’ ያለው ‘ያገባው ምን’ ጠፍቶት

    ድህነት ተላምዶ — ጠኔን ቀልዶበት
    በ ሰማኒያ ቆርቦ — ስንፍናን ተጋብቶት
    ‘ምን አገባኝ?!’ ይላል ትዳሩን ረስቶት!

    Reply
  6. dawit says

    October 17, 2012 02:16 am at 2:16 am

    ምን አገባኝ ማለት – ትርጉሙ ምንድነው?
    ለ-ኔ እንደመሰለኝ – ስያሜና ፍቺው
    ምን አገባኝ ማለት የሞት ሁሉ ሞት ነው፤
    ከመሞት መሰንበት ይሻላል ያላችሁ
    ቁሙበት ላዩ ላይ ምን አገባኝን ቀብራችሁ፤

    Reply
  7. yeKanadaw kebede says

    October 17, 2012 10:54 pm at 10:54 pm

    የፉክክር ደጃፍ ሳይዘጋ ቀርቶ
    አውሬውም ሌባውም ይገባል ተዝናንቶ
    ምን አገባኝ ያለው የቤቱ ባለቤት
    ‘ጠጋ በል‘ ተብሎ ይወጣል በመስኮት

    Reply
  8. inkopa says

    October 22, 2012 07:29 pm at 7:29 pm

    “ምን አገባኝ” ብለው
    የዘጉበትን ቤት
    ያገኙታል ኋላ
    ያገባው ገብቶበት!

    Reply
  9. በለው ! says

    December 30, 2012 06:08 pm at 6:08 pm

    እኔ ምን አገባኝ ?
    “እኔ ምን ቸገረኝ
    ፀሐይ ብትወጣ ባትወጣ
    ታበራልኛለች የ—መላጣ”
    በሀገር ብቻ አደለም ሲቀለድ በፀሐይ
    ሁሉን በእየፊናው ችላ ማለቱን ሳይ
    ተጠያቂው ማነው? እየተብከነከንኩ
    ስሜቴ ቢነካም ኮራሁ ንፁህ እንደሆንኩ
    ውጪ ወጣሁና አልኩ ምን አስገባኝ
    ፈገግ አልኩ እጄን ኪሴ ከተትኩ
    ለሀገሬ መታረድ ቢላዋ አልሳልኩኝ
    ኑረዲን ዒሳ አንድ ዜጋ ነው አልኩኝ !!
    ^^^^^^^^^^^^^^^^^
    በለው! ከሀገረ ካናዳ በቸር ይግጠመን

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule