ሙዚቃን በተለየ መንገድ በማዋሐድ ሙላቱ አስታጥቄ የሙዚቃ ሳይንቲስት መሆኑን በአምስት አሠርታት የሙዚቃ ጉዞው ውስጥ አስመስክሯል፡፡ የተለያዩ ቅላፄዎችንና ምቶችን ከተለያዩ አፍሪካ አገሮች፣ አሜሪካና አውሮፓ ሙዚቃ በመውሰድና በማጣመር አዲስ የሆነ ሙዚቃንም ለዓለም አበርክቷል፡፡ የኢትዮ ጃዝ ፈጣሪው ሙላቱ አስታጥቄ የሙዚቃ ትምህርቱን ያጠናው በለንደን፣ ኒውዮርክና ቦስተን ከተሞች ሲሆን፣ የራሱን የሆነ የሙዚቃ ስልት ከኢትዮጵያ የሙዚቃ ቅኝቶች ጋር አጣምሮ ኢትዮ ጃዝን ፈጥሯል፡፡ በቀላሉ በዓለም አቀፍ ሙዚቃ አፍቃሪዎች ዘንድ ጆሮ ማግኘት የቻለው ሙላቱ ከመቶ ሺሕ በላይ የሚሆኑ ታዳሚዎችም ኮንሠርቱን ለማየት መሽቀዳደም የተለመደ ሆኗል፡፡ ከሙዚቃ ክህሎቱም በተጨማሪ በጥንታዊ ሙዚቃዎች ላይ ፈር ቀዳጅ የሆኑ ምርምሮችንም በማካሄድ ነው፡፡ የአምስት አሠርታት የሙዚቃ ጉዞውንም በተመለከተ ከሪፖርተሩ … [Read more...] about “ሙዚቃ መምራትን ለዓለም ያስተዋወቀችው ኢትዮጵያ ናት”
Interviews
“እንተያያለን አስክሬንህ ነው የሚወጣው” የህወሃት አሸባሪዎች
* "በክፉ ጊዜ የከዱን አሉ፤ ለእነሱም ፈጣሪ ልቦና ይስጣቸው" "የመጣሁት ከትግል እንጂ ከሽርሽር አይደለም" ይላሉ ዳንኤል ሺበሺ! የቀድሞው አንድት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ምክትል ኃላፊና የደቡብ ቀጠና ኃላፊ ሆነው ሲያገለግሉ የነበረ ሲሆን ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ክስ ከተመሰረተባቸው በኋላ ላለፉት 22 ወራት በእስር ላይ ቆይተው ባለፈው ማክሰኞ ከሰዓት በኋላ ከእሥር ተፈትተዋል፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ናፍቆት ዮሴፍ አየር ጤና አካባ በተለምዶ ቻይና ካምፕ በተሰኘው የአቶ ዳንኤል መኖሪያ ቤት ተገኝታ በእስር ቆይታቸው ስላሳለፏቸው ነገሮች፣ ስለወደፊት ሀሳባቸውና ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ ተከታዩን ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ እንዴትና በምን ሁኔታ ነበር የተያዙት? የተያዝኩት ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም በተለምዶ ጀርመን አደባባይ … [Read more...] about “እንተያያለን አስክሬንህ ነው የሚወጣው” የህወሃት አሸባሪዎች
“ትግራይ ወረዳ ውስጥ ያለ የመንግሥት አሰራር በኦሮሚያ ውስጥ … ይገኛል”
* "የአዲስ አበባ መሬት በማለቁ ወደ ኦሮሚያ መሬት እጃቸውን መዘርጋት ጀመሩ" * "ማስተር ፕላኑ መሰሪ ነው" በቀለ ገርባ የአዲስ አበባና የፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን ማስተር ፕላንን በተመለከተ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ያለውን ዝርዝር አቋም በተመለከተ የፓርቲው ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባን አዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ በፅ/ቤታቸው ተገኝቶ አነጋግሯቸዋል፡፡ መንግሥት ማስተር ፕላኑ ከተሞችን በመሰረተ ልማት በማስተሳሰር እድገትን ለማምጣት ከፍተኛ ጥቅም አለው ይላል፡፡ ፓርቲያችሁ ደግሞ ማስተር ፕላኑን አልቀበልም ብሏል፡፡ በምን ምክንያት ነው የማትቀበሉት? እኛ ማስተር ፕላኑን የማንቀበለው በትክክል የህዝቡን የልማት ጥያቄ ለመመለስ የተዘጋጀ ነው የሚል እምነት ስለሌለን ነው፡፡ መንግሥት በዚህ አሳቦ ወደ ኦሮሚያ አጎራባች ከተሞች ዘልቆ እየገባ … [Read more...] about “ትግራይ ወረዳ ውስጥ ያለ የመንግሥት አሰራር በኦሮሚያ ውስጥ … ይገኛል”
“ገበሬው ነፃነት ካላገኘ ችጋር ሁልጊዜ በኢትዮጵያ ይኖራል” ፕሮፌሰር መስፍን
* “ችጋር የሰው ልጅ እንደ ማገዶ እንጨት ተለብልቦ የሚያልቅበት የውርደት ሞት ነው” ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ (Institute of Development Research) ሥር ከ1967 ዓ.ም. ጀምሮ ለ10 ዓመታት ያህል በ102 የኢትዮጵያ አውራጃዎች ላይ ምርምር አድርገው ስለ ድርቅ በእርሳቸው አጠራር (ስለ ችጋር) (Rural vulnerability to famine in Ethiopia 1958-1977) የሚል መጽሐፍ ጽፈዋል። የእንቢልታ ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል በዛሬው እትማችን ለበርካታ ዓመታት በድርቅ ጉዳይ ያካሄዱትን የምርምር ሥራ መሠረት አድርገን በወቅታዊው የአገሪቱ የድርቅ ሁኔታ ላይ ከጽዮን ግርማ ጋር ቆይታ አድርገዋል። (ዓርብ መጋቢት 26 ቀን 2000 ዓ.ም) ድርቅን በሚመለከት በርካታ ጥናቶች አድርገዋል። ለምን ያህል ዓመት ነው በጉዳዩ ዙሪያ … [Read more...] about “ገበሬው ነፃነት ካላገኘ ችጋር ሁልጊዜ በኢትዮጵያ ይኖራል” ፕሮፌሰር መስፍን
“በዓሉ ይመጣል ብዬ አሁንም በር በሩን አያለሁ”
በኢትዮጵያ ሥነ ፅሐፍ ውስጥ ስማቸው ጎልቶ ከሚጠሩት ደራስያን መካከል አንዱ የሆነው ደራሲና ጋዜጠኛ በዓሉ ግርማ "ኦሮማይ" በሚል ርዕስ ባሳተመው መፅሐፉ ሳቢያ መስዋዕትነትን የከፈለ ደራሲ ነው፡፡ በአፃፃፍ ቴክኒኩ፤ በአጫጭር አርፍተ ነገሮቹና በድርሰት መዋቅሩ አዲስ የአፃፃፍ ብልሃትን አምጠቷል ተብሎ የሚታመነው ደራሲ በዓሉ ግርማ የካቲት 24 ቀን 1976 ዓ.ም ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ ከቤቱ እንደወጣ የደረሰበት ያልታወቀ ደራሲ ነው፡፡ የበዓሉ መጨረሻ ከዓመት ዓመት ሲያነጋግርና የቆየና ያውቃሉ የሚባሉ ሰዎችን ምስክርነት እንደሻተ እነሆ 30 ዓመት ሞላው፡፡ ይህኑ መሰረት በማድረግ የሙያ አጋሩ ደራሲና ጋዜጠኛ አበራ ለማ ባለፉት ሁለት ተከታታይ እትሞች "የማይጮሁት በዓሉን የበሉ ጅቦች" የሚል መጣጥፉን በቁም ነገር መፅሔት ላይ አስነብቦናል፡፡ ይህንኑ መነሻ በማድረግ የበዓሉ ግርማን ባለቤት … [Read more...] about “በዓሉ ይመጣል ብዬ አሁንም በር በሩን አያለሁ”
“ጎንደር ቤተ መንግስት ውስጥ ኦሮሚኛ ቋንቋ ይነገር ነበር”
በተለያዩ ድረ-ገፆች በኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በሚያንሸራሽሩት ሃሳብ ይታወቃሉ፡፡ ስለ ኢትዮጵያኒዝም፣ ስለ ፓንአፍሪካኒዝም እንቅስቃሴዎች የተለያዩ ምልከታዎችና ምክረ ሃሳቦችን በማቅረብ ተሰሚነት ካላቸው ኢትዮጵያዊያን ምሁራን አንዱ ናቸው - ፕ/ር ማሞ ሙጬ፡፡ ሰሞኑን ጐንደር ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተበትን 60ኛ አመት በዓል ሲያከብር “Towards Innovative Africa: The Significance of Science, Technology, Engineering and Innovation for Sustainable Development” በሚል ርዕስ ጥናታዊ ፅሁፍ አቅርበዋል፡፡ ፕሮፌሰሩ በአሁን ሰአት በደቡብ አፍሪካ ሊዋኔ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቴክኖሎጂና በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ በማስተማር ላይ ይገኛሉ፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ ባለፈው ሳምንት በጐንደር … [Read more...] about “ጎንደር ቤተ መንግስት ውስጥ ኦሮሚኛ ቋንቋ ይነገር ነበር”
“የድሮ ስርዓት ናፋቂ”?
ይህ ቃለመጠይቅ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ ከአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ናፍቆት ተስፋዬ ጋር (19 April, 2014) ካደረጉት ቃለምልልስ ተቀንጭቦ የተወሰደ ነው፡፡ አዲስ አድማስ፤ ባለፉት ተከታታይ ሳምንታት በሬዲዮ ፋና ላይ በነፃው ፕሬስ ዙሪያ ውይይቶች ሲካሄዱ ቆይተዋል፡፡ እርስዎም በውይይቱ ላይ ተሳታፊ ነበሩ፡፡ በውይይቱ ላይ “ዶ/ር ዳኛቸው ስሜታዊ ሆነው ነበር” የሚሉ ወገኖች አሉ፡፡ “የድሮ ስርዓት ናፋቂ” የሚል ትችትም ተሰንዝሮቦታል፡፡ የእርስዎ ምላሽ ምንድን ነው? ዶ/ር ዳኛቸው፤ የስሜታዊነቱን ነገር ያመጡት እንኳን እነሱ ናቸው፡፡ ስድብና ዘለፋውን በመጀመር እነሱ ይቀድማሉ፡፡ “የድሮ ስርዓት ናፋቂ” ለሚለው በእውነቱ በናፍቆት ደረጃ ፍትህ ናፋቂ ነኝ፡፡ ዴሞክራሲና የህዝባችንን ነፃነት ናፋቂ ነኝ፡፡ የዱሮ ሥርዓት ናፋቂ የሚሉኝ “አሁን ያለንበት ወርቃማው ጊዜ ነው” የሚሉ ዜጎች … [Read more...] about “የድሮ ስርዓት ናፋቂ”?
“የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ በኢትዮጵያ ፍ/ቤቶች ላይ ያለው እምነት ተሟጥጧል”
የህዝበ ሙስሊሙ የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ወደ አፍሪካ የሰብዓዊ መብቶችና ህዝቦች ኮሚሽን ሂደው በመንግስት ላይ ክስ መመስረታቸው ይታወቃል። ይህንን በማስመልከትም በድር ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (ቢቢኤን) የኮሚቴውን የክስ ሂደት በቅርበት ከሚከታተለው ዶ/ር አወል ቃሲም አሎ ጋር በዚሁ ጉዳይ ቆይታ አድርጓል። ዶ/ር አወል የአለም ዓቀፍ ህግ ምሁር ሲሆን በአሁኑ ጊዜ በLondon School of Economics የሰብዓዊ መብት Fellow ነው። ቢቢኤን፡- የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ጉዳያቸውን ወደ አፍሪካ ኮሚሽን ለመውሰድና ለመክሰስ ያሰቡት ለምንድን ነው? ጉዳያቸውን በኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች መጨረስ አይችሉም ነበር? ዶክተር አወል፡- አመሰግናለሁ። የኢትዮጵያ ሙስሊሞች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ጉዳዩን ወደ አፍሪካ ኮሚሽን ለመውሰድ የተገደደበት ምክንያት በኢትዮጵያ … [Read more...] about “የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ በኢትዮጵያ ፍ/ቤቶች ላይ ያለው እምነት ተሟጥጧል”
ምሁራኑ ሠልጣኝ፣ ሹመኞች አሰልጣኝ የሆኑበት ዩኒቨርሲቲ ሆኗል – ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ
መጽሔታችን የአገራችን የትምህርት ሁኔታበከፍተኛ ደረጃ ችግር ላይ የወደቀ መሆኑን በመገንዘብ፣ የችግሩን ጥልቀት ለማወቅና የመፍትሄ ሃሳቦችን ለማስቀመጥ በዘርፉ ጥናትና ምርምር ካደረጉ ምሁራን ጋር ተከታታይ ውይይቶችንስታደርግ ቆይታለች፡፡ በዚህ ዕትማችንም ውይይቱን በመቀጠል ከዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ ጋር ስለትምህርት ፍልስፍና፣ ስለዩኒቨርሲቲ ተልዕኮና ስለሌሎቸ ተያያዥ ጉዳዮች ቆይታ አድርገናል፡፡ ዶ/ር ዳኛቸው ለአብዛኛው የመገናኛ ብዙኃን ተከታታይ እንግዳ ስላልሆኑ ማስተዋወቅ ያለብን አይመስለንም፡፡ ውይይቱን እነሆ፡- ዕንቁ፡-ውይይታችን በዩኒቨርሲቲባህሪና ትርጉም እንጀምር፡፡ ለመሆኑ ዩኒቨርሲቲ ምን ማለት ነው? ዶ/ር ዳኛቸው፡-ከሁሉ አስቀድሞ ይኼ ጥያቄ ለአንዴና ለመጨረሻ መልስ የሚሰጠው ሳይሆን በተለያየ ጊዜና በተለያየ የባህልና የአመለካከት አውድ ውስጥ ተፈትሾ ለመግለጽ የሚሞከር ጉዳይ … [Read more...] about ምሁራኑ ሠልጣኝ፣ ሹመኞች አሰልጣኝ የሆኑበት ዩኒቨርሲቲ ሆኗል – ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ
ፕሮፌሰሩ – ሰክነው ማዳመጥ ለሚችሉ መናገር ያስደስታቸዋል
ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ የኢትዮጵያ ሶሻል ፓርቲና የደቡብ ህብረት ፓርቲ መሪ ናቸው። በግል የመድረክ መስራች ሲሆኑ፣ የሚመሩት ድርጅትም በመድረክ ጥላ ስር ከተሰባሰቡት ፖለቲካ ድርጅቶች መካከል ይገኝበታል። ፕ/ር በየነን ጨምሮ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ኢህአዴግን በመቃወም የሚታወቁ ፖለቲከኞች ተተኪ ፖለቲከኞች አላዘጋጁም በሚል ይወቀሳሉ። በዚህ ጉዳይ ስማቸው ከሚነሱት መካከል አንዱ ፕ/ር በየነ ናቸው። ፕ/ር በየነ አሜሪካ ለሥራ መምጣታቸውን ተከትሎ የጎልጉል ዘጋቢ ቃለ ምልልስ አድርጎላቸዋል። ፕ/ር በየነ በቃለ ምልልሳቸው ወቅት በተደጋጋሚ "እኔ የምናገረው ሰክነው ማዳመጥ ለሚችሉት ነው" በማለት ያሳስባሉ። ለምን? ጎልጉል፡- ስለ መንግሥትና ተቃዋሚዎች እርቅ ጉዳይ ወሬ ይወራል የሰሙት ነገር አለ? ፕ/ር በየነ፡- የለም። ምንም አልሰማሁም። ጎልጉል፡- እርስዎ የሚመሩት ፓርቲ ጥያቄው … [Read more...] about ፕሮፌሰሩ – ሰክነው ማዳመጥ ለሚችሉ መናገር ያስደስታቸዋል