• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ

January 16, 2023 08:50 am by Editor Leave a Comment

በአዲስ አበባ ፖሊስ እና በደንብ ማስከበር ባለስልጣን ቅንጅት በተከናወነ ኦፕሬሽን በተለያዩ ክፍለ ከተሞች ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎች እና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለፀ፡፡

ሺሻ የማስጨስ እና ጫት የማስቃም አዋኪ ድርጊቶችን ለመከላከል ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት እየሰራ የሚገኘው የአዲስ አበባ ፖሊስ ከህዝብ በደረሰው ጥቆማ እና በተለያየ መልኩ ባደረገው ጥናት መነሻነት በየካ፣ በቦሌ እና በቂርቆስ ክፍለ ከተሞች ሺሻ በሚጨስባቸው ሆቴሎች እና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ ከደንብ ማስከበር ባለስልጣን ጋር በመቀናጀት በተከናወነ የኦፕሬሽን ስራ እርምጃ ተወስዷል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ እንደገለፀው በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5፣ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 እንዲሁም በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 እና ወረዳ 3 በተለያዩ አካባቢዎች በአጠቃላይ በ24 ሆቴሎች እና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ ጥር 7 ቀን 2015 ዓ/ም ከምሽት ጀምሮ ቁጥጥር የተደረገ ሲሆን ከእነዚህ መካከል 8ቱ ሺሻ ሲያስጨሱ ተገኝተዋል፡፡

293 የሺሻ ዕቃዎች ከእነዚሁ ቤቶች ውስጥ የተያዙ ሲሆን አዋኪ ድርጊቱን ሲፈፅሙ እና ሲያስፈፅሙ የተገኙ 118 ግለሰቦችም በቁጥጥር ስር ውለው በንግድ ቤቶቹ ላይ እርምጃ መወሰዱን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

በቦሌ እና በቂርቆስ ክፍለ ከተሞች በተከናወነው የኦፕሬሽን በሁለቱ ክፍለ ከተሞች ፍተሻ ካደረጉባቸው 23 ሆቴሎች እና የምሽት ጭፈራ ቤቶች መካከል በ7ቱ ላይ ሺሻ ሲጨስባቸው እንደተገኙ ተናግረዋል።

ከእነዚህ 7 ቤቶች ውስጥ 207 የሺሻ ማጨሻ ዕቃዎች እና በህገ ወጥ ተግባሩ ላይ ተሳትፎ አላቸው የተባሉ 61 ግለሰቦች ተይዘው ጉዳያቸው በህግ አግባብ እየታየ እንደሚገኝ ምክትል ኢንስፔክተር አባይ ባህሩ ገልፀዋል፡፡

በቂርቆስ እና ቦሌ ክፍለ ከተሞች እርምጃ የተወሰደባቸው፤

1. ሪቮ አዲስ ላወንጅ :- 87 የሺሻ ዕቃና በድርጊቱ ተሳታፊ 200 ወጣቶች

2. አቤም ሆቴል 22 የሺሻ ዕቃና 8 ወጣት

3. ናሽናል ሆቴል 16 የሺሻ ዕቃና 67 ወጣቶች

4. ሞሲሳ ሆቴል 7 የሺሻ እቃ

በቦሌ ክ/ከተማ

5.ቀነኒሳ ሆቴል 35 የሺሻ እቃ

6.ዘባንክ ላውንጅ 28 የሺሻ እቃ

በተመሳሳይ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 መገናኛ አካባቢ በሚገኝ አንድ ሆቴል ላይ በተደረገ ፍተሻ 86 የሺሻ ማጨሻ ዕቃዎች እና በአዋኪ ድርጊቱ ላይ ተሳትፈው የተገኙ 57 ግለሰቦች እንደተያዙ የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሃላፊ ኮማንደር አስፋው የሺዳኜ ተናግረዋል፡፡

በየካ ክፍለ ከተማ እርምጃ የተወሰደበት፤

7.ቤልቪው ሆቴል 86 የሺሻ ዕቃ እና 54 ሠው ነው።

በህጋዊነት ሽፋን ህገ ወጥ ተግባር እንዲፈፀም በመፍቀድ በከተማችን ለሚከናወነው የፀጥታ ስራ እንቅፋት የሚሆኑ አንዳንድ ሆቴሎች፣ ባርና ሬስቶራንቶች ፣ የምሽት ጭፈራ ቤቶች እና መሰል የንግድ ተቋማት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ቀጣይነት እንዳለው የጠቀሰው የአዲስ አበባ ፖሊስ፤ ህብረተሰቡ መረጃ እና ጥቆማ በመስጠት ትብብሩን እንዲያጠናክር ጥሪውን አቅርቧል፡፡ (ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8፤ አዲስ ሚዲያ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Social Tagged With: Ethiopia Night Clubs, operation dismantle tplf, Revo Addis, shisha ethiopia

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule