• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ጎንደር ቤተ መንግስት ውስጥ ኦሮሚኛ ቋንቋ ይነገር ነበር”

July 14, 2014 07:25 am by Editor 1 Comment

በተለያዩ ድረ-ገፆች በኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በሚያንሸራሽሩት ሃሳብ ይታወቃሉ፡፡ ስለ ኢትዮጵያኒዝም፣ ስለ ፓንአፍሪካኒዝም እንቅስቃሴዎች የተለያዩ ምልከታዎችና ምክረ ሃሳቦችን በማቅረብ ተሰሚነት ካላቸው ኢትዮጵያዊያን ምሁራን አንዱ ናቸው – ፕ/ር ማሞ ሙጬ፡፡ ሰሞኑን ጐንደር ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተበትን 60ኛ አመት በዓል ሲያከብር  “Towards Innovative Africa: The Significance of Science, Technology, Engineering and Innovation for Sustainable Development” በሚል ርዕስ ጥናታዊ ፅሁፍ አቅርበዋል፡፡

ፕሮፌሰሩ በአሁን ሰአት በደቡብ አፍሪካ ሊዋኔ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቴክኖሎጂና በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ በማስተማር ላይ ይገኛሉ፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ ባለፈው ሳምንት በጐንደር ሳለ ከፕ/ር ማሞ ሙጬ ጋር ያደረገውን ቃለ ምልልስ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡

የኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና ምንድን ነው?

የኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና የተጀመረው በአሜሪካ ነው፡፡ ከዚያ በእንግሊዝና በፈረንሳይ ቅኝ ወደተያዙ የአፍሪካ ሃገሮች ተዛመተ፡፡ እነ ካሜሮን፣ ሴኔጋል፣ ጋና፣ ናይጄሪያ… ወደ መሳሰሉት ሃገሮች ነው የተስፋፋው። የመስፋፋት ማዕከላት የነበሩት ደግሞ ቤተ – ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ ቤተ-ክርስቲያኖች የሃይማኖት አስተምህሮ ዘረኝነት ይደርስባቸው ነበር፡፡ ያንን እንዴት እንቃወመው ብለው ሲያስቡ ነው የኢትዮጵያኒዝም እንቅስቃሴ የመነጨው፡፡ ነጮች ሲሰብኩ ጥቁሮችን የሠይጣን ምሳሌ፣ ነጮቹን የመላእክት አምሳል አድርገው ነበር። ነገር ግን “ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች” የሚለውን የመፅሃፍ ቅዱስ ጥቅስ ስታይ ነጮቹን የሚወክል ስም የለም፡፡ ኢትዮጵያ የጥቁሮች ሃገርን ብቻ ነው የሚጠቅሰው፡፡ እናም “ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች” ሲል እግዚአብሔር ጥቁሮችን ይሰማል ማለት ነው ብለው ያምናሉ፡፡ የዚህ እንቅስቃሴ አራማጆች ለተጨቆኑ የጥቁር ህዝቦች “ኢትዮጵያን ማኒፌስቶ” የሚል እ.ኤ.አ በ1820 አወጡ። እነ አሜሪካና ሌሎች የበለፀጉት ሃገራት የስጋ ምግብ ሲሰጡ ኢትዮጵያ ግን የመንፈስ ምግብ ሰጠች ማለት ነው፡፡ በዚህ ከሁሉም ትበልጣለች፡፡ በአፍሪካ የነፃነት እንቅስቃሴ የተቋቋመው በኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና መነሻነት ነው፡፡ የመጀመሪያዎቹ የእንቅስቃሴ አራማጆች በኢትዮጵያዊነት ፍቅር የወደቁ ነበሩ፤ በዚህም ታስረዋል ተገድለዋል፡፡

ኢትዮጵያዊነት በዘርና በቋንቋ የሚለካ አይደለም፡፡ ሰዎች የመጣባቸውን ችግር ለመቋቋም ባደረጉት ትግል፣ ባገኙት ውጤትና ስኬት ውስጥ ያለፈ ፍልስፍና ነው፡፡ ኢትዮጵያዊነት የብሄር ትርጉም ያለው አይደለም፡፡ አንዳንድ ሰዎች ኢትዮጵያዊነትን ከዘር ጋር :- ከአማራ፣ ከትግሬ ከጉራጌ ጋር ወዘተ ያያይዛሉ፤ ነገር ግን ይሄ የተሳሳተ ነው፡፡ ኢትዮጵያዊነት ከትግል፣ ከስኬትና ከተገኙ የትግል ድሎች ጋር የተያያዘ ፍልስፍና ያለው ነው፡፡

ጥናትዎን ሲያቀርቡ፣ “ወደ ምዕራባውያኑ የሄደው ሁሉ የኛ ነገር ነው፤ ተመልሶ መምጣቱ አይቀርም” ብለው ነበር፡፡ ምን ለማለት ነው?

እኛ ሁሉም ነገር አለን፡፡ ቋንቋው፣ የስነ ህንፃ ጥበቡ፣ ስነፅሁፉ… ሁሉም አለን፡፡ ግን የራሳችንን ትተን ሌላውን ወደ መኮረጁ ገባን፣ ኩረጃ ጥሩ አይደለም፡፡ አወዛግቦናል። ሁሉንም ሚስጥራችንን የጥንት ኢትዮጵያውያን ተንትነው አስቀምጠውልናል፡፡ የእግዚአብሔር ማንነት ሚስጥር፣ የቀንና ሌሊት ሚስጥር የመሳሰሉት፡፡ በአቡሻከር እስከ 15 እና 22 ፕላኔቶ አሉ የሚል ተፅፏል፡፡ እኛ 9 ፕላኔቶች አሉ ተብለን ነው የተማርነው፡፡ አሁን ፈረንጆቹ 13 አድርሰዋቸዋል፡፡ እንግዲህ እኛ በመደበኛ ትምህርት ባንማረውም የቀደሙት ግን 22 ፕላኔቶች አሉ ብለው በአቡሻከር አስቀምጠዋል፡፡ አሁን እኔ ፕሮፌሰር ተብዬ በድጋሚ 13 ፕላኔቶች አሉ እየተባልኩ ልማር ነው ማለት ነው፡፡

ማንዴላ ከእስር ቤት ሲወጣ ነው ኤርትራ ከኢትዮጵያ የተገነጠለችው፡፡ ማንዴላ በወቅቱ ምን አለ አሉ? ለአቶ መለስ እና ለአቶ ኢሳያስ ስልክ ደውሎ “እንዴት አንድ ህዝብ ትከፋፍላላችሁ እኛ ከአውሮፓ የመጡ አፍሪካኖችንና ከአፍሪካ የተፈጠሩ አፍሪካኖችን አንድ እያደረግን፣ ለእናንተ አንድ የሆነውን ህዝብ እንዴት ትለያያላችሁ”? ብሏል ይባላል፡፡ በወቅቱም አቶ መለስ እና አቶ ኢሳያስ አንደኛቸው ፕሬዚዳንት አንደኛቸው ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆኑ ምክር ለግሷል፡፡ አገሪቱ ሳትገነጠል ማለት ነው፡፡  ግን አልተቀበሉትም፤ መከፋፈሉ መጣ፡፡

እኔ ወደ ደቡብ አፍሪካ ስሄድ፣ አንድ ደስ ያለኝ ነገር ምርጫ ሲያደርጉ ማንም ይመረጥ ዋናው የምርጫው ሂደት ውጤታማ መሆኑ ነው፡፡ ተቃዋሚ ነኝ የሚለው ወገን ተጠቃሁ አይልም፡፡ ለምሳሌ አሁን በስልጣን ላይ ያለውን መሪ ብዙዎቹ አይወዱትም ግን ምርጫው ከወገናዊነት የፀዳ መሆኑን ነው የሚናገሩት፡፡ በዚህ ሂደት አምስት ጊዜ ሰላማዊ ምርጫ አድርገዋል፡፡ እኔ በዚህ በጣም  እኮራባቸዋለሁ፡፡ ነጮች ጥቁርን ሰይጣን ነው እንጂ ሰው አይደለም ይሉ ነበር፡፡ እነ ማንዴላ ያንን ችግር በግጭት ሳይሆን በእርቅና በሰላማዊ መንገድ ነው የፈቱት፡፡ አሁን ከአፍሪካ ሃገራት መካከል እነ ቻድ፣ ማሊ፣ ሊቢያ ሌሎችም በግጭት ውስጥ ናቸው፡፡ እነዚህ ሃገሮች የደቡብ አፍሪካን ፈለግ ተከትለው ችግራቸውን ቢፈቱ ህዝባቸው ምንኛ በታደለ ነበር፡፡ በኢትዮጵያም ቢሆን ለግጭቶች መላ ሲፈለግ በመገዳደል ባይሆን ጥሩ ነው፡፡ በመናናቅ፣ በመዘላለፍ፣ ባለመተማመንና በውይይት ቢሆን ሃገርን በማስበለጥ፣ በመረዳዳት፣ የአመለካከት ለውጥ በማምጣትና በመወያየት መሆን አለበት፡፡ እኛ የፈለግነው ወገን ሥልጣን ካልያዘ ሞተን እንገኛለን የሚለው አስተሳሰብ መለወጥ ይኖርበታል፡፡
በቀጣይ አመት በኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ይካሄዳል? ከምርጫው ምን ይጠብቃል?

ምርጫው እግዚአብሄር ታክሎበትም ቢሆን ንፁህ መሆን አለበት፡፡ ንፁህ ከሆነና ያ ባህል ከተፈጠረ ለኢትዮጵያ ትልቅ ስኬት ነው፡፡ ደቡብ አፍሪካዎች ይሄን ማድረግ ችለዋል፡፡ በእነሱ እየቀናሁባቸው ነው፡፡ አሁን ለምሳሌ ዙማን ብዙዎች አይወዱትም፡፡ ኢኮኖሚያው ላይ ጥያቄ አለበት፤ ነገር ግን መርጠውታል፡፡ ዋናው ማን ተመረጠ የሚለው ሳይሆን ሂደቱን ሰው ማመን አለበት፡፡ ንፁህና እንከን የለሽ ነው ብሎ ከልቡ ሊቀበለው ይገባል፡፡ አለበለዚያ ምርጫ አያስፈልገንም፡፡

የዳያስፖራው ፖለቲካ ለዚህች ሃገር ባለው ፋይዳ ላይ ጥያቄ የሚያነሱ ወገኖች አሉ፡፡ እርስዎስ ምን ይላሉ?

ከቅንጅት በፊት እዚህ ሃገር መጥቼ ነበር፡፡ ገጠር ድረስ በበቅሎ ሄጄ አይቸዋለሁ፡፡ በወቅቱ የገጠሩ ሰው ሁሉ ስለምርጫ በሚገባ እንዳወቀ የተረዳሁበት አጋጣሚ ነበር፡፡ በጣም ደስ ይላል ብዬ ተስፋ አድርጌ ወደ መጣሁበት ተመለስኩ፡፡ ከምርጫው በኋላ ግን የሆነው አሳዛኝ ነው፡፡ በወቅቱም በፃፍኩት ፅሁፍ፤ እንዲህ ያለ እድል ተገኝቶ እንዴት እናበላሸዋለን ብዬ ተቆጭቻለሁ። ኢትዮጵያ አንዳች ነገር እንዳጣች ተናግሬያለሁ፡፡ በውጪ ሃገር የተለያዩ ተቃዋሚዎች አሉ፡፡ ግን በጣም የተበጣጠሱ፣ በአንድነት ተቀናጅተው ሃይል መሆን ያልቻሉ ናቸው፡፡ በሃገራችን ለውጥን በሰላማዊ መንገድ ማምጣት አለብን የሚለው አስተሳሰብ ቢዳብር ጥሩ ነው። እኔ ለኢትዮጵያ ጥሩ ነገር ነው የምመኘው፡፡

በዳያስፖራው አካባቢ የከፋ ዘረኝነት ይራመዳል ይባላል፡፡ እርስዎም በፅሁፍዎ ይሄን ነገር በተደጋጋሚ ይገልፁታል፡፡ የዚህ የዘረኝነት አንድምታው ምንድን ነው?

አንድ ጓደኛ አለኝ፡፡ ከሱ ጋር ሆነን አንድ ጊዜ የብሄራዊ መግባባት መድረክ ፈጠርን፡፡ ሁሉንም ብሄሮች የብሄር ፖለቲከኞች ጠራን፤ ኦነግን ጨምሮ፡፡ ግን ለመወያየት ከባድ ነበር፤ ዘረኝነት አይሎ አስቸገረን። ዘረኝነታቸው የእውነት ይሁን የይስሙላ አላውቅም፡፡ እኔን “የግራዚያኒን ሃውልት ለምን ትቃወማላችሁ? የአፄ ምኒልክ እያለ” ይሉኝ ነበር፡፡ እኔም በወቅቱ ተናድጄ “እንዴት አፄ ምኒልክን እንደዚህ ትላላችሁ” ብዬአቸዋለሁ። አፄ ምኒልክ ለአፍሪካ ትልቅ ሚና ተጫውተዋል፡፡

ለአፍሪካውያን ድል የአፄ ምኒልክ እጅ አለበት፤ እሳቸውን ማጥቃት ማለት ጠቅላላ ኢትዮጵያን ማጥቃት ነው ብዬ ተቃውሜያለሁ፡፡ እንዲህ ያሉ ፅንፍ የያዙ አለመግባባቶች ይታያሉ፡፡ ግን ሰው ከዚህ ወጥቶ በውይይት መግባባትን ቢለምድ ጥሩ ነው፡፡ በአንድ የሆነ መላ ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት የዘር ፖለቲካ ብትወጣ ጥሩ ነው፡፡

ይሄ በቅርቡ እውን የሚሆን ይመስልዎታል?

አሁን እንግዲህ እዚህ የምትኖሩት ናችሁ ይሄን የምታውቁት፡፡ እኔ ውጭ ነው የምኖረው፡፡ ነገር ግን የዘር ፖለቲካ አይጠቅምም የሚለው አቋሜ ነው፡፡ ኢትዮጵያዊነት፣ አፍሪካዊነት ብቻ ይበቃል፡፡ ወደ ታች ወርዶ በቋንቋ ምናምን መከፋፈሉ አያዋጣም፡፡ ዋናው የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ መብቶቹ መጠበቃቸው ነው። ቋንቋ የሰውን ልጅ ሊከፋፍል አይገባውም፡፡ ለምሳሌ በደቡብ አፍሪካ 11 ያህል ቋንቋዎች ለማስተማሪያነት ይውላሉ፡፡ በእነሱ ዘንድ ቋንቋዎቹ ከመግባቢያነት ያለፈ ትርጉም የላቸውም፡፡ እኔ አሁን ኦሮሚኛ፣ ትግሪኛ፣ አማርኛ… የሌሎች ቋንቋዎችን ሙዚቃዎችም ስሰማ ደስ ይለኛል፡፡ ታዲያ እንዴት ነው አማራ ብዬ ራሴን የምነጥለው፡፡ በአማራ ክልል የኦሮሞ ዞን ማለት ምን ማለት ነው? እኔ ምን እንደሆነ አይገባኝም፡፡ መብቶች በሙሉ በህግ ጥበቃ ከተደረገላቸው በቂ ነው፡፡ እኔ አሁን ማሞ ሙጬ ነው ስሜ፡፡ አላውቅም አባቴ ኦሮሞ ሊሆን ይችላል፡፡ ምክንያቱም ኦሮሞዎች ጎንደርን ለረጅም አመታት አስተዳድረዋል፡፡ ጎንደር ቤተ መንግስት ውስጥ ኦሮሚኛ ቋንቋ ይነገር ነበር፡፡ ኢትዮጵያዊነት ፍፁም የተደባለቀና የተቀላቀለ ነው፡፡

የፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ ምን ያህል አፍሪካን ያስተሳስራል ይላሉ?

በዚህ አመት በፓን አፍሪካኒዝም ላይ መፅሃፍ ላወጣ እያዘጋጀሁ ነው፡፡ እኛ ኢትዮጵያውያን ከኢትዮጵያዊነትም ባለፈ አፍሪካዊነት ላይ አስቀድመን ብንንቀሳቀስ ለእኛም ሆነ ለአፍሪካውያን ትልድ ድል ነው፡፡ ህዝቡ የፓን አፍሪካኒዝምን ፅንሰ ሃሳብ ቢረዳ፣ ሌሎች አፍሪካውያን በፊት ከሚሰጡን ፍቅር የላቀ ፍቅር ይሰጡን ነበር፡፡ አሁን ያሉት ፖለቲከኞች በዚህ መንፈስ እንዲራመዱ እግዚሃር ይርዳቸው፡፡ ከዘረኝነት ወጥተው በኢትዮጵያዊነት እና በአፍሪካዊነት እንዲያስቡ እንፀልይላቸዋለን፡፡

በመንግስት በኩል ኢኮኖሚው እያደገ መሆኑ ይነገራል፡፡ በሌላ በኩል ግን ዕድገቱ ህዝቡን ከድህነት አላወጣውም የሚል ትችት ይሰነዘራል፡፡ የእርስዎ አስተያየት ምንድነው?

በኢኮኖሚ እድገት ብሄራዊ ገቢን ማብዛት ብቻውን ጥቅም የለውም፡፡ ሰዎችን በማፈናቀል መሬት ለባዕድ በመስጠት የሚመጣ እድገት ጥሩ አይደለም፡፡ እድገት ማለት የህዝቡን ህይወት መቀየር ሲችል ነው፡፡ እንደዚህ አይነት ሁኔታ ካልተፈጠረ እድገት አለ ለማለት ይከብዳል፡፡ የህዝቡን ህይወት መቀየር መቻል አለበት፡፡ ይሄን ለማድረግ ጥሩ የሆነ የኢኮኖሚ ፖሊሲና ማህበራዊ አቅጣጫ ያስፈልጋል፡፡ ብዙዎቹ የአፍሪካ ሃገሮች ይሄ ይጎድላቸዋል፡፡

ብዙውን ጊዜ በውጭ እርዳታ ላይ ስለሚንጠለጠሉ ያመኑበትን ፖሊሲያቸውን ትተው በለጋሾች ለመመራት ይገደዳሉ፡፡ ሌላው መኮረጅም ጥሩ አይደለም፡፡ ለምሳሌ ከቻይና መማር ያለብን እንዴት ጎበዝ እንደሆኑ ብቻ ነው፡፡ ከዚያ በኋላ የራስን የቤት ስራ መስራት ነው፡፡ አሁን ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ሃብት ስንመለከት፣ አንድም ዜጋዋ መራብ አልነበረበትም፡፡(ርእሱ የተቀየረ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Interviews Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Melese Getaneh says

    August 28, 2014 06:39 pm at 6:39 pm

    First, i need to thank prf. Mamo Much.Next i have an idea on this issue. In my view now ‘Ethiopianism’ comes to ‘Ethinic ideologies’. So how to build up the idea of “ETHIOPIANISM” in to days context.Thanks!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule