• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ

January 16, 2023 08:50 am by Editor Leave a Comment

በአዲስ አበባ ፖሊስ እና በደንብ ማስከበር ባለስልጣን ቅንጅት በተከናወነ ኦፕሬሽን በተለያዩ ክፍለ ከተሞች ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎች እና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለፀ፡፡

ሺሻ የማስጨስ እና ጫት የማስቃም አዋኪ ድርጊቶችን ለመከላከል ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት እየሰራ የሚገኘው የአዲስ አበባ ፖሊስ ከህዝብ በደረሰው ጥቆማ እና በተለያየ መልኩ ባደረገው ጥናት መነሻነት በየካ፣ በቦሌ እና በቂርቆስ ክፍለ ከተሞች ሺሻ በሚጨስባቸው ሆቴሎች እና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ ከደንብ ማስከበር ባለስልጣን ጋር በመቀናጀት በተከናወነ የኦፕሬሽን ስራ እርምጃ ተወስዷል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ እንደገለፀው በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5፣ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 እንዲሁም በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 እና ወረዳ 3 በተለያዩ አካባቢዎች በአጠቃላይ በ24 ሆቴሎች እና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ ጥር 7 ቀን 2015 ዓ/ም ከምሽት ጀምሮ ቁጥጥር የተደረገ ሲሆን ከእነዚህ መካከል 8ቱ ሺሻ ሲያስጨሱ ተገኝተዋል፡፡

293 የሺሻ ዕቃዎች ከእነዚሁ ቤቶች ውስጥ የተያዙ ሲሆን አዋኪ ድርጊቱን ሲፈፅሙ እና ሲያስፈፅሙ የተገኙ 118 ግለሰቦችም በቁጥጥር ስር ውለው በንግድ ቤቶቹ ላይ እርምጃ መወሰዱን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

በቦሌ እና በቂርቆስ ክፍለ ከተሞች በተከናወነው የኦፕሬሽን በሁለቱ ክፍለ ከተሞች ፍተሻ ካደረጉባቸው 23 ሆቴሎች እና የምሽት ጭፈራ ቤቶች መካከል በ7ቱ ላይ ሺሻ ሲጨስባቸው እንደተገኙ ተናግረዋል።

ከእነዚህ 7 ቤቶች ውስጥ 207 የሺሻ ማጨሻ ዕቃዎች እና በህገ ወጥ ተግባሩ ላይ ተሳትፎ አላቸው የተባሉ 61 ግለሰቦች ተይዘው ጉዳያቸው በህግ አግባብ እየታየ እንደሚገኝ ምክትል ኢንስፔክተር አባይ ባህሩ ገልፀዋል፡፡

በቂርቆስ እና ቦሌ ክፍለ ከተሞች እርምጃ የተወሰደባቸው፤

1. ሪቮ አዲስ ላወንጅ :- 87 የሺሻ ዕቃና በድርጊቱ ተሳታፊ 200 ወጣቶች

2. አቤም ሆቴል 22 የሺሻ ዕቃና 8 ወጣት

3. ናሽናል ሆቴል 16 የሺሻ ዕቃና 67 ወጣቶች

4. ሞሲሳ ሆቴል 7 የሺሻ እቃ

በቦሌ ክ/ከተማ

5.ቀነኒሳ ሆቴል 35 የሺሻ እቃ

6.ዘባንክ ላውንጅ 28 የሺሻ እቃ

በተመሳሳይ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 መገናኛ አካባቢ በሚገኝ አንድ ሆቴል ላይ በተደረገ ፍተሻ 86 የሺሻ ማጨሻ ዕቃዎች እና በአዋኪ ድርጊቱ ላይ ተሳትፈው የተገኙ 57 ግለሰቦች እንደተያዙ የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሃላፊ ኮማንደር አስፋው የሺዳኜ ተናግረዋል፡፡

በየካ ክፍለ ከተማ እርምጃ የተወሰደበት፤

7.ቤልቪው ሆቴል 86 የሺሻ ዕቃ እና 54 ሠው ነው።

በህጋዊነት ሽፋን ህገ ወጥ ተግባር እንዲፈፀም በመፍቀድ በከተማችን ለሚከናወነው የፀጥታ ስራ እንቅፋት የሚሆኑ አንዳንድ ሆቴሎች፣ ባርና ሬስቶራንቶች ፣ የምሽት ጭፈራ ቤቶች እና መሰል የንግድ ተቋማት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ቀጣይነት እንዳለው የጠቀሰው የአዲስ አበባ ፖሊስ፤ ህብረተሰቡ መረጃ እና ጥቆማ በመስጠት ትብብሩን እንዲያጠናክር ጥሪውን አቅርቧል፡፡ (ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8፤ አዲስ ሚዲያ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Social Tagged With: Ethiopia Night Clubs, operation dismantle tplf, Revo Addis, shisha ethiopia

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule