• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት

August 1, 2023 09:25 am by Editor 1 Comment

አሁናዊ የመከላከያ ሠራዊቱን ያለበትን ሁኔታ በተመለከተ የኢፌዴሪ የመከላከያ ሠራዊት የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት መግለጫ ሰጥቷል።

መግለጫውን የሰጡት የሠራዊቱ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ ኮሎኔል ጌትነት አዳነ፣ መግለጫው በተለያዩ አካላት በሠራዊቱ ላይ እየተናፈሱ ያሉ ብዥታዎችን ለማጥራት የተሰጠ ነው ብለዋል።

ሠራዊቱ ካለፉት ዓመታት በነበረበት ቁመና ላይ እንዳለ የሚያስቡ አካላት ካሉ የቆሙት እነርሱ እንጂ ሠራዊቱ ተራማጅ ነው ያሉት ኮሎኔል ጌትነት፣ ሠራዊቱ ዘርፈ ብዙ ግዳጁን እየተወጣ ነው ብለዋል።

“ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚል አካል ላይ ሠራዊቱ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ ይቀጥላልም ብለዋል።

ሠራዊቱን መቋቋም ያልቻሉ አካላት በሠራዊቱ ላይ ሰፊ የስም ማጥፋት ዘመቻ ላይ ይገኛሉም ነው ያሉት ኮሎኔል ጌትነት።

በተለይ አሁን ላይ በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ አካላት ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በኦሮሚያ ክልል ሸኔ የመደምሰስ ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን አብራርተዋል።

በአማራ ክልል በመሬት ላይ ካለው ግጭት የገዘፈ የሚዲያ ትግል ተከፍቷል ተብሏል በመግለጫው።

ከሰሞኑ በጎንደር የሰሜን ምዕራብ እዝን ዓመታዊ አፈጻጸም ላይ ለመገምገም ወደ ስፍራው እያቀኑ በነበሩ የሠራዊቱ አባላት ላይ ከጩሂት 2 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሲደርሱ ተኩስ  በሠራዊቱ ላይ መከፈቱን ጠቅሰዋል።

የሠራዊቱ አባላትም በመመለስ ላይ ሳለም በቆላድባ አካባቢ በተመሳሳይ ተኩስ ተከፍቷል ነው ያሉት።

ለዚህም ሠራዊቱ ችግሩን በብልሃት ለመፍታት መስራቱንም አስታውሰዋል።

ሐምሌ 23 ቀን 2015 ዓ.ም ከአካባቢው ማህበረሰብ፣ ከወጣቶች እና ከሃገር ሽማግሌዎች ጋር ውይይት ተካሂዶ እንደነበር እና በይቅርታ መዘጋቱን አንስተዋል። (ኢዜአ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: endf, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    August 1, 2023 03:21 pm at 3:21 pm

    እብድ በማያየው ነገር ይስቃል። አንዴ አንድ ጓደኛችን የጥበብ መጀመሪያ ምንድን ነው ተብሎ ተጠየቀ። ትንሽ ካሰበ በህዋላ ትዝ ያለው የእናቱ ቀሚስና መቀነት ነው። ቸኮል ብሎ ቀይ ጥለት አለና ሁላችንም አሳቀን። አሁን በሃበሻ ምድር የሚደረገው ፍልሚያ አላስፈላጊና በውጭና በውስጥ ሃይሎች የፈጠራ ወሬ እየፋመ እየጠፋ ህዝባችን በሰላም እንዳይኖር የሚደረግ የሃገር ጠላቶች የሥራ ውጤት ነው። የሚገርመው የሶሻል ሚዲያም ሆነ የሌላው ወሬ አርከፍካፊ በስማ በለው የሚያወራ፤ አልፎ ተርፎም በፈጠራ የሚደረግ ለጊዜው የሣንቲም ሽራፊ ለመለቃቀም ሆን ተብሎ የሚነዛ ወሬ ነው።
    ሲጀመር ፋኖና መከላከያ ሊፋለሙ የሚገባቸው ሃይሎች አይደሉም። እኔን የሚገርመኝ ሰው ብልጽግና ፓርቲ አባል በመሆኑ መገደሉ፤ ፋኖ በመሆኑ መታሰሩ ወይም መገደሉ ሁሉ የቁልቁለት መንገድ እንጂ በጭራሽ ለህዝባችን ሰላምና ብልጽግናን አያመጣም። በስመ ነጻነት የህዝባችን ሰቆቃ የሚያባብሱ ሁሉ ካለፈው የብሄር ትግል ውጣ ውረድ ትምህርት ያልወሰድ ጅሎች ናቸው። ስንቱን አውድሞ ለጥቂቶች ትርፍ እንደሆነ ዛሬ ላይ የቆሙ መመልከት ይችላሉ። ነጻ እናወጣሃለን ተብሎ በስሙ የተነገደበት ያ ብሄር ዛሬም በሰቆቃ ውስጥ ነው። ትርፍ የለሽ ፓለቲካ ውሃ ወቀጣ ነው። አሁንም በሃገሪቱ ልዪ ልዪ ክፍሎች የሚደረገው ውጊያና ማፈናቀል፤ ግድያና ዝርፊያ ሁሉ ትግል ሳይሆን ሽፍትነት ነው። ህዝብ እያሸበሩ ነጻነት የለም። ህዝብን እያፈናቀሉ አብሮ መኖር አይገኝም። ዛሬ ከጎንህ ያለው ወገንህ በዘሩና በቋንቋው ቤቱ ሲፈርስ፤ ሲዘረፍ፤ ሲፈናቀል እያየህ በሰላም የምታንቀላፋ ነገ ወረፋው ያንተው ይሆናል። የሰው ልጅ ክፋቱ እርከን የለውም። በፈለገው ጊዜ ጤነኛ ነው፤ ጥሩ ሰው ነው የተባለው ጨርቁን ጥሎ ሲሄድ አይተናል።
    ባጭሩ አሁን በጎንደር፤ በወሎ፤ በሽዋና በጎጃም የሚደረገው ግጭትና መንቆራቆስ በፍጥነት ሊገታ ይገባል። ወያኔ ያደረሰው በደል አልበቃ ብሎ ነው አሁን እንደገና ይህ ሁሉ ውድመት የሚደርሰው። እናንተ የወሬ ቱልቱላዎች እከሌ ይህን ሥፍራ ተቆጣጠረ፤ ይህን ያህል ገደለ፤ ያን ያህል አባረረ የምትሉ ሁሉ እባካችሁ ሆነም አልሆነም ወሬ ማናፈሳቹሁን አቁሙ። ዋ በህዋላ ይህች ሃገር እንደ ዪጎዝላቪያ ትሆንና ሁላችንም በቅርብና በርቀት ሃዘኑ እንዳይገለን እፈራለሁ። ህግ ማስከበር የአንድ ሰራዊት ቀዳሚ ተግባር ነው። በአንዲት ሃገር ውስጥ ሁለት ወይም ከዚያ በላይ የታጠቁ ሃይሎች መኖር አይችሉም። የሱዳኑ ፍልሚያ የዚያ ውጤት ነው። የወያኔና የብልጽግናው የ 3 ጊዜ ግብግብ እስከ አፍንጫው የታጠቀው ወያኔ አሻፈረኝ በማለቱ ነው። ስንቱ አለቀ፤ ስንቱ ፈረሰ፤ አያሳዝንም? ግን ሰውን ወደ መከራ የሚገፉት ዛሬም ተመችቷቸው በሃገርና በውጭ ሲንፈላሰሱ ማየት ያበሳጫል። ቢቻል ተመክረው፤ አለበለዚያም በሚገባቸው መንገድ መልስ ተሰቷቸው ሃገሪቱ ወደ ሰላም እስካልተመለሰች ድረስ ሰው ሰርቶ መብላቱ ቀርቶ ለማኝ መሆኑ አይቀሬ ነው። ከሶሪያ፤ ከየመን፤ ከሱማሊያ፤ ከኢራቅ ወዘተ እንማር። ጦርነት ለማንም አይጠቅምም። ይብቃን!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule