• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢትዮጵያ 16.6 ቢሊዮን ዶላር ከዓለም ባንክ አገኘች

July 30, 2024 07:39 pm by Editor Leave a Comment

ለሁለት ዓመታት የተደረገው ድርድር ያስገኘው ውጤት ነው

የዓለም ባንክ በዛሬው ዕለት (ማክሰኞ) “የኢትዮጵያ የመጀመሪያው ዘላቂና ሁሉን ዓቀፍ የልማት ፖሊሲ ዘመቻ” (Ethiopia First Sustainable and Inclusive Growth Development Policy Operation) በሚል ለሚጠራው የልማት ፖሊሲ ማስፈጸሚያ የሚሆን ድጋፍና ብድር መፍቀዱን ይፋ አድርጓል።በወጣው መግለጫ መሠረት ባንኩ የሚያደርገው ድጋፍ ሦስት ዓላማዎችን ያካተተ ነው፤

(ሀ) ለመዋቅር መልሶ ማዋቀርና ንግድን ለማሳለጥ

(ለ) በጀትን በተመለከተ ዘላቂነትንና ግልጽነትን ለማስፋፋት እና

(ሐ) የአካባቢ ጥበቃን እና ማኅበራዊ አይበገሬነትን ለማበረታታት እንደሆነ ተገልጾዋል።

በተለምዶ የዓለም ባንክ የሚባለው ቡድን ሲሆን በሥሩም የተለያዩ ድርጅቶች አሉት፤ ብድርም ሆነ ሥጦታ ሲፈቀድ የዓለም ባንክ ፈቀደ ተብሎ ቢጠቀስም ዋናውን ሚና የሚጫወቱት ገንዘቡን የሚፈቅዱት ድርጅቶች ናቸው።

ለኢትዮጵያ ከተፈቀደው ገንዘብ ጋር በተያያዘ ዓለም አቀፍ የልማት ማኅበር (International Development Association (IDA))፤ ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ትብብር (The International Finance Corporation (IFC)) እና የባለብዙ ወገን የኢንቨስትመንት ዋስትና ኤጀንሲ (Multilateral Investment Guarantee Agency (MIGA)) የሚባሉት ሦስት ድርጅቶች ተሳትፈዋል። ለኢትዮጵያ ከተፈቀደው ገንዘብ በጣም አብላጫውን የሰጠው IDA ነው።

ዛሬ ከዓለም አቀፉ የልማት ማኅበር (IDA) የተፈቀደው ገንዘብ፤

  • ቀጥተኛ ስጦታ (grant) 1 ቢሊዮን ዶላር፤
  • የስምምነት ዱቤ (concessional credit) 500 ሚሊዮን ዶላር፤ ይህ ከገበያው ዋጋ በታች በሆነ ወለድ የሚከፈል ወይም በዜሮ ወለድ የሚከፈል ብድር ነው
  • ማኅበሩ (IDA) ለኢትዮጵያ እሰጣለሁ ብሎ ቃል የገባው 15.5 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን
    • ከዚህ ውስጥ 7 ቢሊዮን ዶላር ኢትዮጵያ ለመረከብ እስከተዘጋጀች ማኅበሩ ለመስጠት እጁ ላይ ያለ ገንዘብ ነው።  
  • ማኅበሩ በቀጣይ ሦስት ዓመታት ወደ 6 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የኢኮኖሚ ተሐድሶውን ለመደገፍ የሚረዳ ለበጀት ድጎማ የሚሆን ተጨማሪ ቃል ሊገባ ይችላል

ዓለም አቀፉ የልማት ማኅበር (IDA) የሚፈቅደው ገንዘብ ለታዳጊ አገሮች የሚሰጥ ሲሆን ዋናው ባህርዩ ከገበያው ዋጋ በታች የወለድ መጠን ወይም በዜሮ የወለድ መጠን ማበደር ሲሆን ከሚሰጠው ብድር ግማሽ ያህሉ በሥጦታ መልክ የሚለገስ ነው። ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ በየዓመቱ ከሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ የስምምነት ዱቤ ከማኅበሩ የምታገኝ ሲሆን ግማሽ ያህሉ ሥጦታ ነው።  

ዛሬ ይፋ የሆነው ሌላው የገንዘብ ድጋፍ ከሁለት የባንኩ ድርጅቶች የተገኘ ነው፤

  • ከዓለም አቀፉ የኢንቨስትመንት ትብብር (The International Finance Corporation (IFC)) 320 ሚሊዮን ዶላር ነው። ይህ ሌላው የዓለም ባንክ ቡድን አባል ሲሆን ዋናው ትኩረቱ በታዳጊ አገራት ዜጎችን ሕይወት ለማሻሻል በግሉ ክፍለ ኢኮኖሚ ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሠራ ነው።
    • ይህ መጠን በቀጣይ ዓመታት እስከ 2.1 ቢሊዮን ዶላር ሊያድግ የሚችል ነው።
  • የባለብዙ ወገን ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ (Multilateral Investment Guarantee Agency (MIGA)) ከሚባለው 1.15 ቢሊዮን ዶላር፤
    • ይህ ከዓለም ባንክ ቡድኖች አንዱ ሲሆን በታዳጊ አገራት ውስጥ በሚፈጸም ከኢንቨስትመንት ጋር በተያያዘ አበዳሪዎች ወይም ኢንቨስተሮች ሊገጥማቸው ለሚችል የፖለቲካ ኪሣራ የመድኅን ዋስትና የሚሰጥ ነው።

በአጠቃላይ ዛሬ ይፋ የሆነው የዓለምአቀፉ ባንክ የገንዘብ ድጎማ በቀጣይ ሦስት ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያ የተፈቀደላት ፓኬጅ 16.6 ቢሊዮን ዶላር እንደሆነ ገልጾዋል።

ባንኩ ኢትዮጵያ መካከለኛ ገቢ ያላቸው አገራት መካከል ለመሆን ያላትን ትልም ግምት ውስጥ በማስገባት የኢኮኖሚ ሪፎርም ወይም ማሻሻያና የበጀት ድጋፍ በማድረግ ዕገዛውን እንደሚቀጥል ዛሬ የወጣው የባንኩ ጋዜጣዊ መግለጫ ያስረዳል።

ይህንን ፈር ቀዳጅ የሆነውን የዓለም ባንክ ውሳኔ ተከትሎ በቀጣይ ሌሎች አበዳሪ ተቋማት ተጨማሪ የገንዘብ ድጎማዎች እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Politics Tagged With: 16.6 billion dollar package by world bank, Ethiopia First Sustainable and Inclusive Growth Development Policy Operation, world bank

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule