
- የጉዞ ዕገዳ እንደ ተጣለባት ይነገራል
ከሰሞኑ የህወሓት የሥልጣን ሽኩቻ ጋር በተያያዘ የነደብረጽዮን ቡድን አዜብ መስፍንን ከማንኛውም የፓርቲ ሥልጣን ካገዳት በኋላ በቁም እስር ላይ እንደምትገኝ ለጎልጉል የደረሰው መረጃ ያመለክታል። የጉዞ ዕገዳም ተጥሎባታል።
ከህወሓት በተሰጠው መግለጫ ለመረዳት እንደሚቻለው የአዜብ ጉዳይ በዕገዳ ቆይቶ በቀጣይ የሚታይ ቢሆንም ዕገዳው በራሱ የቁም እስር እንደሆነ መረጃው ይጠቁማል። አዜብ የኤፈርት ዋና ኃላፊ እንደመሆኗ በቀጣይ ከዚያ ሥልጣኗ ጋር በተያያዘ ውሳኔ ቢሰጥ የሚያመጣው ተቀጣጣይ ውጤት እየታሰበበት ያለ ጉዳይ እንደሆነ የደረሰን መረጃ ያስረዳል። ከዚህ የቁም እስር ጋር በተያያዘ አዜብ የጉዞ ዕገዳ እንደተጣለባት ተጠቁሟል።
መለስ የሞተ ጊዜ የትግራይ ተገንጣይ ቡድን ዋና “ወንበዴ” የሆነው ስብሃት ነጋ “የግለሰብ ሌጋሲ የሚባል የለም፤ ሌጋሲ የድርጅት ነው” ባለው መሠረት ባሁኑ ጊዜ የመለስን “ሌጋሲ” በ“ስብሃት ሌጋሲ” ለመተካት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። የህወሓት ስብሰባ ሳይጠናቀቅ ለኤፈርት ቅርብ የሆኑት አዜብ መስፍንና በየነ ምክሩ መባረራቸው ይፋ መሆኑ የነስብሃት ቡድን የፖለቲካውን ሙቀት የሚለካበት መሣሪያ ሆኖ ተወስዷል። በቀጣይ ስብሃት ከኤፈርት ኃላፊነቱ ተነስቶ በአዜብ የተተካበትን የፖለቲካ ቁማር የሚበቀልበት ይሆናል እየተባለ ይጠበቃል። የፖለቲካውን መዘውር ለማጥበቅ የኢኮኖሚ ድጋፍ ስለሚያስፈልግ ኤፈርትን በስልት በቁጥጥር ሥር ማዋል የነስብሃት ቡድን ወሳኝ ሥራ ይሆናል። ከዚህ ጋር ተያይዞ አዜብን የሚጠብቃት የቁም ይሁን የቂሊንጦ እስር አብሮ የሚወሰን ይሆናል።
በባሏ ትግሬ የሆነችው አዜብ “ጎላ” መስፍን ባለፈው ከሚሚ ስብሃቱ ጋር ባደረገችው ቃለ ምልልስ ህወሓት ቢለቃት “ሃፍታም” እንደምትሆን የገለጸች ሲሆን ይህንንም “ሃፍት” ጉሊት በመቸርቸር መልሳ እንደምታገኘው መግልጽዋ አይዘነጋም። (ፎቶዎቹ ከማህበራዊ ገጾች የተገኙ ሲሆን ተቆራኝተው የተሠሩት በጎልጉል ነው)
ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።
1ኛ – ለአርስቱ የተጠቀማችሁበትን ፎቶ ወድጀዋለሁ በተለይም ቸርቻሪ የሆነቸው አዜብ መስፍንን ሳያት ሳቂን መቆጣጠር ነው ያቃተኝ።
የዓመቱ አስቂና አስደማሚ ፎቶ ብየዋለሁ እናመሥግናለን ጎልጉሎች።
2ኛ – በባላቸውም ሆነ በሚስቶቻው ትግሬ የሆኑ ግን ብዙ ናቸው – ወዳቂዋ እመቤት አዜብ ጎላ የመጀመሪይዋ ብትሆንም ቀጣዩ ደግሞ
ዶ/ር ፀጋዬ አራርሶ ሳይሆን አይቀርም። እንዲያውም ዶ/ር ፀጋይ አራርሶ ሲምልም ሁሉ ትግሬ ሚስቱን በማሰብ እስኪመስል “ትብለፅ
ትሙት እያለ መሆኑን በአካባቢው የሚገኙ ውስጥ አዋቂዎች ሹክ ብለውናል። ዓለም ተሹዓተ አለ ትግሬ ቂ ቂ ቂ ቂ
ሰዎች!! አራርሳ ስልጣን ላይ ተቆናጧል እንዴ?? ከሆነ ንገሩን!!!
Mr. Ezira:
Sometime we say thing that is not related in any way. Using the platform for personal advantage is not cool. The person you mentioned I know him closely and also from his participations in diaspora medias. Here we are talking about dictatorial politics, oppression of Melese mafia group and Azeb’s participation and share of politics and power. Please do not mix family life with ethnic politics There are a lot us who are intermarried across ethnic lines. I have two grown up kids from mixed marriage. I also come from the same mixed marriage as an Ethiopian. This has to do with, love, marriage and family. What Tsegay ሲምልም ሁሉ ትግሬ ሚስቱን በማሰብ እስኪመስል “ትብለፅ is only a sign of love and no more than that. This reminds me Abera Mola’s song with kirar called Tizita where he talks about the lyrics and says, no body in the world swears by his lover except in this country (Ethiopia) and he gives example of Almaz Timut, Abera yimut and I can add Tibeleth Timut . In a place where I was born and raised this is very common sign of love and family. Mr Ezira, please put your politics aside and say something serious and important and if you do not have, it is better not to . I am not hear to defend Tsegay he is very very capable to do, but I can not tolerate a hurtful, hateful comments that absolutely useless for what we are discussing here. We are here to see something useful that takes us out from the tyranny of TPLF to a free and democratic Ethiopia. Please reserve your self from comments that hurt individuals and also divide us more than bring us closer.