• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የመለስ “ሌጋሲ” በአዜብ መታገድ መቃብር ገባ

November 28, 2017 02:43 am by Editor 4 Comments

  • ህወሓትን ለመምራት ደብረጽዮን፣ ዓለም፣ ጌታቸውና ፈትለወርቅ ታጭተዋል

እርስበርሱ ሲነታረክ የቆየው የህወሓት ግምገማ አባይ ወልዱን በማባረርና አዜብ መስፍንን በማገድ እርምጃ መውሰዱ ታውቋል። እነደብረጽዮን የሚመሩት የማጽዳት ዘመቻ በመለስ “ሌጋሲ” ላይ አብሮ እርምጃ ወስዷል። የመሪነቱን ቦታ ፈትለወርቅ፣ ደብረጽዮን፣ ጌታቸውና ዓለም እየተፎካከሩበት ነው ተብሏል።

አፍቃሪ ህወሓትና የህወሓት ልሳን ከሆኑ የዜና ምንጮች በቀረበው መረጃ መሠረት ሰሞኑን በግምገማ እርስበርሱ ሊበላላ ደርሶ የነበረው የህወሓት ግምገማ “ቆራጥ” እርምጃዎችን ወስዷል። በዚህም መሠረት በመለስ ዜናዊ ምትክ የ“ወንበዴ” ድርጅቱ ኃላፊ ሆኖ ሲሠራ የነበረው አባይ ወልዱ ከሊቀመንበርና ሌሎች ከፍተኛ ኃላፊነቶች ተወግዶ በተራ አባልነት እንዲቀጥል ተወስኖበታል።

ከአባይ መሰናበት በተጨማሪ “አዜብን መንካት የመለስ ሌጋሲን አደጋ ላይ መጣል ነው” በሚል እንድምታ በግዱ ለአዜብ ሲያጎነብስ የነበረው ትግራይን ለመገንጠል የተቋቋመው ቡድን አዜብን ከከፍተኛ ኃላፊነቷ አንስቷታል። ከቀናት በፊት አዜብንና ተላላኪዎቿን ለመቀርጠፍ ግምገማው ሲጣደፍ በነበረበት ጊዜ አዜብ መስፍን ስብሰባውን ረግጣ መውጣቷ ይታወቃል። ለዚህ ድርጊቷ በተደጋጋሚ ይቅርታ ብትጠይቅም ሆነ ደብዳቤ ጽፋ ብታስገባም “ኃጢአቷን ካናዘዘ” በኋላ በዕገዳው ጸንቷል።

“ባለራዕዩ መሪ” እየተባለ ሲሞገስና ሲሞካሽ የኖረው መለስ በሙት መንፈስ አገሪቱን ሲመራ መቆየቱ የሚታወቅ ነው። ሞት እንደ ቡሽ ክዳን በድንገት ቢያስፈነጥረውም ህወሓት በእርሱ መንፈስ እመራለሁ ሲል አዜብም “አንዲት ሓሳብ ይዞ ወደ ምድር” የመጣውን ሙት ባሏን ከለላ በማድረግ ያሻትን ስትናገርና ስትከውን ላለፉት አምስት ዓመታት ቆይታለች።

መለስ ከመሞቱ 3ዓመት በፊት በአሜሪካ ከአውሮጵላን ለመውረድ ሲችገር

በህወሓት ነባር ወንበዴዎች ዘንድ በንቀት የምትታየው አዜብ ከመለስ ሞት በኋላ ከማንኛውም ኃላፊነት እንድትወገድ ሲሞከር ቆይቷል። ሆኖም እርሷን በሙስና ወይም በሌላ ሰበብ ማባረር በመለስ ውርስ (ሌጋሲ) ላይ ትልቅ ጥያቄ ያስነሳል በሚል ውሳኔው ተግባራዊ ሳይደረግ ቆይቷል። በሙስና ከተባረረች የሙስናው እፍታ ለመለስም ደርሷል የሚለው አስተሳሰብ የባለራዕዩን መሪ ስም የሚያጠለሽ ነው የሚል አስተያየት ሲሰጥበት ቆይቷል። በኪራይ ሰብሳቢነት ወይም በችሎታ፣ በአቅም ማነስ ወይም በአስተሳሰብ ደካማነት ወይም በሥልጣን መባለግ በሚሉ ሰበቦች ብትባረር ያለ ችሎታዋና ያለ አቅሟ ወደ ሥልጣን እንድትመጣ ያደረገውን መለስ አሁንም የሚያዋርድ ነው በሚል ጥርስ ሲነከስባት ሰንብቷል።

በህወሓት ጉዳይ ውስጥ አዋቂ ነን የሚሉ እንደሚናገሩት አዜብ መታገድ ብቻ ሳይሆን ሙሉ በሙሉ ከድርጅቱ ትባረራለች የሚል አስተያየት እየሰጡ ናቸው። ይህ በሚሆንበት ጊዜ ደግሞ ከእርሷ ጋር አብሮ የመለስ ሌጋሲ በዜሮ እንዳባዛ ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት ያሳስባሉ። በመሆኑም እስካሁን የአዜብን ጉዳይ በትዕግስት ሲያስታምም የቆየው ህወሓት አዜብ የምትባረረው ከመለስ ሞት በኋላ በፈጸመችው ስህተት መሆኑን በማጉላት የመለስን “ሌጋሲ” ለማዳን የፕሮፓጋንዳ ሥራ የመሥራት ዕቅድ ያስፈልጋል የሚሉ ወያኔዎች የሚሰጡት አስተያየት አብላጫነት እያገኘ መጥቷል።

አዜብን በማገድ፣ በየነ ምክሩንና አባይ ወልዱን በማባረር የቀጠለው የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት) ግምገማ በተባረሩት ምትክ አዳዲስ አባላትን ያስገባል። በዓለምአቀፋዊ የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ለተመዘገበው ድርጅት – ህወሓት – መሪ ይመርጣል። ሁለቱ የደኅንነትና የስለላ ማሽኖች ደብረጽዮን ገብረሚካኤልና ጌታቸው አሰፋ እንዲሁም ዓለም ገብረዋህድ ለመሪነት ቀዳሚ ተፎካካሪዎች እንደሆኑ የህወሓት ተላላኪዎች ቢናገሩም በበረሃ ስሟ “ሞንጆርኖ” እየተባለች የምትጠራው ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር ቀጣይዋ የህወሓት መሪ እንደምትሆን ስዩም ተሾመ ምንጮቼ አረጋግጠውልኛል በማለት በፌስቡክ ገጹ ላይ ዘግቧል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Alem says

    November 28, 2017 06:53 pm at 6:53 pm

    ውድ ጎልጉል፣
    የሚያሳዝነው፣ ህወሓት በአገራችን ዕጣ ብቸኛ ወሳኝ ሆኖ የሚያካሄደውን ስብሰባ ሌላው እንደ ተመጽዋች እጁን አጣምሮ መጠባበቁ ነው። ዛሬ ደግሞ አፍቃሬ ወያኔው ሪፖርተር፣ ምሑራን ወደ ኤርትራ ሄደው ሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት እንዲያደርጉ ህወሓት መፍቀዱን ገልጿል። ምሑራኑን የሚመሩት ሀብቶም እና መድሐኔ ናቸው። ትልቅ ቀልድ፣ የሰው ልክ የማያውቅ መንግሥት ገጥሞናል። የሥልጣን ጥመኛውና ሥራፈቱ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ደግሞ የኢትዮጵያ ደመኛ ኢሳይያስ የሥልጣን ኮርቻ ላይ ያፈናጥጠኛል ብሎ ተስፋ አድርጓል። ከሌንጮ ለታ፣ ከታምራት ላይኔ እንኳ መማር አልቻለም። ዶ/ር ብርሃኑ በ97 ምርጫ ህዝብ ተገልብጦ ወጥቶ እርሱ ግን ፈርጥጦ ከአገር ወጣ። ህወሓት ወዲያው የተበተነውን ወጣት ለቃቅሞ ኪሱ ከተተ። ከዚያን ወዲህ “ተቃዋሚ” ገለመሌ የሚለው ቋንቋ ወጣቱን ቋቅ ብሎታል። የህወሓት ጥንካሬ የኛ ዝርክርክነትና ዓለማ ቢስነት ግልባጭ ነው። ሌላው አሳዛኝ ጉዳይ የድረገጾች የውሸት ናዳና ተስፋ ነው። ህወሓት ሊወድቅ ነው! ምሥጢሩን ይዘናል! የውሸት ተስፈኞች አድርጎናል። ስንት ዓመት ይህን ስንሰማ ኖርን፤ አንዱም እውን አልሆነም። እናንተ ግን ጎልጉላችሁ እውነቱን ከመናገር ችላ አትበሉ።

    Reply
    • Editor says

      November 29, 2017 09:30 am at 9:30 am

      ሰላም Alem

      ለላኩልን መልዕክት እናመሰግናለን።

      በተለይ “… ዛሬ ደግሞ አፍቃሬ ወያኔው ሪፖርተር፣ ምሑራን ወደ ኤርትራ ሄደው ሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት እንዲያደርጉ ህወሓት መፍቀዱን ገልጿል። ምሑራኑን የሚመሩት ሀብቶም እና መድሐኔ ናቸው …” ባሉት ጉዳይ ላይ እየሠራንበት ነው በቀጣይ የምናቀርበው የዜና ዘገባ ይሆናል።

      ከአክብሮት ሰላምታ ጋር

      የጎልጉል አርታኢ

      Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    November 28, 2017 10:48 pm at 10:48 pm

    አይ ዓዜብ!ዓዜብ!የመለስ ሚስት! ዓዜብ!
    ልክሰስሽ!? አሁን!?ሰው እስኪታዘብ?
    ላዋርድሽ!? ቂሊንጦ ላስገባሽ?ላስጠብቅሽ በዘብ?

    አየሽ! ዓዜብ!ዓዜብ!
    ላሸክምሽ! የውርደትሽን ቀለብ?
    ባልሽና አንቺ ከጠላት ወግኖ መረባረብ?
    እሱ ሲሞት አንቺ በማደብ!
    በመደበቅ! ዱካ አጥፍቶ መረባረብ?
    ልክተትሽ?ከሴ?ዓዜብ?

    ነውር ነው!! በስርቆት ተለክፈሽ!
    ይባስ ብለሽ አይናውጣ ሆነሽ!እኔን ልታጠፊ ሞክረሽ!
    ልክተትሽ? በተራ ስርቆት ላስገባሽ?
    ውነት ቅን ነበር ባልሽ?
    እኛን ጨፍልቆ አንቺን ሲያሻሽ!
    በስርቆት ወንጀል ላስገባሽ?
    እስቲ ማን ዋቢ ይሁንሽ?
    ቢቀር ቢቀር ስድስት ወር ታጪያለሽ?
    ነውር ነው! ነውር ነው! ያንቺና የባልሽ!
    መልስ ስጪኝና ላሳይሽ!
    ተቀመጪ ቅሌት ተከናንበሽ!
    ዓዜብ! ዓዜብ!አበቃልሽ!የተራ እንኳን አባልነትሽ!
    ዕድሜ ለሃይለ ማርያም ብለሽ!
    ተቀመጪ ከእንግዲህ በቃሽ!!
    ከእንግዲህ ስልጣን አይመርሽ!!

    Reply
  3. dergu temelese says

    November 29, 2017 11:07 am at 11:07 am

    የቀን ገቢው ሚሊዮን፣
    የወር ገቢው ቢሊዮን፣
    ከጫካ ሲመጣ ያልነበረው ስሙኒ፣
    ዛሬ ባለ ካምፓኒ፣
    ሎተሪ ያልወጣለት ውርስ የሌለው፣
    ይህን ሰው ማን ዕንበለው?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule