• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የፌዴሬሽን ም/ቤት ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ ስለ ህወሃት ማብራሪያ ሰጠ

October 13, 2020 12:56 am by Editor 2 Comments

የፌዴሬሽን ምክር ቤት ህወኃትን በተመለከተ ባሳለፈው ውሳኔዎች ዙሪያ ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ ማብራሪያ ሰጥቷል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባዘጋጀው በዚህ መድረክ በአዲስ አበባ የሚገኙ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች እና የቆንስላ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት የትግራይ ክልል ምርጫን በሚመለከት ባሳለፈው ውሳኔ ዙሪያ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገ መንግሥት ትርጉምና የማንነት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጸሐፊ ወርቁ አዳሙ ማብራሪያ አቅርበዋል።

በማብራሪያው በ2012ዓ.ም በኢትዮጵያ ሊደረግ የነበረው ሀገራዊ ምርጫ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም ምክር ቤቱ በሕገ መንግሥት ትርጉም ተመሥርቶ ውሳኔ ማሳለፉ ተነስቷል፤ የትግራይ ክልልን የሚመራው ፓርቲ ህወሀት ውሳኔውን ወደ ጎን በመተው ኢ-ሕገ መንግሥታዊ በሆነ መንገድ ምርጫ በማድረግ ወደ መንግሥት ምሥረታ መግባቱም ተጠቅሷል።

ህወሀት ከዚህ ድርጊቱ እንዲቆጠብ ጥረት ቢደረግም ፈቃደኛ ባለመሆኑ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ያሳለፋቸውን ውሳኔዎችን አቶ ወርቁ ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ አብራርተዋል።

ህወሀት እየሄደበት ካለው ኢ- ሕገ መንግሥታዊ ጉዞው እንዲታረም በፌዴራል መንግሥት በኩል ሁሉንም ዓይነት ውይይቶችን እና ሕጋዊ መንገዶችን ተከትሎ መጠየቁን ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ ማብራሪያ ተሰጥቷል። ህወሀት የሰላም እና ሕጋዊነት የተላበሱ ውይይቶችን ለመቀበል ፍቃደኛ አለመሆኑም ተጠቅሷል።

ሀገራዊ ምርጫውን በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ ለማካሄድ ሁሉም ዓይነት ዝግጅቶች እየተደረጉ እንደነበር በሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል የሕዝብና ዓለማቀፍ ግንኙነት ኃላፊ ቢቄላ ሁዴሳ (ዶክተር) አስረድተዋል።

በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት የምርጫ ቦርድ ምርጫውን ማካሄድ እንደማይችል በማሳወቁ መንግሥት የወሰደውን የሕገ መንግሥት ትርጉም መፍትሔም አብራርተዋል። ምርጫው ከ9 ወር እስከ 1 ዓመት እንዲራዘም ውሳኔ ያሳለፈ መሆኑ እየታወቀ በትግራይ ክልል መንግሥት በኩል ግን ኢ-ሕገ መንግሥታዊ የሆነ ምርጫ መካሄዱን ዶ/ር ቢቂላ ገልጸዋል።

‘‘የሀገሪቱ ሕገ ሁሉ የበላይ ሕግ የሆነው ሕገ መንግሥት በሁሉም ክልሎች እኩል መከበር አለበት። ሁለቱ ምክር ቤቶች የሚያሳልፉት ውሳኔ ገዥ መሆኑ እየታወቀ ‘የትግራይ ክልል መንግሥት ያካሄደው ምርጫ ተቀባይነት የሌለው፣ የማይፀና እና ኢ-ሕገ-መንግሥታዊ ነው’ በሚል በትግራይ በኩል የተካሄደው ምርጫ ተቀባይነት የለውም’’ በሚል ውሳኔ መተላለፉን የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ እንዲረዳም ዶ/ር ቢቂላ አብራርተዋል።

የልማት ሥራዎችን በመንግሥትም ሆነ በተለያዩ ለጋሽ አካላት ማከናወን ያልተቋረጠና የሚቀጥል መሆኑንም ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ አስታውቀዋል። (ጋሻው ፋንታሁን፤ አብመድ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Left Column, News Tagged With: tigray tplf election, tplf, tplf fake election

Reader Interactions

Comments

  1. GI Haile says

    October 13, 2020 12:22 pm at 12:22 pm

    TPLF Leaders are not Law abiding group. They are not representing Tugray people and Tigray people are hostages by TPLF. Tigray people they don’t have democratic rights and they were under Dictatorships for 30 Years. Tigray people silenced by TPLF they have no choices.

    Reply
  2. Mr Frank Talk says

    October 14, 2020 06:03 am at 6:03 am

    TBLF is adamant to hear the very people it is claiming to serve. Worse still, it thinks the people can be human shields and save it when the final whistle is blown by the Federal Government. This will never happen as it never shared what it looted for 27 years from the country with them.

    Reply

Leave a Reply to GI Haile Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule