• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የፌዴሬሽን ም/ቤት ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ ስለ ህወሃት ማብራሪያ ሰጠ

October 13, 2020 12:56 am by Editor 2 Comments

የፌዴሬሽን ምክር ቤት ህወኃትን በተመለከተ ባሳለፈው ውሳኔዎች ዙሪያ ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ ማብራሪያ ሰጥቷል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባዘጋጀው በዚህ መድረክ በአዲስ አበባ የሚገኙ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች እና የቆንስላ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት የትግራይ ክልል ምርጫን በሚመለከት ባሳለፈው ውሳኔ ዙሪያ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገ መንግሥት ትርጉምና የማንነት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጸሐፊ ወርቁ አዳሙ ማብራሪያ አቅርበዋል።

በማብራሪያው በ2012ዓ.ም በኢትዮጵያ ሊደረግ የነበረው ሀገራዊ ምርጫ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም ምክር ቤቱ በሕገ መንግሥት ትርጉም ተመሥርቶ ውሳኔ ማሳለፉ ተነስቷል፤ የትግራይ ክልልን የሚመራው ፓርቲ ህወሀት ውሳኔውን ወደ ጎን በመተው ኢ-ሕገ መንግሥታዊ በሆነ መንገድ ምርጫ በማድረግ ወደ መንግሥት ምሥረታ መግባቱም ተጠቅሷል።

ህወሀት ከዚህ ድርጊቱ እንዲቆጠብ ጥረት ቢደረግም ፈቃደኛ ባለመሆኑ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ያሳለፋቸውን ውሳኔዎችን አቶ ወርቁ ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ አብራርተዋል።

ህወሀት እየሄደበት ካለው ኢ- ሕገ መንግሥታዊ ጉዞው እንዲታረም በፌዴራል መንግሥት በኩል ሁሉንም ዓይነት ውይይቶችን እና ሕጋዊ መንገዶችን ተከትሎ መጠየቁን ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ ማብራሪያ ተሰጥቷል። ህወሀት የሰላም እና ሕጋዊነት የተላበሱ ውይይቶችን ለመቀበል ፍቃደኛ አለመሆኑም ተጠቅሷል።

ሀገራዊ ምርጫውን በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ ለማካሄድ ሁሉም ዓይነት ዝግጅቶች እየተደረጉ እንደነበር በሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል የሕዝብና ዓለማቀፍ ግንኙነት ኃላፊ ቢቄላ ሁዴሳ (ዶክተር) አስረድተዋል።

በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት የምርጫ ቦርድ ምርጫውን ማካሄድ እንደማይችል በማሳወቁ መንግሥት የወሰደውን የሕገ መንግሥት ትርጉም መፍትሔም አብራርተዋል። ምርጫው ከ9 ወር እስከ 1 ዓመት እንዲራዘም ውሳኔ ያሳለፈ መሆኑ እየታወቀ በትግራይ ክልል መንግሥት በኩል ግን ኢ-ሕገ መንግሥታዊ የሆነ ምርጫ መካሄዱን ዶ/ር ቢቂላ ገልጸዋል።

‘‘የሀገሪቱ ሕገ ሁሉ የበላይ ሕግ የሆነው ሕገ መንግሥት በሁሉም ክልሎች እኩል መከበር አለበት። ሁለቱ ምክር ቤቶች የሚያሳልፉት ውሳኔ ገዥ መሆኑ እየታወቀ ‘የትግራይ ክልል መንግሥት ያካሄደው ምርጫ ተቀባይነት የሌለው፣ የማይፀና እና ኢ-ሕገ-መንግሥታዊ ነው’ በሚል በትግራይ በኩል የተካሄደው ምርጫ ተቀባይነት የለውም’’ በሚል ውሳኔ መተላለፉን የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ እንዲረዳም ዶ/ር ቢቂላ አብራርተዋል።

የልማት ሥራዎችን በመንግሥትም ሆነ በተለያዩ ለጋሽ አካላት ማከናወን ያልተቋረጠና የሚቀጥል መሆኑንም ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ አስታውቀዋል። (ጋሻው ፋንታሁን፤ አብመድ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: tigray tplf election, tplf, tplf fake election

Reader Interactions

Comments

  1. GI Haile says

    October 13, 2020 12:22 pm at 12:22 pm

    TPLF Leaders are not Law abiding group. They are not representing Tugray people and Tigray people are hostages by TPLF. Tigray people they don’t have democratic rights and they were under Dictatorships for 30 Years. Tigray people silenced by TPLF they have no choices.

    Reply
  2. Mr Frank Talk says

    October 14, 2020 06:03 am at 6:03 am

    TBLF is adamant to hear the very people it is claiming to serve. Worse still, it thinks the people can be human shields and save it when the final whistle is blown by the Federal Government. This will never happen as it never shared what it looted for 27 years from the country with them.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule