• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል

February 3, 2023 10:06 am by Editor Leave a Comment

የኮማንዶ ብርጌዱ የተሣካ የተልዕኮ አፈፃፀሙ ታይቶና ተገምግሞ በ1992 ዓ.ም በክፍለጦር ደረጃ ማደጉ ይታወቃል፡፡ ከ2009 ዓ.ም ወዲህ ከክፍለጦር በላይ ሆኖ መደራጀቱም እንዲሁ፡፡

በሀገራችን ላይ የሚፈፀም ማንኛውንም ትንኮሳ መመከት እና መደምሰስ የሚችል አደረጃጀት ለመፍጠር በማሰብ የልዩ ኃይልና የአየር ወለድ አሃዱዎችን በማሥፋት የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ የሚለውን ስያሜ እና አደረጃጀት አሁን ላይም ይዞ ይገኛል፡፡

የሚሠጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ በእምነት የሚፈፅምና በከፍተኛ ፅናት ዘብ የሚቆም እንዲሁም በተሰማራበት የውጊያ ውሎ የውጊያው ማርሽ ቀያሪ እና አይበገሬ ሠራዊት በመገንባት ባሳለፍናቸው ዘመቻዎች አኩሪ የጀግንነት ገድል እንደ ዕዝ በመፈፀም የላቀ ጀግና ሜዳይ ተሸላሚ ለመሆን በቅቷል፡፡

በኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ ሥር ካሉት ወታደራዊ የአቅም ግንባታ ማዕከላት አንዱ የኮማንዶና አየር ወለድ ማሠልጠኛ ማዕከል ሲሆን በውስጡ አራት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤቶችንና አንድ ድጋፍ ሰጭ ክፍልን አካቶ የያዘ ነው፡፡

ማዕከሉ ማንኛውንም ወታደራዊ ግዳጅ ሕዝባዊ ባሕርይ ተላብሶ፣ በላቀ አስተሳሰብ፣ ስነልቦና፣ አካላዊ፣ ቴክኒካዊና ሥልታዊ ብቃት መፈፀም የሚችሉ የኮማንዶ፣ የአየርወለድ፣ የልዩ ኃይል እና ፀረ-ሽብር ተዋጊ ወታደሮችን እና የበታች ሹም አመራሮችን በማፍራት ሀገራዊ ተልዕኮውን በውጤት እየፈፀመ ይገኛል፡፡

ማሠልጠኛ ማዕከሉ የሀገር ወዳድነት ተምሳሌቶች እና ገፀ በረከቶች የሆኑ የቀድሞ የሠራዊት አባላት እና ብቃታቸውን በተግባር ያረጋገጡ አሰልጣኞችን በመያዝ የበኩሉን ድርሻ የተወጣ እና እየተወጣ የሚገኝ የሠራዊታችን የግንባታ ማዕከል ነው፡፡

የኮማንዶ ማሠልጠኛ ልዩ የሆነ የግዳጅ አይነቶችን እንደ አስፈላጊነቱ ከየብስ፣ ከባሕር እና ከአየር በመነሳት ውጊያን ማከናወን የሚያስችል አቅም ያላቸውና በተሰማሩበት የግዳጅ ቀጠና ተጣጣፊ በሆነ ወታደራዊ ብልሃት ተልዕኳቸውን የሚፈፅሙ የውጊያ ማርሽ ቀያሪና ጠላት አንበርካኪ አባላትን በሚገባ አሠልጥኖ የሚያበቃ አንጋፋ ማሠልጠኛ ነው፡፡

ማንኛውንም የውጊያ ግዳጅ ለመወጣት የሚያስችሉትን እና ድንገተኝነትን የሚያላብሱ ወታደራዊ አቅምን የሚያሥጨብጡ የሚያሰለጥኑ አሰልጣኞች ሁለንተናዊ ብቃትን የተላበሱና የተመረጡ አቅም ፈጣሪ አቅም ያላቸው በዘመኑ የውጊያ ጥበብ ወታደራዊ አስተሳሰብ ላይ የረቀቁ ቴክኒኮችን እና ታክቲኮችን በብቃት በማስጨበጥ አሰልጣኞች አሥተዋፇቸው ከፍተኛ ነው፡፡

በከፍተኛ የዓላማ ፅናትና ቁርጠኝነት እንዲሁም በዲስፕሊን አክባሪነት የተገነቡ በሃገር ውስጥም ይሁን ከሀገር ውጪ የሚሰጣቸውን የልዩ ኦፕሬሽን ውጊያ ተልዕኮ በነፍስ ወከፍ እና በቡድን በላቀ የጀግንነት ውጤት ተልዕኳቸውን የሚወጡ የልዩ ኃይል ፀረ ሽብር ወታደሮችን በማሠልጠን ማሰልጠኛ ማዕከሉ ኃላፊነቱን በሚገባ ተወጥቷል፡፡

ጠንካራ ሀገራዊ እና ተቋማዊ ዕምነት ያላቸው በማንኛውም ጊዜና ሁኔታ የሚሰጣቸውን የኮማንዶና አየር ወለድ ኃይል በብቃት መምራትና ግዳጃቸውን መወጣት የሚችሉ እንዲሁም መመሪያና ደንብና ጠንቅቀው ያወቁ በመመሪያ መፈጸምና ማስፈፀም የሚችሉ የበታች ሹም አመራሮችን ማፍራት ላይም ማሠልጠኛ ማዕከሉ ከፍተኛ ሥራ ሠርቷል፡፡

የኮማንዶና አየር ወለድ ማሠልጠኛ የክልል የፌዴራል እና ለሀገራችን ሠላም እውን መሆን የሚታትሩ የፀጥታ ሃይሎችን አሠልጥኖ በማብቃቱ ረገድ ከፍተኛ ሀገራዊ አሥተዋፆ ያለው ማሠልጠኛ ነው፡፡

ማሠልጠኛ ማዕከሉ ከአካባቢው ህብረተሠብና የመስተዳደር አካላት ጋር በማህበራዊ፣ በፀጥታ፣ በአካባቢ ልማትና በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ሥራዎች ላይ ተባብሮ በመስራት እና የተቸገሩ ወገኖችን አሥፈላጊውን ድጋፍ በማድረጉ ረገድ ማሠልጠኛ ማዕከሉ ለየት ያለ ተወዳጅ እንቅስቃሴ የሚያደርግ ነው ፡፡

በድምሩ የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ በአራቱም የሀገራችን ማዕዘናት በመንቀሳቀስ ለተፈጥሮ መሰናክሎች ሳይበገር በርሃውን፣ ውሀ ጥሙን፣ አስቸጋሪውን የእግር ጉዞ አልፎ ለሀገራችን ሰላምና ፈጣን ልማት በመስዋዕትነት የደመቀ ሕያው ታሪክ ያኖረ ዕዝ ሲሆን አሁንም አባላቱ በታላቅ ሀገራዊ ጀግንነት ተልዕኳቸውን በውጤት እየፈፀሙ ይገኛሉ፡፡ (የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት፣ ኤልያስ ባይለየኝ ፎቶግራፍ ሃይሉ ሉሌ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Politics Tagged With: endf, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule