• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አዜብ መስፍን በቁም እስር ላይ ነች

November 28, 2017 11:32 pm by Editor 3 Comments

  • የጉዞ ዕገዳ እንደ ተጣለባት ይነገራል

ከሰሞኑ የህወሓት የሥልጣን ሽኩቻ ጋር በተያያዘ የነደብረጽዮን ቡድን አዜብ መስፍንን ከማንኛውም የፓርቲ ሥልጣን ካገዳት በኋላ በቁም እስር ላይ እንደምትገኝ ለጎልጉል የደረሰው መረጃ ያመለክታል። የጉዞ ዕገዳም ተጥሎባታል።

ከህወሓት በተሰጠው መግለጫ ለመረዳት እንደሚቻለው የአዜብ ጉዳይ በዕገዳ ቆይቶ በቀጣይ የሚታይ ቢሆንም ዕገዳው በራሱ የቁም እስር እንደሆነ መረጃው ይጠቁማል። አዜብ የኤፈርት ዋና ኃላፊ እንደመሆኗ በቀጣይ ከዚያ ሥልጣኗ ጋር በተያያዘ ውሳኔ ቢሰጥ የሚያመጣው ተቀጣጣይ ውጤት እየታሰበበት ያለ ጉዳይ እንደሆነ የደረሰን መረጃ ያስረዳል። ከዚህ የቁም እስር ጋር በተያያዘ አዜብ የጉዞ ዕገዳ እንደተጣለባት ተጠቁሟል።

መለስ የሞተ ጊዜ የትግራይ ተገንጣይ ቡድን ዋና “ወንበዴ” የሆነው ስብሃት ነጋ “የግለሰብ ሌጋሲ የሚባል የለም፤ ሌጋሲ የድርጅት ነው” ባለው መሠረት ባሁኑ ጊዜ የመለስን “ሌጋሲ” በ“ስብሃት ሌጋሲ” ለመተካት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። የህወሓት ስብሰባ ሳይጠናቀቅ ለኤፈርት ቅርብ የሆኑት አዜብ መስፍንና በየነ ምክሩ መባረራቸው ይፋ መሆኑ የነስብሃት ቡድን የፖለቲካውን ሙቀት የሚለካበት መሣሪያ ሆኖ ተወስዷል። በቀጣይ ስብሃት ከኤፈርት ኃላፊነቱ ተነስቶ በአዜብ የተተካበትን የፖለቲካ ቁማር የሚበቀልበት ይሆናል እየተባለ ይጠበቃል። የፖለቲካውን መዘውር ለማጥበቅ የኢኮኖሚ ድጋፍ ስለሚያስፈልግ ኤፈርትን በስልት በቁጥጥር ሥር ማዋል የነስብሃት ቡድን ወሳኝ ሥራ ይሆናል። ከዚህ ጋር ተያይዞ አዜብን የሚጠብቃት የቁም ይሁን የቂሊንጦ እስር አብሮ የሚወሰን ይሆናል።

በባሏ ትግሬ የሆነችው አዜብ “ጎላ” መስፍን ባለፈው ከሚሚ ስብሃቱ ጋር ባደረገችው ቃለ ምልልስ ህወሓት ቢለቃት “ሃፍታም” እንደምትሆን የገለጸች ሲሆን ይህንንም “ሃፍት” ጉሊት በመቸርቸር መልሳ እንደምታገኘው መግልጽዋ አይዘነጋም። (ፎቶዎቹ ከማህበራዊ ገጾች የተገኙ ሲሆን ተቆራኝተው የተሠሩት በጎልጉል ነው)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Ezira says

    November 29, 2017 11:36 pm at 11:36 pm

    1ኛ – ለአርስቱ የተጠቀማችሁበትን ፎቶ ወድጀዋለሁ በተለይም ቸርቻሪ የሆነቸው አዜብ መስፍንን ሳያት ሳቂን መቆጣጠር ነው ያቃተኝ።
    የዓመቱ አስቂና አስደማሚ ፎቶ ብየዋለሁ እናመሥግናለን ጎልጉሎች።
    2ኛ – በባላቸውም ሆነ በሚስቶቻው ትግሬ የሆኑ ግን ብዙ ናቸው – ወዳቂዋ እመቤት አዜብ ጎላ የመጀመሪይዋ ብትሆንም ቀጣዩ ደግሞ
    ዶ/ር ፀጋዬ አራርሶ ሳይሆን አይቀርም። እንዲያውም ዶ/ር ፀጋይ አራርሶ ሲምልም ሁሉ ትግሬ ሚስቱን በማሰብ እስኪመስል “ትብለፅ
    ትሙት እያለ መሆኑን በአካባቢው የሚገኙ ውስጥ አዋቂዎች ሹክ ብለውናል። ዓለም ተሹዓተ አለ ትግሬ ቂ ቂ ቂ ቂ

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    December 1, 2017 02:24 am at 2:24 am

    ሰዎች!! አራርሳ ስልጣን ላይ ተቆናጧል እንዴ?? ከሆነ ንገሩን!!!

    Reply
  3. aradw says

    December 1, 2017 08:24 pm at 8:24 pm

    Mr. Ezira:

    Sometime we say thing that is not related in any way. Using the platform for personal advantage is not cool. The person you mentioned I know him closely and also from his participations in diaspora medias. Here we are talking about dictatorial politics, oppression of Melese mafia group and Azeb’s participation and share of politics and power. Please do not mix family life with ethnic politics There are a lot us who are intermarried across ethnic lines. I have two grown up kids from mixed marriage. I also come from the same mixed marriage as an Ethiopian. This has to do with, love, marriage and family. What Tsegay ሲምልም ሁሉ ትግሬ ሚስቱን በማሰብ እስኪመስል “ትብለፅ is only a sign of love and no more than that. This reminds me Abera Mola’s song with kirar called Tizita where he talks about the lyrics and says, no body in the world swears by his lover except in this country (Ethiopia) and he gives example of Almaz Timut, Abera yimut and I can add Tibeleth Timut . In a place where I was born and raised this is very common sign of love and family. Mr Ezira, please put your politics aside and say something serious and important and if you do not have, it is better not to . I am not hear to defend Tsegay he is very very capable to do, but I can not tolerate a hurtful, hateful comments that absolutely useless for what we are discussing here. We are here to see something useful that takes us out from the tyranny of TPLF to a free and democratic Ethiopia. Please reserve your self from comments that hurt individuals and also divide us more than bring us closer.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule