• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እኔ ምን አገባኝ?

October 15, 2012 10:46 pm by Editor 10 Comments

እኔ ምን አገባኝ

እኔ ምን አገባኝ የምትሉት ሐረግ

እሱ ነው ሀገሬን ያረዳት እንደ በግ

የሚል ግጥም ልጽፍ

ስሜት አንዘርዝሮኝ ብድግ አልኩኝና

ምን አገባኝ ብየ ቁጭ አልኩ እንደገና::

ግጥሙ የተወሰደው ከኑረዲን ዒሳ ፌስቡክ ነው:: ባለፈው ሌባዬ በሚል ርዕስ ላወጣነው የግጥም ጨዋታ የተሳተፋችሁትን ሁሉ በተለይ ደግሞ Tsinat ፣ Gedion Adenew እና አበበ አዲስ ከልብ እናመሰግናለን:: እስቲ ለዚህኛውም አንድ ሁለት ሁላችንም እንበል!! እንደበፊቱ ሁሉ ምላሹ በግጥም ቢሆን ጨዋታዋን ሞቅ ያደርገዋል::

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. dawit says

    October 16, 2012 12:01 am at 12:01 am

    ጎልጉሎች ቀስ በቀስ የወግ ገበታ ጀመራችሁ እኮ!! ድንቅ ጦማር ናት። ግን ለምን ይዘገያል። ለምን ታሳንሱታላችሁ?

    Reply
    • Editor says

      October 16, 2012 01:41 am at 1:41 am

      ሰላም dawit
      ለመልካሙ አስተያየትዎ ከፍ ያለ ምስጋና እናቀርባለን:: በምክርዎ መሠረት ላለመዘግየት እንሞክራለን::ማነሱን በተመለከተ ምናልባት እንዲናፈቅና እንዲጣፍጥ ብለን ይሆን? 🙂

      አርታኢ/Editor
      ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ/Golgul: the Internet Newspaper
      http://www.goolgule.com
      editor@goolgule.com

      Reply
  2. Tsinat says

    October 16, 2012 12:19 am at 12:19 am

    ግጥሙን እንዳነበብኩ ብእሬን ብድግ አረግኩ
    ስላገር ልነግሮት ልሞግቶት ወሰንኩ
    ግና ምን ያደርጋል አንድ ሃረግ እንደጨረስኩ
    ምን አገባኝ ብዬ እኔም ብእሬን መለስኩ::

    Reply
  3. ሰማኸኝ says

    October 16, 2012 11:10 am at 11:10 am

    በግጥም ጨዋታው ልሳተፍ አልኩና
    ለጨዋታው የሚሆን ስንኞች ቋጥሬ
    ፖስት ላደርግ ብዬ …
    …አንድ ጊዜ …
    … ሞክሬ
    እምቢ ሲለኝ ጊዜ…
    ሃሳቤን ቀይሬ…
    … ምን አገባኝ ብዬ
    ተውኩት እንደገና::

    Reply
  4. yeKanadaw kebede says

    October 16, 2012 07:08 pm at 7:08 pm

    ምን አገባኝ ብለህ የተውከው ቁም-ነገር
    ዉሎ-አድሮ፤ ጎልብቶ መመለሱ ላይቀር
    እረፍት የሚሰጥህ ብትጨርሰው ነበር

    Reply
  5. Gedeon says

    October 16, 2012 10:03 pm at 10:03 pm

    ድፍን አገር ወገን — ‘ምን አገባኝ’ ገብቶት
    ወኔውን ተሰልቦ — ‘ነግ-በኔ’ ን ረስቶት

    ‘ምን አገባኝ?!’ ያለው ‘ያገባው ምን’ ጠፍቶት

    ድህነት ተላምዶ — ጠኔን ቀልዶበት
    በ ሰማኒያ ቆርቦ — ስንፍናን ተጋብቶት
    ‘ምን አገባኝ?!’ ይላል ትዳሩን ረስቶት!

    Reply
  6. dawit says

    October 17, 2012 02:16 am at 2:16 am

    ምን አገባኝ ማለት – ትርጉሙ ምንድነው?
    ለ-ኔ እንደመሰለኝ – ስያሜና ፍቺው
    ምን አገባኝ ማለት የሞት ሁሉ ሞት ነው፤
    ከመሞት መሰንበት ይሻላል ያላችሁ
    ቁሙበት ላዩ ላይ ምን አገባኝን ቀብራችሁ፤

    Reply
  7. yeKanadaw kebede says

    October 17, 2012 10:54 pm at 10:54 pm

    የፉክክር ደጃፍ ሳይዘጋ ቀርቶ
    አውሬውም ሌባውም ይገባል ተዝናንቶ
    ምን አገባኝ ያለው የቤቱ ባለቤት
    ‘ጠጋ በል‘ ተብሎ ይወጣል በመስኮት

    Reply
  8. inkopa says

    October 22, 2012 07:29 pm at 7:29 pm

    “ምን አገባኝ” ብለው
    የዘጉበትን ቤት
    ያገኙታል ኋላ
    ያገባው ገብቶበት!

    Reply
  9. በለው ! says

    December 30, 2012 06:08 pm at 6:08 pm

    እኔ ምን አገባኝ ?
    “እኔ ምን ቸገረኝ
    ፀሐይ ብትወጣ ባትወጣ
    ታበራልኛለች የ—መላጣ”
    በሀገር ብቻ አደለም ሲቀለድ በፀሐይ
    ሁሉን በእየፊናው ችላ ማለቱን ሳይ
    ተጠያቂው ማነው? እየተብከነከንኩ
    ስሜቴ ቢነካም ኮራሁ ንፁህ እንደሆንኩ
    ውጪ ወጣሁና አልኩ ምን አስገባኝ
    ፈገግ አልኩ እጄን ኪሴ ከተትኩ
    ለሀገሬ መታረድ ቢላዋ አልሳልኩኝ
    ኑረዲን ዒሳ አንድ ዜጋ ነው አልኩኝ !!
    ^^^^^^^^^^^^^^^^^
    በለው! ከሀገረ ካናዳ በቸር ይግጠመን

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule