• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት

August 1, 2023 09:25 am by Editor 1 Comment

አሁናዊ የመከላከያ ሠራዊቱን ያለበትን ሁኔታ በተመለከተ የኢፌዴሪ የመከላከያ ሠራዊት የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት መግለጫ ሰጥቷል።

መግለጫውን የሰጡት የሠራዊቱ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ ኮሎኔል ጌትነት አዳነ፣ መግለጫው በተለያዩ አካላት በሠራዊቱ ላይ እየተናፈሱ ያሉ ብዥታዎችን ለማጥራት የተሰጠ ነው ብለዋል።

ሠራዊቱ ካለፉት ዓመታት በነበረበት ቁመና ላይ እንዳለ የሚያስቡ አካላት ካሉ የቆሙት እነርሱ እንጂ ሠራዊቱ ተራማጅ ነው ያሉት ኮሎኔል ጌትነት፣ ሠራዊቱ ዘርፈ ብዙ ግዳጁን እየተወጣ ነው ብለዋል።

“ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚል አካል ላይ ሠራዊቱ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ ይቀጥላልም ብለዋል።

ሠራዊቱን መቋቋም ያልቻሉ አካላት በሠራዊቱ ላይ ሰፊ የስም ማጥፋት ዘመቻ ላይ ይገኛሉም ነው ያሉት ኮሎኔል ጌትነት።

በተለይ አሁን ላይ በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ አካላት ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በኦሮሚያ ክልል ሸኔ የመደምሰስ ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን አብራርተዋል።

በአማራ ክልል በመሬት ላይ ካለው ግጭት የገዘፈ የሚዲያ ትግል ተከፍቷል ተብሏል በመግለጫው።

ከሰሞኑ በጎንደር የሰሜን ምዕራብ እዝን ዓመታዊ አፈጻጸም ላይ ለመገምገም ወደ ስፍራው እያቀኑ በነበሩ የሠራዊቱ አባላት ላይ ከጩሂት 2 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሲደርሱ ተኩስ  በሠራዊቱ ላይ መከፈቱን ጠቅሰዋል።

የሠራዊቱ አባላትም በመመለስ ላይ ሳለም በቆላድባ አካባቢ በተመሳሳይ ተኩስ ተከፍቷል ነው ያሉት።

ለዚህም ሠራዊቱ ችግሩን በብልሃት ለመፍታት መስራቱንም አስታውሰዋል።

ሐምሌ 23 ቀን 2015 ዓ.ም ከአካባቢው ማህበረሰብ፣ ከወጣቶች እና ከሃገር ሽማግሌዎች ጋር ውይይት ተካሂዶ እንደነበር እና በይቅርታ መዘጋቱን አንስተዋል። (ኢዜአ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: endf, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    August 1, 2023 03:21 pm at 3:21 pm

    እብድ በማያየው ነገር ይስቃል። አንዴ አንድ ጓደኛችን የጥበብ መጀመሪያ ምንድን ነው ተብሎ ተጠየቀ። ትንሽ ካሰበ በህዋላ ትዝ ያለው የእናቱ ቀሚስና መቀነት ነው። ቸኮል ብሎ ቀይ ጥለት አለና ሁላችንም አሳቀን። አሁን በሃበሻ ምድር የሚደረገው ፍልሚያ አላስፈላጊና በውጭና በውስጥ ሃይሎች የፈጠራ ወሬ እየፋመ እየጠፋ ህዝባችን በሰላም እንዳይኖር የሚደረግ የሃገር ጠላቶች የሥራ ውጤት ነው። የሚገርመው የሶሻል ሚዲያም ሆነ የሌላው ወሬ አርከፍካፊ በስማ በለው የሚያወራ፤ አልፎ ተርፎም በፈጠራ የሚደረግ ለጊዜው የሣንቲም ሽራፊ ለመለቃቀም ሆን ተብሎ የሚነዛ ወሬ ነው።
    ሲጀመር ፋኖና መከላከያ ሊፋለሙ የሚገባቸው ሃይሎች አይደሉም። እኔን የሚገርመኝ ሰው ብልጽግና ፓርቲ አባል በመሆኑ መገደሉ፤ ፋኖ በመሆኑ መታሰሩ ወይም መገደሉ ሁሉ የቁልቁለት መንገድ እንጂ በጭራሽ ለህዝባችን ሰላምና ብልጽግናን አያመጣም። በስመ ነጻነት የህዝባችን ሰቆቃ የሚያባብሱ ሁሉ ካለፈው የብሄር ትግል ውጣ ውረድ ትምህርት ያልወሰድ ጅሎች ናቸው። ስንቱን አውድሞ ለጥቂቶች ትርፍ እንደሆነ ዛሬ ላይ የቆሙ መመልከት ይችላሉ። ነጻ እናወጣሃለን ተብሎ በስሙ የተነገደበት ያ ብሄር ዛሬም በሰቆቃ ውስጥ ነው። ትርፍ የለሽ ፓለቲካ ውሃ ወቀጣ ነው። አሁንም በሃገሪቱ ልዪ ልዪ ክፍሎች የሚደረገው ውጊያና ማፈናቀል፤ ግድያና ዝርፊያ ሁሉ ትግል ሳይሆን ሽፍትነት ነው። ህዝብ እያሸበሩ ነጻነት የለም። ህዝብን እያፈናቀሉ አብሮ መኖር አይገኝም። ዛሬ ከጎንህ ያለው ወገንህ በዘሩና በቋንቋው ቤቱ ሲፈርስ፤ ሲዘረፍ፤ ሲፈናቀል እያየህ በሰላም የምታንቀላፋ ነገ ወረፋው ያንተው ይሆናል። የሰው ልጅ ክፋቱ እርከን የለውም። በፈለገው ጊዜ ጤነኛ ነው፤ ጥሩ ሰው ነው የተባለው ጨርቁን ጥሎ ሲሄድ አይተናል።
    ባጭሩ አሁን በጎንደር፤ በወሎ፤ በሽዋና በጎጃም የሚደረገው ግጭትና መንቆራቆስ በፍጥነት ሊገታ ይገባል። ወያኔ ያደረሰው በደል አልበቃ ብሎ ነው አሁን እንደገና ይህ ሁሉ ውድመት የሚደርሰው። እናንተ የወሬ ቱልቱላዎች እከሌ ይህን ሥፍራ ተቆጣጠረ፤ ይህን ያህል ገደለ፤ ያን ያህል አባረረ የምትሉ ሁሉ እባካችሁ ሆነም አልሆነም ወሬ ማናፈሳቹሁን አቁሙ። ዋ በህዋላ ይህች ሃገር እንደ ዪጎዝላቪያ ትሆንና ሁላችንም በቅርብና በርቀት ሃዘኑ እንዳይገለን እፈራለሁ። ህግ ማስከበር የአንድ ሰራዊት ቀዳሚ ተግባር ነው። በአንዲት ሃገር ውስጥ ሁለት ወይም ከዚያ በላይ የታጠቁ ሃይሎች መኖር አይችሉም። የሱዳኑ ፍልሚያ የዚያ ውጤት ነው። የወያኔና የብልጽግናው የ 3 ጊዜ ግብግብ እስከ አፍንጫው የታጠቀው ወያኔ አሻፈረኝ በማለቱ ነው። ስንቱ አለቀ፤ ስንቱ ፈረሰ፤ አያሳዝንም? ግን ሰውን ወደ መከራ የሚገፉት ዛሬም ተመችቷቸው በሃገርና በውጭ ሲንፈላሰሱ ማየት ያበሳጫል። ቢቻል ተመክረው፤ አለበለዚያም በሚገባቸው መንገድ መልስ ተሰቷቸው ሃገሪቱ ወደ ሰላም እስካልተመለሰች ድረስ ሰው ሰርቶ መብላቱ ቀርቶ ለማኝ መሆኑ አይቀሬ ነው። ከሶሪያ፤ ከየመን፤ ከሱማሊያ፤ ከኢራቅ ወዘተ እንማር። ጦርነት ለማንም አይጠቅምም። ይብቃን!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule