• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል

February 3, 2023 10:06 am by Editor Leave a Comment

የኮማንዶ ብርጌዱ የተሣካ የተልዕኮ አፈፃፀሙ ታይቶና ተገምግሞ በ1992 ዓ.ም በክፍለጦር ደረጃ ማደጉ ይታወቃል፡፡ ከ2009 ዓ.ም ወዲህ ከክፍለጦር በላይ ሆኖ መደራጀቱም እንዲሁ፡፡

በሀገራችን ላይ የሚፈፀም ማንኛውንም ትንኮሳ መመከት እና መደምሰስ የሚችል አደረጃጀት ለመፍጠር በማሰብ የልዩ ኃይልና የአየር ወለድ አሃዱዎችን በማሥፋት የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ የሚለውን ስያሜ እና አደረጃጀት አሁን ላይም ይዞ ይገኛል፡፡

የሚሠጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ በእምነት የሚፈፅምና በከፍተኛ ፅናት ዘብ የሚቆም እንዲሁም በተሰማራበት የውጊያ ውሎ የውጊያው ማርሽ ቀያሪ እና አይበገሬ ሠራዊት በመገንባት ባሳለፍናቸው ዘመቻዎች አኩሪ የጀግንነት ገድል እንደ ዕዝ በመፈፀም የላቀ ጀግና ሜዳይ ተሸላሚ ለመሆን በቅቷል፡፡

በኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ ሥር ካሉት ወታደራዊ የአቅም ግንባታ ማዕከላት አንዱ የኮማንዶና አየር ወለድ ማሠልጠኛ ማዕከል ሲሆን በውስጡ አራት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤቶችንና አንድ ድጋፍ ሰጭ ክፍልን አካቶ የያዘ ነው፡፡

ማዕከሉ ማንኛውንም ወታደራዊ ግዳጅ ሕዝባዊ ባሕርይ ተላብሶ፣ በላቀ አስተሳሰብ፣ ስነልቦና፣ አካላዊ፣ ቴክኒካዊና ሥልታዊ ብቃት መፈፀም የሚችሉ የኮማንዶ፣ የአየርወለድ፣ የልዩ ኃይል እና ፀረ-ሽብር ተዋጊ ወታደሮችን እና የበታች ሹም አመራሮችን በማፍራት ሀገራዊ ተልዕኮውን በውጤት እየፈፀመ ይገኛል፡፡

ማሠልጠኛ ማዕከሉ የሀገር ወዳድነት ተምሳሌቶች እና ገፀ በረከቶች የሆኑ የቀድሞ የሠራዊት አባላት እና ብቃታቸውን በተግባር ያረጋገጡ አሰልጣኞችን በመያዝ የበኩሉን ድርሻ የተወጣ እና እየተወጣ የሚገኝ የሠራዊታችን የግንባታ ማዕከል ነው፡፡

የኮማንዶ ማሠልጠኛ ልዩ የሆነ የግዳጅ አይነቶችን እንደ አስፈላጊነቱ ከየብስ፣ ከባሕር እና ከአየር በመነሳት ውጊያን ማከናወን የሚያስችል አቅም ያላቸውና በተሰማሩበት የግዳጅ ቀጠና ተጣጣፊ በሆነ ወታደራዊ ብልሃት ተልዕኳቸውን የሚፈፅሙ የውጊያ ማርሽ ቀያሪና ጠላት አንበርካኪ አባላትን በሚገባ አሠልጥኖ የሚያበቃ አንጋፋ ማሠልጠኛ ነው፡፡

ማንኛውንም የውጊያ ግዳጅ ለመወጣት የሚያስችሉትን እና ድንገተኝነትን የሚያላብሱ ወታደራዊ አቅምን የሚያሥጨብጡ የሚያሰለጥኑ አሰልጣኞች ሁለንተናዊ ብቃትን የተላበሱና የተመረጡ አቅም ፈጣሪ አቅም ያላቸው በዘመኑ የውጊያ ጥበብ ወታደራዊ አስተሳሰብ ላይ የረቀቁ ቴክኒኮችን እና ታክቲኮችን በብቃት በማስጨበጥ አሰልጣኞች አሥተዋፇቸው ከፍተኛ ነው፡፡

በከፍተኛ የዓላማ ፅናትና ቁርጠኝነት እንዲሁም በዲስፕሊን አክባሪነት የተገነቡ በሃገር ውስጥም ይሁን ከሀገር ውጪ የሚሰጣቸውን የልዩ ኦፕሬሽን ውጊያ ተልዕኮ በነፍስ ወከፍ እና በቡድን በላቀ የጀግንነት ውጤት ተልዕኳቸውን የሚወጡ የልዩ ኃይል ፀረ ሽብር ወታደሮችን በማሠልጠን ማሰልጠኛ ማዕከሉ ኃላፊነቱን በሚገባ ተወጥቷል፡፡

ጠንካራ ሀገራዊ እና ተቋማዊ ዕምነት ያላቸው በማንኛውም ጊዜና ሁኔታ የሚሰጣቸውን የኮማንዶና አየር ወለድ ኃይል በብቃት መምራትና ግዳጃቸውን መወጣት የሚችሉ እንዲሁም መመሪያና ደንብና ጠንቅቀው ያወቁ በመመሪያ መፈጸምና ማስፈፀም የሚችሉ የበታች ሹም አመራሮችን ማፍራት ላይም ማሠልጠኛ ማዕከሉ ከፍተኛ ሥራ ሠርቷል፡፡

የኮማንዶና አየር ወለድ ማሠልጠኛ የክልል የፌዴራል እና ለሀገራችን ሠላም እውን መሆን የሚታትሩ የፀጥታ ሃይሎችን አሠልጥኖ በማብቃቱ ረገድ ከፍተኛ ሀገራዊ አሥተዋፆ ያለው ማሠልጠኛ ነው፡፡

ማሠልጠኛ ማዕከሉ ከአካባቢው ህብረተሠብና የመስተዳደር አካላት ጋር በማህበራዊ፣ በፀጥታ፣ በአካባቢ ልማትና በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ሥራዎች ላይ ተባብሮ በመስራት እና የተቸገሩ ወገኖችን አሥፈላጊውን ድጋፍ በማድረጉ ረገድ ማሠልጠኛ ማዕከሉ ለየት ያለ ተወዳጅ እንቅስቃሴ የሚያደርግ ነው ፡፡

በድምሩ የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ በአራቱም የሀገራችን ማዕዘናት በመንቀሳቀስ ለተፈጥሮ መሰናክሎች ሳይበገር በርሃውን፣ ውሀ ጥሙን፣ አስቸጋሪውን የእግር ጉዞ አልፎ ለሀገራችን ሰላምና ፈጣን ልማት በመስዋዕትነት የደመቀ ሕያው ታሪክ ያኖረ ዕዝ ሲሆን አሁንም አባላቱ በታላቅ ሀገራዊ ጀግንነት ተልዕኳቸውን በውጤት እየፈፀሙ ይገኛሉ፡፡ (የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት፣ ኤልያስ ባይለየኝ ፎቶግራፍ ሃይሉ ሉሌ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Politics Tagged With: endf, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm
  • “ሙሽራው እስኪመጣ የምትቆይ ቤተክርስቲያን እናድርጋት” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ February 15, 2023 03:13 pm
  • በመዝገበ ቃላት የችጋር መጠሪያ የነበረችው ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ስንዴ ወደ ውጭ ላከች February 13, 2023 03:28 am
  • ውዝግቡን በሐዋሪያት መንገድ ለመፍታት ስምምነት ላይ ተደርሷል February 10, 2023 09:06 am
  • የሚከተልህ ሁሉ ወዳጅህ አይደለም – መልዕክት “ለመንፈሳዊው ቄሮ” መሪ ዘመድኩን በቀለ! February 10, 2023 12:48 am
  • በሰማዕትነት ጥሪ ቤተመንግሥቱን ባቋራጭ መቆጣጠር February 9, 2023 01:25 pm
  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule