• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሃፍታም ምሆነው ሕወሃት ሲለቅቀኝ ነው!” አዜብ መስፍን

November 28, 2017 11:52 am by Editor Leave a Comment

  • የህወሃት ሽኩቻ አላባራም!

“ሃፍታም የምትሆነው ህወሃት ወይንም ኤፈርት ሲለቅቀኝ ብቻ ነው!” ብላ ከነገረችን ገና መንፈቅ እንኳ አልሞላም። ከጥልቅ ተሃድሶ እና ከመተካካት ቀጥሎ የተመሰከረለት የአዜብ ጎላ መሪ ቃል ነበረች። የመልቀቁን ጨዋታ ለኛ ተየት አድርጊያትና መሪርዋን ጽዋ ተጎንጪ ሲሉ እነሆ መርዶውን ነግረዋታል። ሂስዋን አልውጥም ብላ ከመቀሌ እንደፈረጠጠች በዚያው ቀርታለች። መቼም “መለስ የሞተው አሁን ነው!” ሳትል አትቀርም በልብዋ። የዛሚዋ ደላሊት እድል አትሰጣትም እንጂ፣ ይህንኑ የልብዋን ሃሳብ “ለሚወዳት ሕዝብ” ትተነፍሰው ነበር። ግን ምን ያደርጋል? የወደቀ ፈላጊ አይኖረውም። ቀልደኛይቱ የጎላ ልጅ፣ “ድሮስ ቢሆን ድሃን ማን ይወደዋል” ማለትዋ በፌዝ ቡክ ላይ አነበብን።

አዎ! አዜብ መስፍን ከታሰረችበት የህወሃት ጎራ አሁን ተለቅቃለች። ቃል እንደገባችውም የድህነትን በሽታ ከራስዋ ላይ የምታባርርበት ግዜ አሁን ነው። ጉልት ቁጭ ብላ ቸርችራ ሃብታም እንደምትሆን ታሳየናለች። ይህንን ስታደርግ ታዲያ የባለ ራዕዩን “ታላቁ መሪ” ፎቶ ከአጠገብዋ ማራቅዋን እንዳትዘነጋ። አንዲት ድሃ እናት ጉልት ተቀምጣ ውላ ልጆችዋን እንዴት እንደምታሳድግ በቃል ሳይሆን በተግባር ስታሳየን – ያኔ እናምናታለን። እርግጥ የፖለቲካ ሀ-ሁ በውል ሳይገባትና  ከአመራር እውቀት ነጻ ሆና እስካሁን መርታለች። የመኖርዋ ትርጉም የተቋጨው የመለስ ሚስት በመሆንዋ ብቻ ባገኘችው በዚሁ እድል ፈንታዋ ነበር። የአርባ ቀን እድልዋን በዜሮ እስካባዙባት እስከዛሬዋ ሰዓት በርግጥም ቀልዳብን ነበር።   

ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከህወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ መባረርዋ የባንክ ሂሳቧ ላይ አንዳች ሃሳብ አያመጣባትም። ከህወሃት የገንዘብ ክምችት ከሆነው ኤፈርት ያስወገድዋት ቀን ግን የተመኘችው ጉልትዋ ተቀምጣ ስትቸረችር እናያት ይሆናል። ለዚያም እድል ከሰጥዋት! ሰዎቹ ወገብዋ ላይ መቆማቸው እርግጥ መሆኑ የታወቀው የአድዋው ጸረ-ሙስና ቡድን የአዜብ ፋይሎችን አዋራ እያራገፈ መሆኑ ሲሰማ ነው። በነገራችን ላይ ከ 16 ዓመት በፊት መለስ ዜናዊ፣ ስብሰባ ረግጠው በወጡት በእነ አቶ ገብሩ አስራት፣ አረጋሽ አዳነ፣ ስዬ አብርሃ፣ ጀነራል ፃድቃን ገ/ተንሳኤ ላይ የወሰደው እርምጃ ነው አሁን በአዜብ ላይ የደረሰው። እነ ስዬ በወቅቱ አብዛኛ ድምጽ ቢኖራቸውም እንደወጡ በዚያው ቀሩ። ከጸረ-ሙስናው በትርም ሊያመልጡ አልትቻላቸውም ነበር። የሚገርመው፣ ያ ታሪክ መደገሙ ሳይሆን የቅጣት ዱላው በቀጭዋ አዜብ ላይ መዞሩ ነው።

ጎናቸው እየተመታ ያለው እነ ሳሞራ የኑስ አውቆ እንደተኛ ዝም ብለው አድፍጠዋል። እንደ መርዘኛ እባብ ራሱን ቀብሮ የመቀሌውን ድራማ መጨረሻ የሚጠብቀው ቡድን ዝምታም የአድዋውን ቡድን ስጋት ውስጥ መጣሉ ግልጽ ነው።

“የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ /ህወሓት/ ማዕከላዊ ኮሚቴ በድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ።” የሚለውን ዜና ሲያሰሙን ትልቅ ለውጥ የመጣ መስሎን ነበር። በሕዝብ ጫንቃ ላይ ለ27 አመታት ሸክም የሆኑት ታሰሩ የሚል ዝርዝር ስንጠብቅ ይልቁንም ስለ አዜብ እና ስለ ቦታ መቀያየር ይነግሩናል።

አድዋዎች ከመቀሌ፣ መቀሌዎች ከአዲግራት፣ አዲግራቶች ከኤርትራዎች… የሚያደርጉት የፍትጊያ ድራማ አሁንም መስመር አልያዘም። የድራማው ዦንራ ኮሜዲም ትራጀዲም ነው። በታንክ እና መትረየስ መታጀቡ ደግሞ ጦርነትም አስመስሎታል። በሴራ፤ ሽብር እና ብቀላ ዙርያ ባጠነጠነው በዚህ ማራቶን የአድዋዎቹ ጡንቻ ለግዜውም ቢሆን ፈርጥሞ፣ ሌሎቹን ሲያብጠለጥል፣ ያሻውን ሲያወርድና ያሻውን ደግሞ ሲሰቅል ከርሟል። የተነካው ወገንም የተኛ መስሎ ሹክሹክታውን  እያደመጠ ነው። ምን ይታወቃል የስብሃት ቡድን ገና የአሸናፊነት ድሉን ሳያጣጥም ሃዘን ይቀመጥ ይሆናል።

ሰሞናዊው የመቀሌ ፉክቻ፤ በሰባዎቹ የነበረውን የኡጋንዳ ድራማ ያስታውሰናል። ሚልተን ኦቦቴ እና ኢድ አሚን ዳዳ፤  ተባብረው፣ ተሰባብረው፣ በለስም ቀንቷቸው የስልጣን ማማ ላይ ጉብ እንዳሉ፣ ከበድ ያለ የኮንትሮባንድ ንግድ ላይ ነበር የተሰማሩ። የሃገሪቷን ወርቅና የዝሆን ጥርስ ሁለት ሆነው ጋጡት። ዘረፋው ላይ ምንም ጸብ አልነበረም። ችግሩ የመጣው  የሃብት ክፍፍሉ ላይ እንደደረሱ ነው። ከዚያ በኋላ አብረው መብላት አልቻሉምና ተለያዩ። ብሄራዊውን ጉዳይ ረሱትና። ግዜያቸውን የሚያጠፉት አንዱ ሌላውን ማጥፋት ላይ ሆነ። የታሪክ መዛግብት እንደሚለን ሁለቱ የሰው ጅቦች በመፈንቅለ መንግስት እየተገለባበጡ ሃገሪቱን በፈረቃ መግዛትን ያዙ። መተካካት!

“የኢትዮጵያን ችግር ሊፈቱ” መቀሌ ላይ የተሰበሰቡት ዱዶች ነገር እንደ አዲስ ማስገረሙ አልቀረም። የሚዘርፉት እነሱ፣ የሚገድሉት እነሱ፣ የሚተካኩት እነሱ፣ የሚታደሱት እነሱ፣ የሚገመግሙት እነሱ፣ የሚገመገሙትም እነሱ! ስለሆኑ  የኢትዮጵያ ጉዳይ የትግራይ ብሄረተኞች ጉዳይ ብቻ ነው ብለው ከደመደሙ ሰነባበቱ። የመቀሌውን ክስተት መተካካት እንበለው ወይንም መከካካት ግና ሃገሪቱ ለገባችበት ቀውስ ምንም ፋይዳ የለውም። የህወሀት ሊቀመንበርና የትግራይ ክልል ኘሬዝደንት የሆኑትን አቶ አባይ ወልዱን ከዚያ አንስቶ እዚያ ማስቀመጥ ለውጥ አይደለም። የኤፈርት ምክትል ሥራ አስፈፃሚ አቶ በየነ ምክሩ፣ ከፓርቲው ሥራ አስፈፃሚነት ወደ ማዕከላዊ ኮሚቴነት አባልነት ማዛወር እርምጃ ሊሆን አይችልም። ባልዋ በህይወት እያለ የቀለደችባቸው አዜብን መገፍተርም እንዲያው ከአህዮች እርግጫ አያልፍም። አህያ ለአህያ ቢራገጥ ደግሞ ጥርስ አይዋለቅም።

በዚህ ሁሉ መሃል ግን ቀረብ ብሎ የሚታይ ነገር አለ። መፍትሄ ያልተገኘለት ችግር፣ የማይታረቅ ቅራኔ፣ የማያባራ ሽኩቻ። …. (በፎቶው የሚታዩት አዜብ መስፍን፣ አባይ ወልዱና በየነ ምክሩ ናቸው – ፎቶው በጸሃፊው የተላከ ነው)

ክንፉ አሰፋ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule