• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የፌዴሬሽን ም/ቤት ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ ስለ ህወሃት ማብራሪያ ሰጠ

October 13, 2020 12:56 am by Editor 2 Comments

የፌዴሬሽን ምክር ቤት ህወኃትን በተመለከተ ባሳለፈው ውሳኔዎች ዙሪያ ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ ማብራሪያ ሰጥቷል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባዘጋጀው በዚህ መድረክ በአዲስ አበባ የሚገኙ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች እና የቆንስላ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት የትግራይ ክልል ምርጫን በሚመለከት ባሳለፈው ውሳኔ ዙሪያ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገ መንግሥት ትርጉምና የማንነት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጸሐፊ ወርቁ አዳሙ ማብራሪያ አቅርበዋል።

በማብራሪያው በ2012ዓ.ም በኢትዮጵያ ሊደረግ የነበረው ሀገራዊ ምርጫ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም ምክር ቤቱ በሕገ መንግሥት ትርጉም ተመሥርቶ ውሳኔ ማሳለፉ ተነስቷል፤ የትግራይ ክልልን የሚመራው ፓርቲ ህወሀት ውሳኔውን ወደ ጎን በመተው ኢ-ሕገ መንግሥታዊ በሆነ መንገድ ምርጫ በማድረግ ወደ መንግሥት ምሥረታ መግባቱም ተጠቅሷል።

ህወሀት ከዚህ ድርጊቱ እንዲቆጠብ ጥረት ቢደረግም ፈቃደኛ ባለመሆኑ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ያሳለፋቸውን ውሳኔዎችን አቶ ወርቁ ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ አብራርተዋል።

ህወሀት እየሄደበት ካለው ኢ- ሕገ መንግሥታዊ ጉዞው እንዲታረም በፌዴራል መንግሥት በኩል ሁሉንም ዓይነት ውይይቶችን እና ሕጋዊ መንገዶችን ተከትሎ መጠየቁን ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ ማብራሪያ ተሰጥቷል። ህወሀት የሰላም እና ሕጋዊነት የተላበሱ ውይይቶችን ለመቀበል ፍቃደኛ አለመሆኑም ተጠቅሷል።

ሀገራዊ ምርጫውን በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ ለማካሄድ ሁሉም ዓይነት ዝግጅቶች እየተደረጉ እንደነበር በሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል የሕዝብና ዓለማቀፍ ግንኙነት ኃላፊ ቢቄላ ሁዴሳ (ዶክተር) አስረድተዋል።

በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት የምርጫ ቦርድ ምርጫውን ማካሄድ እንደማይችል በማሳወቁ መንግሥት የወሰደውን የሕገ መንግሥት ትርጉም መፍትሔም አብራርተዋል። ምርጫው ከ9 ወር እስከ 1 ዓመት እንዲራዘም ውሳኔ ያሳለፈ መሆኑ እየታወቀ በትግራይ ክልል መንግሥት በኩል ግን ኢ-ሕገ መንግሥታዊ የሆነ ምርጫ መካሄዱን ዶ/ር ቢቂላ ገልጸዋል።

‘‘የሀገሪቱ ሕገ ሁሉ የበላይ ሕግ የሆነው ሕገ መንግሥት በሁሉም ክልሎች እኩል መከበር አለበት። ሁለቱ ምክር ቤቶች የሚያሳልፉት ውሳኔ ገዥ መሆኑ እየታወቀ ‘የትግራይ ክልል መንግሥት ያካሄደው ምርጫ ተቀባይነት የሌለው፣ የማይፀና እና ኢ-ሕገ-መንግሥታዊ ነው’ በሚል በትግራይ በኩል የተካሄደው ምርጫ ተቀባይነት የለውም’’ በሚል ውሳኔ መተላለፉን የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ እንዲረዳም ዶ/ር ቢቂላ አብራርተዋል።

የልማት ሥራዎችን በመንግሥትም ሆነ በተለያዩ ለጋሽ አካላት ማከናወን ያልተቋረጠና የሚቀጥል መሆኑንም ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ አስታውቀዋል። (ጋሻው ፋንታሁን፤ አብመድ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: tigray tplf election, tplf, tplf fake election

Reader Interactions

Comments

  1. GI Haile says

    October 13, 2020 12:22 pm at 12:22 pm

    TPLF Leaders are not Law abiding group. They are not representing Tugray people and Tigray people are hostages by TPLF. Tigray people they don’t have democratic rights and they were under Dictatorships for 30 Years. Tigray people silenced by TPLF they have no choices.

    Reply
  2. Mr Frank Talk says

    October 14, 2020 06:03 am at 6:03 am

    TBLF is adamant to hear the very people it is claiming to serve. Worse still, it thinks the people can be human shields and save it when the final whistle is blown by the Federal Government. This will never happen as it never shared what it looted for 27 years from the country with them.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule