• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የፌዴሬሽን ም/ቤት ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ ስለ ህወሃት ማብራሪያ ሰጠ

October 13, 2020 12:56 am by Editor 2 Comments

የፌዴሬሽን ምክር ቤት ህወኃትን በተመለከተ ባሳለፈው ውሳኔዎች ዙሪያ ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ ማብራሪያ ሰጥቷል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባዘጋጀው በዚህ መድረክ በአዲስ አበባ የሚገኙ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች እና የቆንስላ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት የትግራይ ክልል ምርጫን በሚመለከት ባሳለፈው ውሳኔ ዙሪያ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገ መንግሥት ትርጉምና የማንነት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጸሐፊ ወርቁ አዳሙ ማብራሪያ አቅርበዋል።

በማብራሪያው በ2012ዓ.ም በኢትዮጵያ ሊደረግ የነበረው ሀገራዊ ምርጫ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም ምክር ቤቱ በሕገ መንግሥት ትርጉም ተመሥርቶ ውሳኔ ማሳለፉ ተነስቷል፤ የትግራይ ክልልን የሚመራው ፓርቲ ህወሀት ውሳኔውን ወደ ጎን በመተው ኢ-ሕገ መንግሥታዊ በሆነ መንገድ ምርጫ በማድረግ ወደ መንግሥት ምሥረታ መግባቱም ተጠቅሷል።

ህወሀት ከዚህ ድርጊቱ እንዲቆጠብ ጥረት ቢደረግም ፈቃደኛ ባለመሆኑ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ያሳለፋቸውን ውሳኔዎችን አቶ ወርቁ ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ አብራርተዋል።

ህወሀት እየሄደበት ካለው ኢ- ሕገ መንግሥታዊ ጉዞው እንዲታረም በፌዴራል መንግሥት በኩል ሁሉንም ዓይነት ውይይቶችን እና ሕጋዊ መንገዶችን ተከትሎ መጠየቁን ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ ማብራሪያ ተሰጥቷል። ህወሀት የሰላም እና ሕጋዊነት የተላበሱ ውይይቶችን ለመቀበል ፍቃደኛ አለመሆኑም ተጠቅሷል።

ሀገራዊ ምርጫውን በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ ለማካሄድ ሁሉም ዓይነት ዝግጅቶች እየተደረጉ እንደነበር በሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል የሕዝብና ዓለማቀፍ ግንኙነት ኃላፊ ቢቄላ ሁዴሳ (ዶክተር) አስረድተዋል።

በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት የምርጫ ቦርድ ምርጫውን ማካሄድ እንደማይችል በማሳወቁ መንግሥት የወሰደውን የሕገ መንግሥት ትርጉም መፍትሔም አብራርተዋል። ምርጫው ከ9 ወር እስከ 1 ዓመት እንዲራዘም ውሳኔ ያሳለፈ መሆኑ እየታወቀ በትግራይ ክልል መንግሥት በኩል ግን ኢ-ሕገ መንግሥታዊ የሆነ ምርጫ መካሄዱን ዶ/ር ቢቂላ ገልጸዋል።

‘‘የሀገሪቱ ሕገ ሁሉ የበላይ ሕግ የሆነው ሕገ መንግሥት በሁሉም ክልሎች እኩል መከበር አለበት። ሁለቱ ምክር ቤቶች የሚያሳልፉት ውሳኔ ገዥ መሆኑ እየታወቀ ‘የትግራይ ክልል መንግሥት ያካሄደው ምርጫ ተቀባይነት የሌለው፣ የማይፀና እና ኢ-ሕገ-መንግሥታዊ ነው’ በሚል በትግራይ በኩል የተካሄደው ምርጫ ተቀባይነት የለውም’’ በሚል ውሳኔ መተላለፉን የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ እንዲረዳም ዶ/ር ቢቂላ አብራርተዋል።

የልማት ሥራዎችን በመንግሥትም ሆነ በተለያዩ ለጋሽ አካላት ማከናወን ያልተቋረጠና የሚቀጥል መሆኑንም ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ አስታውቀዋል። (ጋሻው ፋንታሁን፤ አብመድ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: tigray tplf election, tplf, tplf fake election

Reader Interactions

Comments

  1. GI Haile says

    October 13, 2020 12:22 pm at 12:22 pm

    TPLF Leaders are not Law abiding group. They are not representing Tugray people and Tigray people are hostages by TPLF. Tigray people they don’t have democratic rights and they were under Dictatorships for 30 Years. Tigray people silenced by TPLF they have no choices.

    Reply
  2. Mr Frank Talk says

    October 14, 2020 06:03 am at 6:03 am

    TBLF is adamant to hear the very people it is claiming to serve. Worse still, it thinks the people can be human shields and save it when the final whistle is blown by the Federal Government. This will never happen as it never shared what it looted for 27 years from the country with them.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule