• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል

February 3, 2023 10:06 am by Editor Leave a Comment

የኮማንዶ ብርጌዱ የተሣካ የተልዕኮ አፈፃፀሙ ታይቶና ተገምግሞ በ1992 ዓ.ም በክፍለጦር ደረጃ ማደጉ ይታወቃል፡፡ ከ2009 ዓ.ም ወዲህ ከክፍለጦር በላይ ሆኖ መደራጀቱም እንዲሁ፡፡

በሀገራችን ላይ የሚፈፀም ማንኛውንም ትንኮሳ መመከት እና መደምሰስ የሚችል አደረጃጀት ለመፍጠር በማሰብ የልዩ ኃይልና የአየር ወለድ አሃዱዎችን በማሥፋት የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ የሚለውን ስያሜ እና አደረጃጀት አሁን ላይም ይዞ ይገኛል፡፡

የሚሠጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ በእምነት የሚፈፅምና በከፍተኛ ፅናት ዘብ የሚቆም እንዲሁም በተሰማራበት የውጊያ ውሎ የውጊያው ማርሽ ቀያሪ እና አይበገሬ ሠራዊት በመገንባት ባሳለፍናቸው ዘመቻዎች አኩሪ የጀግንነት ገድል እንደ ዕዝ በመፈፀም የላቀ ጀግና ሜዳይ ተሸላሚ ለመሆን በቅቷል፡፡

በኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ ሥር ካሉት ወታደራዊ የአቅም ግንባታ ማዕከላት አንዱ የኮማንዶና አየር ወለድ ማሠልጠኛ ማዕከል ሲሆን በውስጡ አራት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤቶችንና አንድ ድጋፍ ሰጭ ክፍልን አካቶ የያዘ ነው፡፡

ማዕከሉ ማንኛውንም ወታደራዊ ግዳጅ ሕዝባዊ ባሕርይ ተላብሶ፣ በላቀ አስተሳሰብ፣ ስነልቦና፣ አካላዊ፣ ቴክኒካዊና ሥልታዊ ብቃት መፈፀም የሚችሉ የኮማንዶ፣ የአየርወለድ፣ የልዩ ኃይል እና ፀረ-ሽብር ተዋጊ ወታደሮችን እና የበታች ሹም አመራሮችን በማፍራት ሀገራዊ ተልዕኮውን በውጤት እየፈፀመ ይገኛል፡፡

ማሠልጠኛ ማዕከሉ የሀገር ወዳድነት ተምሳሌቶች እና ገፀ በረከቶች የሆኑ የቀድሞ የሠራዊት አባላት እና ብቃታቸውን በተግባር ያረጋገጡ አሰልጣኞችን በመያዝ የበኩሉን ድርሻ የተወጣ እና እየተወጣ የሚገኝ የሠራዊታችን የግንባታ ማዕከል ነው፡፡

የኮማንዶ ማሠልጠኛ ልዩ የሆነ የግዳጅ አይነቶችን እንደ አስፈላጊነቱ ከየብስ፣ ከባሕር እና ከአየር በመነሳት ውጊያን ማከናወን የሚያስችል አቅም ያላቸውና በተሰማሩበት የግዳጅ ቀጠና ተጣጣፊ በሆነ ወታደራዊ ብልሃት ተልዕኳቸውን የሚፈፅሙ የውጊያ ማርሽ ቀያሪና ጠላት አንበርካኪ አባላትን በሚገባ አሠልጥኖ የሚያበቃ አንጋፋ ማሠልጠኛ ነው፡፡

ማንኛውንም የውጊያ ግዳጅ ለመወጣት የሚያስችሉትን እና ድንገተኝነትን የሚያላብሱ ወታደራዊ አቅምን የሚያሥጨብጡ የሚያሰለጥኑ አሰልጣኞች ሁለንተናዊ ብቃትን የተላበሱና የተመረጡ አቅም ፈጣሪ አቅም ያላቸው በዘመኑ የውጊያ ጥበብ ወታደራዊ አስተሳሰብ ላይ የረቀቁ ቴክኒኮችን እና ታክቲኮችን በብቃት በማስጨበጥ አሰልጣኞች አሥተዋፇቸው ከፍተኛ ነው፡፡

በከፍተኛ የዓላማ ፅናትና ቁርጠኝነት እንዲሁም በዲስፕሊን አክባሪነት የተገነቡ በሃገር ውስጥም ይሁን ከሀገር ውጪ የሚሰጣቸውን የልዩ ኦፕሬሽን ውጊያ ተልዕኮ በነፍስ ወከፍ እና በቡድን በላቀ የጀግንነት ውጤት ተልዕኳቸውን የሚወጡ የልዩ ኃይል ፀረ ሽብር ወታደሮችን በማሠልጠን ማሰልጠኛ ማዕከሉ ኃላፊነቱን በሚገባ ተወጥቷል፡፡

ጠንካራ ሀገራዊ እና ተቋማዊ ዕምነት ያላቸው በማንኛውም ጊዜና ሁኔታ የሚሰጣቸውን የኮማንዶና አየር ወለድ ኃይል በብቃት መምራትና ግዳጃቸውን መወጣት የሚችሉ እንዲሁም መመሪያና ደንብና ጠንቅቀው ያወቁ በመመሪያ መፈጸምና ማስፈፀም የሚችሉ የበታች ሹም አመራሮችን ማፍራት ላይም ማሠልጠኛ ማዕከሉ ከፍተኛ ሥራ ሠርቷል፡፡

የኮማንዶና አየር ወለድ ማሠልጠኛ የክልል የፌዴራል እና ለሀገራችን ሠላም እውን መሆን የሚታትሩ የፀጥታ ሃይሎችን አሠልጥኖ በማብቃቱ ረገድ ከፍተኛ ሀገራዊ አሥተዋፆ ያለው ማሠልጠኛ ነው፡፡

ማሠልጠኛ ማዕከሉ ከአካባቢው ህብረተሠብና የመስተዳደር አካላት ጋር በማህበራዊ፣ በፀጥታ፣ በአካባቢ ልማትና በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ሥራዎች ላይ ተባብሮ በመስራት እና የተቸገሩ ወገኖችን አሥፈላጊውን ድጋፍ በማድረጉ ረገድ ማሠልጠኛ ማዕከሉ ለየት ያለ ተወዳጅ እንቅስቃሴ የሚያደርግ ነው ፡፡

በድምሩ የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ በአራቱም የሀገራችን ማዕዘናት በመንቀሳቀስ ለተፈጥሮ መሰናክሎች ሳይበገር በርሃውን፣ ውሀ ጥሙን፣ አስቸጋሪውን የእግር ጉዞ አልፎ ለሀገራችን ሰላምና ፈጣን ልማት በመስዋዕትነት የደመቀ ሕያው ታሪክ ያኖረ ዕዝ ሲሆን አሁንም አባላቱ በታላቅ ሀገራዊ ጀግንነት ተልዕኳቸውን በውጤት እየፈፀሙ ይገኛሉ፡፡ (የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት፣ ኤልያስ ባይለየኝ ፎቶግራፍ ሃይሉ ሉሌ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Politics Tagged With: endf, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule