• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢትዮጵያ 16.6 ቢሊዮን ዶላር ከዓለም ባንክ አገኘች

July 30, 2024 07:39 pm by Editor Leave a Comment

ለሁለት ዓመታት የተደረገው ድርድር ያስገኘው ውጤት ነው

የዓለም ባንክ በዛሬው ዕለት (ማክሰኞ) “የኢትዮጵያ የመጀመሪያው ዘላቂና ሁሉን ዓቀፍ የልማት ፖሊሲ ዘመቻ” (Ethiopia First Sustainable and Inclusive Growth Development Policy Operation) በሚል ለሚጠራው የልማት ፖሊሲ ማስፈጸሚያ የሚሆን ድጋፍና ብድር መፍቀዱን ይፋ አድርጓል።በወጣው መግለጫ መሠረት ባንኩ የሚያደርገው ድጋፍ ሦስት ዓላማዎችን ያካተተ ነው፤

(ሀ) ለመዋቅር መልሶ ማዋቀርና ንግድን ለማሳለጥ

(ለ) በጀትን በተመለከተ ዘላቂነትንና ግልጽነትን ለማስፋፋት እና

(ሐ) የአካባቢ ጥበቃን እና ማኅበራዊ አይበገሬነትን ለማበረታታት እንደሆነ ተገልጾዋል።

በተለምዶ የዓለም ባንክ የሚባለው ቡድን ሲሆን በሥሩም የተለያዩ ድርጅቶች አሉት፤ ብድርም ሆነ ሥጦታ ሲፈቀድ የዓለም ባንክ ፈቀደ ተብሎ ቢጠቀስም ዋናውን ሚና የሚጫወቱት ገንዘቡን የሚፈቅዱት ድርጅቶች ናቸው።

ለኢትዮጵያ ከተፈቀደው ገንዘብ ጋር በተያያዘ ዓለም አቀፍ የልማት ማኅበር (International Development Association (IDA))፤ ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ትብብር (The International Finance Corporation (IFC)) እና የባለብዙ ወገን የኢንቨስትመንት ዋስትና ኤጀንሲ (Multilateral Investment Guarantee Agency (MIGA)) የሚባሉት ሦስት ድርጅቶች ተሳትፈዋል። ለኢትዮጵያ ከተፈቀደው ገንዘብ በጣም አብላጫውን የሰጠው IDA ነው።

ዛሬ ከዓለም አቀፉ የልማት ማኅበር (IDA) የተፈቀደው ገንዘብ፤

  • ቀጥተኛ ስጦታ (grant) 1 ቢሊዮን ዶላር፤
  • የስምምነት ዱቤ (concessional credit) 500 ሚሊዮን ዶላር፤ ይህ ከገበያው ዋጋ በታች በሆነ ወለድ የሚከፈል ወይም በዜሮ ወለድ የሚከፈል ብድር ነው
  • ማኅበሩ (IDA) ለኢትዮጵያ እሰጣለሁ ብሎ ቃል የገባው 15.5 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን
    • ከዚህ ውስጥ 7 ቢሊዮን ዶላር ኢትዮጵያ ለመረከብ እስከተዘጋጀች ማኅበሩ ለመስጠት እጁ ላይ ያለ ገንዘብ ነው።  
  • ማኅበሩ በቀጣይ ሦስት ዓመታት ወደ 6 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የኢኮኖሚ ተሐድሶውን ለመደገፍ የሚረዳ ለበጀት ድጎማ የሚሆን ተጨማሪ ቃል ሊገባ ይችላል

ዓለም አቀፉ የልማት ማኅበር (IDA) የሚፈቅደው ገንዘብ ለታዳጊ አገሮች የሚሰጥ ሲሆን ዋናው ባህርዩ ከገበያው ዋጋ በታች የወለድ መጠን ወይም በዜሮ የወለድ መጠን ማበደር ሲሆን ከሚሰጠው ብድር ግማሽ ያህሉ በሥጦታ መልክ የሚለገስ ነው። ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ በየዓመቱ ከሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ የስምምነት ዱቤ ከማኅበሩ የምታገኝ ሲሆን ግማሽ ያህሉ ሥጦታ ነው።  

ዛሬ ይፋ የሆነው ሌላው የገንዘብ ድጋፍ ከሁለት የባንኩ ድርጅቶች የተገኘ ነው፤

  • ከዓለም አቀፉ የኢንቨስትመንት ትብብር (The International Finance Corporation (IFC)) 320 ሚሊዮን ዶላር ነው። ይህ ሌላው የዓለም ባንክ ቡድን አባል ሲሆን ዋናው ትኩረቱ በታዳጊ አገራት ዜጎችን ሕይወት ለማሻሻል በግሉ ክፍለ ኢኮኖሚ ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሠራ ነው።
    • ይህ መጠን በቀጣይ ዓመታት እስከ 2.1 ቢሊዮን ዶላር ሊያድግ የሚችል ነው።
  • የባለብዙ ወገን ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ (Multilateral Investment Guarantee Agency (MIGA)) ከሚባለው 1.15 ቢሊዮን ዶላር፤
    • ይህ ከዓለም ባንክ ቡድኖች አንዱ ሲሆን በታዳጊ አገራት ውስጥ በሚፈጸም ከኢንቨስትመንት ጋር በተያያዘ አበዳሪዎች ወይም ኢንቨስተሮች ሊገጥማቸው ለሚችል የፖለቲካ ኪሣራ የመድኅን ዋስትና የሚሰጥ ነው።

በአጠቃላይ ዛሬ ይፋ የሆነው የዓለምአቀፉ ባንክ የገንዘብ ድጎማ በቀጣይ ሦስት ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያ የተፈቀደላት ፓኬጅ 16.6 ቢሊዮን ዶላር እንደሆነ ገልጾዋል።

ባንኩ ኢትዮጵያ መካከለኛ ገቢ ያላቸው አገራት መካከል ለመሆን ያላትን ትልም ግምት ውስጥ በማስገባት የኢኮኖሚ ሪፎርም ወይም ማሻሻያና የበጀት ድጋፍ በማድረግ ዕገዛውን እንደሚቀጥል ዛሬ የወጣው የባንኩ ጋዜጣዊ መግለጫ ያስረዳል።

ይህንን ፈር ቀዳጅ የሆነውን የዓለም ባንክ ውሳኔ ተከትሎ በቀጣይ ሌሎች አበዳሪ ተቋማት ተጨማሪ የገንዘብ ድጎማዎች እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Politics Tagged With: 16.6 billion dollar package by world bank, Ethiopia First Sustainable and Inclusive Growth Development Policy Operation, world bank

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule