• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሃፍታም ምሆነው ሕወሃት ሲለቅቀኝ ነው!” አዜብ መስፍን

November 28, 2017 11:52 am by Editor Leave a Comment

  • የህወሃት ሽኩቻ አላባራም!

“ሃፍታም የምትሆነው ህወሃት ወይንም ኤፈርት ሲለቅቀኝ ብቻ ነው!” ብላ ከነገረችን ገና መንፈቅ እንኳ አልሞላም። ከጥልቅ ተሃድሶ እና ከመተካካት ቀጥሎ የተመሰከረለት የአዜብ ጎላ መሪ ቃል ነበረች። የመልቀቁን ጨዋታ ለኛ ተየት አድርጊያትና መሪርዋን ጽዋ ተጎንጪ ሲሉ እነሆ መርዶውን ነግረዋታል። ሂስዋን አልውጥም ብላ ከመቀሌ እንደፈረጠጠች በዚያው ቀርታለች። መቼም “መለስ የሞተው አሁን ነው!” ሳትል አትቀርም በልብዋ። የዛሚዋ ደላሊት እድል አትሰጣትም እንጂ፣ ይህንኑ የልብዋን ሃሳብ “ለሚወዳት ሕዝብ” ትተነፍሰው ነበር። ግን ምን ያደርጋል? የወደቀ ፈላጊ አይኖረውም። ቀልደኛይቱ የጎላ ልጅ፣ “ድሮስ ቢሆን ድሃን ማን ይወደዋል” ማለትዋ በፌዝ ቡክ ላይ አነበብን።

አዎ! አዜብ መስፍን ከታሰረችበት የህወሃት ጎራ አሁን ተለቅቃለች። ቃል እንደገባችውም የድህነትን በሽታ ከራስዋ ላይ የምታባርርበት ግዜ አሁን ነው። ጉልት ቁጭ ብላ ቸርችራ ሃብታም እንደምትሆን ታሳየናለች። ይህንን ስታደርግ ታዲያ የባለ ራዕዩን “ታላቁ መሪ” ፎቶ ከአጠገብዋ ማራቅዋን እንዳትዘነጋ። አንዲት ድሃ እናት ጉልት ተቀምጣ ውላ ልጆችዋን እንዴት እንደምታሳድግ በቃል ሳይሆን በተግባር ስታሳየን – ያኔ እናምናታለን። እርግጥ የፖለቲካ ሀ-ሁ በውል ሳይገባትና  ከአመራር እውቀት ነጻ ሆና እስካሁን መርታለች። የመኖርዋ ትርጉም የተቋጨው የመለስ ሚስት በመሆንዋ ብቻ ባገኘችው በዚሁ እድል ፈንታዋ ነበር። የአርባ ቀን እድልዋን በዜሮ እስካባዙባት እስከዛሬዋ ሰዓት በርግጥም ቀልዳብን ነበር።   

ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከህወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ መባረርዋ የባንክ ሂሳቧ ላይ አንዳች ሃሳብ አያመጣባትም። ከህወሃት የገንዘብ ክምችት ከሆነው ኤፈርት ያስወገድዋት ቀን ግን የተመኘችው ጉልትዋ ተቀምጣ ስትቸረችር እናያት ይሆናል። ለዚያም እድል ከሰጥዋት! ሰዎቹ ወገብዋ ላይ መቆማቸው እርግጥ መሆኑ የታወቀው የአድዋው ጸረ-ሙስና ቡድን የአዜብ ፋይሎችን አዋራ እያራገፈ መሆኑ ሲሰማ ነው። በነገራችን ላይ ከ 16 ዓመት በፊት መለስ ዜናዊ፣ ስብሰባ ረግጠው በወጡት በእነ አቶ ገብሩ አስራት፣ አረጋሽ አዳነ፣ ስዬ አብርሃ፣ ጀነራል ፃድቃን ገ/ተንሳኤ ላይ የወሰደው እርምጃ ነው አሁን በአዜብ ላይ የደረሰው። እነ ስዬ በወቅቱ አብዛኛ ድምጽ ቢኖራቸውም እንደወጡ በዚያው ቀሩ። ከጸረ-ሙስናው በትርም ሊያመልጡ አልትቻላቸውም ነበር። የሚገርመው፣ ያ ታሪክ መደገሙ ሳይሆን የቅጣት ዱላው በቀጭዋ አዜብ ላይ መዞሩ ነው።

ጎናቸው እየተመታ ያለው እነ ሳሞራ የኑስ አውቆ እንደተኛ ዝም ብለው አድፍጠዋል። እንደ መርዘኛ እባብ ራሱን ቀብሮ የመቀሌውን ድራማ መጨረሻ የሚጠብቀው ቡድን ዝምታም የአድዋውን ቡድን ስጋት ውስጥ መጣሉ ግልጽ ነው።

“የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ /ህወሓት/ ማዕከላዊ ኮሚቴ በድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ።” የሚለውን ዜና ሲያሰሙን ትልቅ ለውጥ የመጣ መስሎን ነበር። በሕዝብ ጫንቃ ላይ ለ27 አመታት ሸክም የሆኑት ታሰሩ የሚል ዝርዝር ስንጠብቅ ይልቁንም ስለ አዜብ እና ስለ ቦታ መቀያየር ይነግሩናል።

አድዋዎች ከመቀሌ፣ መቀሌዎች ከአዲግራት፣ አዲግራቶች ከኤርትራዎች… የሚያደርጉት የፍትጊያ ድራማ አሁንም መስመር አልያዘም። የድራማው ዦንራ ኮሜዲም ትራጀዲም ነው። በታንክ እና መትረየስ መታጀቡ ደግሞ ጦርነትም አስመስሎታል። በሴራ፤ ሽብር እና ብቀላ ዙርያ ባጠነጠነው በዚህ ማራቶን የአድዋዎቹ ጡንቻ ለግዜውም ቢሆን ፈርጥሞ፣ ሌሎቹን ሲያብጠለጥል፣ ያሻውን ሲያወርድና ያሻውን ደግሞ ሲሰቅል ከርሟል። የተነካው ወገንም የተኛ መስሎ ሹክሹክታውን  እያደመጠ ነው። ምን ይታወቃል የስብሃት ቡድን ገና የአሸናፊነት ድሉን ሳያጣጥም ሃዘን ይቀመጥ ይሆናል።

ሰሞናዊው የመቀሌ ፉክቻ፤ በሰባዎቹ የነበረውን የኡጋንዳ ድራማ ያስታውሰናል። ሚልተን ኦቦቴ እና ኢድ አሚን ዳዳ፤  ተባብረው፣ ተሰባብረው፣ በለስም ቀንቷቸው የስልጣን ማማ ላይ ጉብ እንዳሉ፣ ከበድ ያለ የኮንትሮባንድ ንግድ ላይ ነበር የተሰማሩ። የሃገሪቷን ወርቅና የዝሆን ጥርስ ሁለት ሆነው ጋጡት። ዘረፋው ላይ ምንም ጸብ አልነበረም። ችግሩ የመጣው  የሃብት ክፍፍሉ ላይ እንደደረሱ ነው። ከዚያ በኋላ አብረው መብላት አልቻሉምና ተለያዩ። ብሄራዊውን ጉዳይ ረሱትና። ግዜያቸውን የሚያጠፉት አንዱ ሌላውን ማጥፋት ላይ ሆነ። የታሪክ መዛግብት እንደሚለን ሁለቱ የሰው ጅቦች በመፈንቅለ መንግስት እየተገለባበጡ ሃገሪቱን በፈረቃ መግዛትን ያዙ። መተካካት!

“የኢትዮጵያን ችግር ሊፈቱ” መቀሌ ላይ የተሰበሰቡት ዱዶች ነገር እንደ አዲስ ማስገረሙ አልቀረም። የሚዘርፉት እነሱ፣ የሚገድሉት እነሱ፣ የሚተካኩት እነሱ፣ የሚታደሱት እነሱ፣ የሚገመግሙት እነሱ፣ የሚገመገሙትም እነሱ! ስለሆኑ  የኢትዮጵያ ጉዳይ የትግራይ ብሄረተኞች ጉዳይ ብቻ ነው ብለው ከደመደሙ ሰነባበቱ። የመቀሌውን ክስተት መተካካት እንበለው ወይንም መከካካት ግና ሃገሪቱ ለገባችበት ቀውስ ምንም ፋይዳ የለውም። የህወሀት ሊቀመንበርና የትግራይ ክልል ኘሬዝደንት የሆኑትን አቶ አባይ ወልዱን ከዚያ አንስቶ እዚያ ማስቀመጥ ለውጥ አይደለም። የኤፈርት ምክትል ሥራ አስፈፃሚ አቶ በየነ ምክሩ፣ ከፓርቲው ሥራ አስፈፃሚነት ወደ ማዕከላዊ ኮሚቴነት አባልነት ማዛወር እርምጃ ሊሆን አይችልም። ባልዋ በህይወት እያለ የቀለደችባቸው አዜብን መገፍተርም እንዲያው ከአህዮች እርግጫ አያልፍም። አህያ ለአህያ ቢራገጥ ደግሞ ጥርስ አይዋለቅም።

በዚህ ሁሉ መሃል ግን ቀረብ ብሎ የሚታይ ነገር አለ። መፍትሄ ያልተገኘለት ችግር፣ የማይታረቅ ቅራኔ፣ የማያባራ ሽኩቻ። …. (በፎቶው የሚታዩት አዜብ መስፍን፣ አባይ ወልዱና በየነ ምክሩ ናቸው – ፎቶው በጸሃፊው የተላከ ነው)

ክንፉ አሰፋ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule