• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

CNN ትህነግን እንደ ማስረጃ ጠቅሶ የሠራው ዘገባና ያፈተለከው ቅሌት

September 12, 2021 10:09 am by Editor 1 Comment

ሲኤንኤን (CNN) “አሰቃቂው ዕይታ” የሚል ርዕስ የሰጠውን እና በሁመራ ተፈፅሟል ያለውን ግርፋት፣ ጅምላ እስር እና ግድያን በተመለከተ የምርመራ ዘገባ አቅርቧል።

እነዚህ ግርፋት፣ ጅምላ እስር እና ግድያ የተፈፀሙት “በኢትዮጵያ ሠራዊት እና አጋሮቹ” ሲል በገለጻቸው ኃይሎች መሆኑንም ምስክሮቹን ጠቅሶ ደምድሟል።

የዚህ የምርመራ ዘገባ መነሻ የሆነው በሱዳን ድንበር አካባቢ በሚገኝ ወንዝ ላይ የሚንሳፈፉ አስከሬኖች ዳግም መገኘታቸው እንደሆነ ሚዲያው ጠቅሷል።

ኒማ ኤልባጊር

ይሁን እንጂ የዘገባው አዘጋጅ የሆነችው ሱዳናዊቷ ጋዜጠኛ ኒማ ኤልባጊር ለምስክርነት የመረጠቻቸው ሰዎች ገለልተኛ አለመሆን እና የአሸባሪው ህወሓት ቡድን ደጋፊዎች መሆናቸው የዘገባውን ተዓማኒነት አጠያያቂ አድርጎታል።

በተለይ ተፈፅመዋል የተባሉትን ግድያዎች በዝርዝር የሚናገረው እና የሞቱ ሰዎች አስከሬን ያለበትን ቦታ አንድ በአንድ የሚመራው ‘ገሬ’ የተባለ ግለሰብ የአሸባሪው ቡድን ደጋፊ መሆኑን በገሃድ አሳይቷል።

ግልሰቡ ከፊት በኩል “ለካቲት 11” (ህወሓት የተመሠረተበትን ቀን የሚጠቁም) ከኋላ በኩል ደግሞ “ወይንቕንቕ” (የአሸባሪው ህወሓት አይበገሬነትን የሚገልጽ) ጽሑፍ ያለበትን ኮፊያ አድርጓል።

‘ገሬ’ ለበርካታ ዓመታት ኑሮውን በሱዳን ያደረገ የትግራይ ተወላጅ እና ከኢትዮጵያ ወደ ሱዳን የሚሰደዱ የትግራይ ተወላጆችን የሚቀበል መሆኑን ጋዜጠኛ ኒማ ገልጻለች።

ይህ ሰው ኑሮውን በሱዳን ካደረገ መቆዩቱን የምትገልጸው ጋዜጠኛዋ፣ “ሁመራ ውስጥ በኢትዮጵያ ወታደሮች እና አጋሮች ተፈፅሟል” ላለችው ግርፋት፣ ጅምላ እስር እና ግድያ ምስክር አድርጋ ያቀረበችበት አመክንዮ ለማንም ግልጽ አይደለም።

ሌላኛው አስከሬን በጫነች ጀልባ ላይ ከጋዜጠኛዋ እና ሌሎች ምስክሮች ጋር የሚታየው ግለሰብ የአሸባሪው ህወሓት ታጣቂ መሆኑን ካደረገው ኮፊያ መረዳት ይቻላል።

ቀድሞውኑ መንግሥትን ለመፈረጅ የሌለ ምክንያት እየፈጠሩ ክሶችን የሚያቀርቡ ወገኖችን ሰብስቦ ለእንደዚህ ዓይነቱ ከፍተኛ ውንጀላ የተሞላበት ዘገባ በምስክርነት ማቅረብ የሲኤንኤንን አቅጣጫ አመላካች ነው።

ሲኤንኤን እስካሁን በገለልተኛ አካል ያልተረጋገጠውን “የሁመራ ጭፍጨፋን” በተደጋጋሚ ሲያራግብ፣ የተመድ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ጭምር እያጣራው ስለሚገኘው የማይካድራ ጭፍጨፋ እስካሁን ትኩረት ሲሰጠው አይታይም።

ከማይካድራ ጭፍጨፋ በተጨማሪ የአሸባሪው ህወሓት ታጣቂዎች በአፋር ክልል ጋሊኮማ ስደተኞች ጣቢያ ላይ ስለፈፀሙት አረመኔያዊ ድርጊት ትንፍሽ አላለም።

በቅርቡ እንኳ በሰሜን ጎንደር ዳባት ወረዳ ጭና ቀበሌ የተፈፀመውን እና ከ200 በላይ ሰዎች የተጨፈጨፉበትን ድርጊት በርካታ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ሲዘግቡት ሲኤንኤን ጉዳዬ አላለውም።

በዚህ ሐቅን በረሳው ዘገባው ሲኤንኤን በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ አላስፈላጊ ጫና ለማሳደር ሞክሯል።

ነገር ግን ይህ ሙከራው ከአንድ ሚዲያ የሚጠበቀውን የጋዜጠኝነት ሥነ-ምግባርን የጣሰ መሆኑን በግልጽ ያመላከተ ነው። (ኢቢሲ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ


Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics, Slider Tagged With: CNN and TPLF, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    September 13, 2021 09:19 am at 9:19 am

    ኒማ ኤልባጊር በሱዳንና በግብጽ የተገዛች ከእውነት የራቁ ወሬዎችን ለCNN በማቀብለ የምትታወቅ ቅጥረኛ ሾተላይ ናት። የሚያሳዝነው ግን የዜና አውታሩ ይህን ወሬ ሳያጣራ ማናፈሱ ነው። አልፎ ተርፎም የእንግሊዙ ባርላማ እውነት ነው ብሎ ማመኑ ይባስ የድንቁርናቸው ጥግ ያሳያል። በመሰረቱ የወያኔ ዓላማ በውሸት ላይ ተመርኩዞ የአለምን እይታ መሳብ ነው። ግፍ እየሰሩ ግፍ ተሰራብኝ ማለት። ማንም ነጭ ማንም አረብ የፈለገውን ይበል የኢትዮጵያ ህዝብ በትግራይ ወራሪዎች ላይ ገሃድ የወጣውን ጭካኔና ገመናቸውን ተረድቷል። በዘር የሰከረው ይህ ስብስብ በገባባቸው የወሎ፤ የጎንደር፤ የአፋር መንደሮች ላይ ያደረሰው ጥፋት ሆን ተብሎ ሰውን ለማስራብና ለመከራ ለማጋለጥ የተደረገ ድርጊት ለመሆኑ እልፍ ነው ማስረጃው። ግን ወያኔ ከጦር ሜዳ የሞቱበትን ሰብስቦ ወንዝ ላይ እያሰረ በመጣል ሬሳ መጣ ካሜራ ይዛችሁ ጠብቁ በማለት ለሱዳናዊያን በመንገር ይህን የመሰለ ሸርና ሴራ በሙታን ላይ መፈጸሙ ከሰው ባህሪ የወጣ የፍጥረት አተላ ቡድን እንደሆነ ያስረግጣል። የወያኔን ክፋትና ሴራ ቀስ በቀስም ቢሆን አፍሪቃዊያንና ሌሎችም የዓለም ህዝቦች እየተረድት ነው። የዘር ማጥፋት ወንጀል ተፈጸመብኝ ይላል ይህ ሰው በላ ቡድን። እውነቱ ግን ከዘመናት በፊት ጀምሮ ዘር አጥፊ የሆነው ድርጅት የትግራዪ ወያኔ ሃርነት (ባርነት) ነው። ተንኮላቸው ጤነኛ የሆነ ሰው ከሚያስበው የከፋ በመሆኑ ረጋ ተብሎ ካልተጤነ በቀላሉ ለማየት ያስቸግራል። ይህ የሃገርና የህዝብ ነቀርሳ ቡድን በትግራይ መሬት እስካለ ድረስ የኢትዮጵያ ህዝብ ሰላም አያገኝም። ይህን ለማድረግ መታጠቅ፤ መደራጀትና ወራሪን መመከት ቀዳሚ ተግባር ይሆናል። መንግስት ይደርስልኛል ብሎ እጅና እግርን አጣጥፎ ከመቀመጥ ሴትም ወንድም ስልጠና ወስዶ በተቻለ መጠን ወያኔን ተጋፍጦ ራስንና ሃገርን ማዳን ወሳኝ ነው። ወያኔ ጦርነት ከእኔ በላይ ላሳር ነው ስለሚል የሚገባው ቋንቋ እሳትን በእሳት መከላከል ብቻ ነው። ወያኔ ይምረኛል ብሎ ማሰብ ከአንበሳ ጋር ተኝቶ አልበላም እንደማለት ነው። ሲርበው ይጎረድምሃል። ወያኔም አራዊት ነው። በአፋርና በአማራ ህዝብ ላይ የሰራውንና የሚሰራውን ማየት በቂ ነው።
    ሱዳናዊቷ ጋዜጠኛ ነኝ ባይ የምታስተላልፋቸውን መረጃ ቢስ ዘገባዎች ሁሉ ከአሁን በፊትም ቢሆን ተመልክቻቸዋለሁ። የፈጠራና ለም ዕራባዊያን ፍጆታ ወያኔ የሰራቸው ዘገባዎች ናቸው። በምችለው ሁሉ የነገሩን እውነተኛነት ለማመሳከርም ጥሬአለሁ። ግን የፈጠራና የወያኔ ጫወታ ወሬ እንደሆነ ብቻ ነው የተረዳኝ። እዚህ ላይ የዜና ቀባይዋም ሆነ የዜና አውታሩ ባለቤት እንግሊዞችን ጨምሮ እንደ ተሸወድ በገሃድ ማየት ይቻላል። አንድ የእንግሊዝኛ ቃል አለ ይህን ጉዳይ በደንብ ሊገልጽ የሚችል፡ ቃሉም Hoodwink ይሉታል። ነገርየው እየሆነ ያለው ወያኔ ልክ እንዳለፈው ሁሉ ሰውን የማታለል ዘይቤ ነው። ያ እማ ባይሆን አንድ ወይም ሁለት ሬሳዎችን አስቀርቶ ከታሰሩበት ገመድ ጀመሮ እስከ መልካቸው ነገሮችን በማፈላለግና በማመሳከር ወያኔ በካሚዪን ጭኖ ውሃ ላይ እያሰረ የለቀቃቸውን አስከሬኖች ማንነት ማረጋገጥ በተቻለም ነበር። ግን እኮ የማይካድራን ጭፍጨፋ የፈጸሙት ናቸው ወንዙ ላይ አስከሬን ለቃሚና ፎቶግራፍ አንሺ የነበሩት? በሰው ደም እጅ የተነከረ ሰው ለቋሚም ሆነ ለበድን ምስክር መሆን አይችልም።
    ከሁሉ የሚያሳዝነው የዜና አውታሩ ግርድፍና በውሸት የተቀነባበረ ወሬ ማናፈሱ ነው። ግን እኮ ይኸው የዜና አውታር አይደል እንዴ ቀዳሜ ዜና አቅራቢ ሆኖ የኢራቅን፤ የሊቢያን፤ የሶሪያን የአፍጋኒስታንን ወሬ ሲያናፍስ የኖረው። የዚህ የዜና አውታር ታማኒነት ከመነመነ ቆይቷል። አሁን ለይቶለት የውሸት የወያኔ ፕሮፓጋንዳ አናፋሽ መሆኑ የውድቀቱን ጥግ ያሳያል። እኔ በጣም የሚያሳዝኑኝ የወያኔ ጭፍን ደጋፊዎች ናቸው። ሰው እንዴት ነገርን በራሱ አስቦና አሰላስሎ ፈትኖ እውነቱን ከፓለቲካው የውሸት ቱልቱላ አይለይም? ወያኔ ለትግራይ ህዝብ የሰራው ትላንትም ሆነ ዛሬ ምን ነገር አለ? ማን እየሞተ ማን እየኖረ ነው በትግራይ መሬት ላይ? ግን ሰው ከዘር ሰልፈኝነት ወጣ ብሎ አለምንና ከባቢውን ማየት ካልቻለ ይህ ሁሉ ነገር አይታየውም። ለዚያ ነው የትግራይ ልጆች ዛሬም ወያኔን የሙጥኝ ያሉት። የፓለቲካ ፍልስፍናና ፓለቲከኞች አላፊዎች ናቸው። 70 ዓመት የተደከመበት የሩሲያው ፓለቲካ ሲንኮታኮት አይተናል። ታዲያ እንዴት የሰው ልጅ የብልጽግናም ሆነ የወያኔን የዘር ፓለቲካ እንዴት ተገን ያደርጋል? ይህ እብደት ነው። ሰው በረጋ መንፈስ የሰው ልጆችን መብትና ነጻነት አስመልክቶ ባሩድ ሳያሸት በሃሳብ ይፋተጋል። ግን ይህ በእኛ ሃገር አልተለመደም። ንፋሱና ገደሉ ሳይቀር ጦርነት ለምዷል። አራዊቶች የሰው አስከሬን መብላት ለምደዋል። እኛም የቁም በድኖች እርስ በእርሳችን ስንጠዛጠዝ በፊት የሚያለቅሱ አይኖች ዛሬም ያለቅሳሉ። ነጩና አረቡ አለም ደግሞ እኛ ጎን የተሰለፉ መስለው በፈካው እሳት ላይ ነዳጅ ያርከፈክፋሉ። የአሜሪካና የአውሮፓ ዋና ችግር ሱማሊያ፤ ኤርትራ፤ ጅቡቲ፤ ኢትዮጵያና ሌሎችም የአፍሪቃ ሃገሮች በአንድ አስበውና አልመው የጎለበተ ሃብትና ሰላም እንዲኖራቸው አይፈልጉም። ትላንትም ዛሬም ሴራቸው ይኸውን ነው። ለወያኔ የሳተላይት ስልኮችን፤ ሌሎችም የመገናኛ አውታሮችን፤ እሳትና መድሃኒቶችን የሚያቀብሉት በእርዳታ ስም የሚገቡት የእነዚህ ሃገሮች የስለላ መረብ ሰራተኞች ናቸው። ጥቁሩ ዓለም ከተኛበት ካልነቃ ገና ያፈራርሱናል። ከ 20 ዓመት በፊት ካቡል አፍጋኒስታን ላይ ቆመው የአፍጋንስታንን ህዝብ ከታሊባን ነጻ አወጣን ያሉን አሜሪካኖች እግሬ አውጪኝ ብለው ስፍራውን ሲለቁ አፍጋኒስታን ድጋሚ በታሊባን ተይዛለች። ኦሮማይ የሚያሰኘው ይህ ነው። ዛሬ ለወያኔ ደረሰበት ለሚሉት ግፍ የሚያላዝኑት አሜሪካኖች በየመን ህዝብ ላይ በተላላኪያቸው በሳውዲ የሚያዘንቡትን የመከራ ዶፍ የሚዘግበው የለም። ፓለቲካ የቀላዋጮችና የሌቦች ስብስብ ውጤት ነው። ህዝብ ገለ መሌ ሃገር የሚባለው ሁሉ ሽፋን ነው። እውነተኛ ዲሞክራሲም በምድር ላይ የለም። ይህን የሚረዳ ሰው ለሰው ልጆች መብትና ነጻነት ይታገላል እንጂ በዘሩ ሰክሮ የፓለቲካ እግዚኦታ በነጭ ፊት ተንበርክኮ አይለምንም። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule