• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የህወሓት ፕሮግራም፤ የመለስ ሌጋሲ – ዜጎችን ማፈናቀል፤ ማጋደል!

September 17, 2017 11:12 pm by Editor 3 Comments

ገና ከመነሻው በበረሃ ያወጣው ፕሮግራሙ በግልጽ እንደሚያመለክተው የህወሓት ዋንኛ ዓላማ ኢትዮጵያን አዳክሞና በጎሣ ከፋፍሎ ትግራይን ታላቅ በማድረግ ሪፑብሊክ መመሥረት ነው። ባለፉት 26 ዓመታት ይህንን ለማሳካት በኢትዮጵያ ውስጥ ያልፈነቀለው የጎሳ ድንጋይ የለም፤ ያላጋጨው ሕዝብ፤ ያላጋደለው ወገን የለም፤ ትግራይን ሳይጨምር!

ሞት እንደ ቡሽ ክዳን ሳያስበው አስፈነጠረው እንጂ የመለስና ዋናዎቹ የህወሓት መሥራቾች  ዕቅድ ይህንኑ ለማሳካት እንደሆነ ሰሞኑን በተከታታይ በምናትመው የአቶ ገብረመድኅን ጽሁፍ በግልጽ የተቀመጠ ሐቅ ነው።

የወቅቱ የፍጅት ዓላማ ደግሞ ኦሮሞን ከሶማሊ ወገኖቹ ጋር በማጋጨት የአገዛዝ ዘመኑን ማራዘም፤ ሁለቱን ጎሣዎች በማይረሳ ቂምና ጥላቻ ውስጥ ማስገባት፤ ይህንንም እስካሁን በሌሎቹ ጎሣዎች መካከል ከፈጠረው ጥላቻና ቁርሾ ጋር ተዳምሮ የኢትዮጵያን ኅልውና አጥፍቶ የትግራይን የበላይነት ማስፈን ነው። ለዚህ ደግሞ የሚደግፉት ከሁሉም ጎሣዎች የተውጣጡ ጥቅም ያሰከራቸው ወሮበላ ጎረምሶች መኖራቸው የሚካድ አይደለም።

አሁንም ከተቀናጀ ኅብረት፤ አሁንም ትኩረት ሁሉ ህወሓትንና ማንነቱን ተረድቶ ከመዋጋት ያነሰ አስተሳሰብ እስከተያዘ ድረስ ውጤቱ ንጹሐንን ማስፈጀት ብቻ ነው የሚሆነው። የሐረርጌ ሙስሊም ኦሮሞና ሙስሊም የኢትዮጵያ ሶማሊ ሊፋጁበት የሚችሉበት ምንም ምክንያት የላቸውም። (ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ)

የሰሞኑን የህወሓት ግፍ በተመከለከተ የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ የዘገበውን ከዚህ በታች አስፍረናል።

በኦሮምያና በሶማሌ ክልሎች ወሰኖች ባሉ ወረዳዎች ውስጥ እየተካሄደ ካለው የጥቃት እርምጃዎችና ግጭቶች ጋር በተያያዙ ምክንያቶች ከተፈጠረው የፀጥታ ቀውስ ጋር ተያይዞ ከሰማሌ ክልል የተፈናቀሉ ከአርባ ሺህ እስከ ሃምሣ ሺህ የሚሆኑ የኦሮሞ ተፈናቃዮች ምሥራቅ ሃረርጌ መግባታቸውን የዞኑ አስተዳዳሪ ለቪኦኤ ገልፀዋል።

በሌላ በኩል ደግሞ ጭናቅሰን ውስጥ ዛሬ (አርብ) በተፈጠረ ግጭት የሦስት ሰው ሕይወት መጥፋቱ ተሰምቷል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከዚሁ የሁለቱ አጎራባች ክልሎች ቀውስ ጋር ተያይዞ ጎረቤት ሶማሌላንድ ውስጥ በስደት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ህይወት ያጠፋ ጥቃት እየተፈፀመባቸው መሆኑና ከፍተኛ ሥጋት ላይ እንደሚገኙ እየገለፁ ናቸው።

ሃርጌሣ ላይ ሁለት ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ተገድለው አንደኛው ላይ ጉዳት እንደደረሰበት የሶማሊላንድ የፀጥታ ሚኒስትር ዴኤታ አስታውቀዋል።

ሶማሊያዊያኑ በኢትዮጵያዊያን ላይ ጥቃት እንዳያደርሱ ጥሪ ያስተላለፉት ሚኒስትር ዴኤታው ሞሐመድ ሙሣ ዴሬ ለኢትዮጵያዊያኑ ስደተኞች ጥበቃ እንዲያደርጉ ኃይሎቻቸውን ማዘዛቸውን አመልክተዋል።

በሌላ በኩል በሶማሌ ክልልና በኦሮሚያ አጎራባች አካባቢዎች ላይ ከተፈፀመው ጥቃቶችና እየታዩ ካሉ ግጭቶች ጋር በተያያዙ ሁከት አዘል ጥቃቶች አወዳይ ከተማ ውስጥ ቁጥሩ የበዛ ሰው ሕይወት መጥፋቱ ተገልጿል፡፡

ጥቃቱን ተከትሎም የሰፋ መፈናቀል ከጅጅጋ እና ሌሎችም የሶማሌ ክልል ከተሞች መከተሉ ተነግሯል።

ማክሰኞ ዕለት መስከረም 2/2010 ዓ.ም. አወዳይ ከተማ ውስጥ ሁከት የቀላቀለ ሰልፍ ያደረጉ ሰዎች ባደረሱት ጥቃት ሃምሣ ሰው መገደሉን የሶማሌ ክልል የመንግሥት ኮምዩኒኬሽንስ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢድሪስ ኢስማኤል ለቪኦኤ የገለፁ ሲሆን የኦሮሚያ ክልል አቻቸው አቶ አዲሱ አረጋ ግን አድራጎቱ መፈፀሙን አረጋግጠው የተገደለው ሰው ቁጥር ግን 18 መሆኑን ከመካከላቸውም 12ቱ የሶማሌ ተወላጆች ስድስቱ የኦሮሞ ጃርሶ ጎሣ አባላት መሆናቸውን አመልክተዋል፡፡

በተፈፀመው ሁኔታ የኦሮሚያ ክልል መንግሥት እንደሚያዝን ቃል አቀባዩ ጠቁመው ወደ ሁለት መቶ የሚሆኑ በጥቃቱ ላይ ተሣትፈዋል የተባሉ ሰዎች በቁጥጥር ሥር ውለው ጉዳዩ እየተጣራ መሆንን አመልክተዋል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ ይህንኑ የአወዳይ ጥቃት ተከትሎ ከሶማሌ ክልል ዋና ከተማ ጂጂጋ ከ21 ሺህ በላይ ሰው ተፈናቅሎ ጭናቅሰን፣ ባቢሌና ሐረር ከተሞች ውስጥ የተጠለሉ መሆናቸውን ያነጋገርናቸው ተፈናቃዮችና የኦሮሚያ ክልል ቃል አቀባይ አቶ አዲሱ አረጋ አመልክተዋል፡፡

ስለዚህ የመፈናቀል ጉዳይ ምላሽ የሰጡት የሶማሌ ክልል ቃል አቀባይ አቶ ኢድሪስ ኢስማኤል ሶማሌ ክልል ውስጥ የሌላ የማንም ብሄር ብሄረሰብ አባል የሆነ ነዋሪ አንድም አለመነካቱንና ሰዎቹ እየወጡ ያሉት በፈቃዳቸው ነው ቢሉም ያነጋገርናቸው ተፈናቃዮች ግን የምንፈርመው ተገድደን እንጂ መውጣት ፈልገን አይደለም ብለዋል።

እንዲያውም የልዩ ፖሊስ አባላት ቤት ለቤት እየዞሩ ትዕዛዝ እንደሰጧቸውና መጠጊያ ፍለጋ ሸሽተው በገቡባቸው የጦር ካምፖች ውስጥ ሁሉ ሳይቀር የደበደቧቸው መሆኑን፤ የተገደሉ ሁለት ሰዎችን በሸራ ጠቅልለው ሲወስዷቸው ማየታቸውን አንድ ተፈናቃይ ተናግረዋል።

አቶ ኢድሪስ በሰጡት ተጨማሪ መረጃ በአስራ አንድ የሶማሌ ወረዳዎች አካባቢዎች ውስጥ በተሠነዘሩ ጥቃቶች እስካሁን የሁለት መቶ አስራ ሦስት ሰው ህይወት መጥፋቱንና አርባ አንድ ሰው መቁሰሉን ገልጸዋል።

ጥቃቶቹን በኦሮሚያ ወረዳዎች ላይ እያደረሰ ያለው የሶማሌ ክልል ልዩ ፖሊስ ነው መባሉንም አቶ ኢድሪስ አስተባብለው የኦሮሚያን ከፍተኛ አመራር አባላት የዘር ፍጅት በመምራት ወንጅለዋል።

የኦሮሚያ ክልል ቃል አቀባይ ይህንን ክሥ የሶማሌ ክልላዊ መንግሥት አቋም ነው ብለው እንደማያምኑ ጠቁመው “የራሳቸውን ጥፋት ለመሸፋፈን የሚሉት፣ ኃላፊነት የጎደለውና ከአቶ ኢድሪስ የአቅም ብቃት ማነስ የመነጨ ነው” ሲሉ አጣጥለውታል።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    September 18, 2017 12:42 am at 12:42 am

    መለስ ከመነሻው ገና ከጅምሩ
    ህገ መንግስት ነድፎ ነበር ላገራችንና ላገሩ
    ግን ቆየት ብሎ ሰንብቶ
    በዚያው ባቋቋመው ፓርላማ ሰግቶ
    ሌላውን ትጥቅ አስፈትቶ
    እሱ ታጥቆ ታጅቦ ዝቶ
    እየመረጠ አስሮ አንገላቶ
    ማስፈራራትን ተያያዘው
    የፓርላማ አባላቱም ለጉድ አለው
    ግን እኮ አልቆየም ፈጣሪ ከረበተው
    ማን ተካው? ማነው ስሙ?
    የመንግስቱ አባት ነው ደሙ??
    የታጠቀው ሰራዊታችን
    የህገ መንግስቱ አለኝታችን
    የምንኮራበት ዋስትናችን
    እንጂ መች እንደ መንግስቱ
    ሰራዊት ዘራፍ ባይ በየታቦቱ
    የሻብያ የወያኔ ራቱ
    አላማየለሽ ባለኮተቱ!
    ለህዝብ የቆመ ከመሰረቱ
    ኧረ ወዲያ! ታዲያ እንደ መንግስቱ??
    የህገ መንግስታችን አለኝታ!
    የማንጠራጠር ላንዳፍታ!
    ለሁሉም ብሄር እፎይታ!
    ታሪክ ሰሪ ባንዳፍታ!
    የህዝባችን አለኝታ!!

    Reply
  2. አለም says

    September 18, 2017 05:11 pm at 5:11 pm

    ውድ ጎልጉል፣
    የጋዜጠኛነት ሙያ አክብራችሁ ርዕሠ አንቀጽ ስለምትጽፉና አስተያየቶችን ስለምታሰተናግዱ በቅድሚያ ላመስግናችሁ። ከላይ የሚታየው ጠመንጃ ያነገቡ ሕጻናት ፎቶ፣ ህወሓት ተተኪውን በነፍሰ ገዳይነት እያሠለጠነ ለመሆኑ መረጃ ነው። የረጅም ጊዜ እቅድ ስለያዘ የአገር ውስጡን ሚድያ ተቆጣጥሮታል፤ አሜሪካኖችን በሽብርተኞች ምክንያት አግባብቶ በገዛ ሕዝቡ ላይ የስለላ መረብ ዘርግተውለታል። አሁን ደግሞ የአልጀዚራ አዲስ አበባ ቢሮ ኃላፊ ሆኖ ኤርትራዊ መሐመድ ጠሃ ተሹሟል፤ እዚህ ጠቁም http://awate.com/tewekel-manages-the-new-al-jazeera-office-in-addis-ababa/ [ስብሃት ነጋ ይታይሃል?]። መሐመድ ጠሃ ቀደም ሲል የቱርክ ዜና አገልግሎት አናዶሉ ኃላፊ ነበር [ከላይ ፎቶውን ተመልከት]። የህወሓት አባላት በዓለም አቀፍ ድርጅቶች ውስጥ ተሠግስገዋል። ቴድሮስ አድሃኖም በዓለም ጤና ድርጅት፣ ሙሉ ቀጸላ፣ መሐሪ ታደሰ፣ ሐዲስ ታደሰ፣ ሙሉጌታ ገ/ሕይወት፣ ወዘተ ወዘተ። ሥራዬ ብለህ ብትከታተል የተዘረጋውን መረብ ስፋት ማየት ትችላለህ። የሚያሳዝነው ዶ/ር ብርሃኑ በሽብር ፈጣሪነቱ ዓለም የፈረጀውን ኢሳይያስን [ያውም የተመሰከረለት የኢትዮጵያ ጠላት] መጠጋቱ ነው። ትልቅ ሥራ ያለው በሚድያ ሆኖ ሳለ የጦር አመራሩን ኢሳይያስ ይዞለት ነገ ሥልጣን እይዛለሁ የማለቱ ጅልነት ያሳዝናል። ትልቁ ጉዳይ አሜሪካኖችን እንግሊዞችን አውሮጳን በምድራችን ህወሓት እያደረሰ ያለውን ግፍና ምዝበራ ማሳመን ሲሆን፣ በእነርሱ ድጋፍ የቆመን መንግሥት ያለእነርሱ ድጋፍ እዋጋለሁ ማለት ቂልነት ነው።

    Reply
  3. Tesfa says

    September 22, 2017 04:00 pm at 4:00 pm

    ወያኔ ያልገባበት ቀዳዳ የለም። በአሜሪካ ሃገር ውስጥ ደም ያፈሰሱና ያፋሰሱ ያለምንም ፍርሃት እንደሚኖሩ የታወቀ ነው። በኬኒያ/በየመን/ በሱዳን/በግብጽና በሌሎችም የአፍሪቃ ሃገሮች ወያኔ በተላላኪዎቹ በኩል ጉቦ በመስጠትና በማባበል ስደተኞችን ያተራምሳል፤ ይገድላል፤ ሲሳካለትም አፍኖ ሃገርቤት ይወስዳል። ከተዘረፈው የሃገር አንጡራ ሃብት ለወያኔ ደጋፊዎች የነዳጅ ማደያ፤ ቤት፤ የምግብ ቤት፤ የመኖሪያ ቤት እየተገዛ እንደሚታደላቸው ድብቅና ሾልከው የወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
    በሃገር ቤት በወታደራዊው፤ በኢኮኖሚው መስክ ላዕላይና ታህታይ መዋቅሩን ወጥረው የያዙት የዚሁ መሰሪ አባላት ብቻ ናቸው። የአማራ፤ የኦሮሞ የደቡብ ክልል ተወካይና ተጠሪ የሚባሉት ተለጣፊ ድርጅቶች ሁሉ የሚበላ ተመልካች ናቸው። ለሃገርም ለወገናቸውም የማይጠቅሙ የወያኔ ጀሌዎች። ወያኔ ለሃገር አንድነትና ብርታት አስቦ አያውቅም። ለትግራይ እንጂ! ህዝባችን አክ እንትፍ ብሎ የተፋቸው እነዚህ ወስላቶች በጸረ ሙስናና በጸረ ሽብርተኝነት ስም የሚያጉሯቸው ሁሉ ለሃገራቸው አንድነት የሚሰሩ፤ የዘር ፓለቲካ አሻፈረኝ ያሉና የወያኔን የዘረፋ ሚስጢር ያወጣሉ ተብለው የሚገመቱትን ነው። ሽብርተኛውና ዘራፊው ወያኔ ነው። የገበሬ ማሳና የሳር ጎጆ እያቃጠለ ረሃብ ሃገራችን ገባ በማለት የተራድኦ ድርጅቶችን የሚማጠን ጠኔ ልማዱ የሆነ ድርጅት ነው። ወያኔ አሁን በኦሮሞና በሶማሊያ የሃገሪቱ ዜጎች ላይ ለኮሰው እሳት በአርሲና በሌሎች የሃገሪቱ ክፍሎች ሃገራችሁ አይደለም አማራ ውጡ በማለት ከህጻን እስከ ሽማግሌ በቆንጪራ እየተገዳደሉ በገደል የተወረወሩትን ወገኖቻችን ትዝ ያስብላል። ወያኔ ፋሺሽታዊ ነው። ወያኔ የሰው ሞት አይገደውም። የሚያስበውና የሚተነፍሰው በዘሩ ዙሪያ በመሆኑ ለሌላው ወገናችን ሰላምን ተመኝቶ አያውቅም።
    በአንጻሩ ወያኔን እንቃወማለን የሚሉ ድርጅቶች (ግንቦት 7 ጨምሮ) በሻብያ ከለላ ሥር ሆነው ሃገርን ማዳን አይችሉም። ሻቢያ ሃገራችን ዛሬ ላለችበት አረንቋ ዋናው ተጠያቂ ነውና። ሻቢያና ወያኔ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው። ትላንት በሃገር ውስጥ በሚጽፋቸው ከፋፋይ መጻጽፍት ይታወቅ የነበረው የሻብያና የወያኔ የስለላ መረብ አገናኝ መኮነን ደራሲ ተስፋዬ ገ/አብ ዛሬ በአስመራ ዋና ስራው ሻቢያንና ወያኔ በሚስጢር አሰራር ማጣመር ነው። ለዛ ነበር የግንቦት 7 ታጋዮች ገና ወንዝ ሳይሻገሩ የተገደሉትና የተማረኩት። ለዛ ነው አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን በወያኔ ሊጠለፍ የበቃው። ሻቢያ ለኢትዮጵያ አንድነትና ህብረት ገዶት አያውቅም። ነጻ ወጣን፤ ድል አረግን እያለ በየአመቱ ከበሮ የሚመታው ሻቢያ የከበሮው ቃናና ግጥም በ 25 ዓመታት አልተቀየረም። የደንቆሮ ዘፈን መልሶ መልሶ እንዲሉ ያንኑ ወንድምና እህቱን የገደለበትን ጀግንነት እንደ ጀብድ ቆጥሮ የሃገሪቱን ባንዲራ በየጊዜው አካኪ ዘራፍ እያለ በሚረጋግጥበት ምድር ሻቢያን ታምኖ ማንም ድርጅት ወያኔን መታገልና ሃገራችንን ማዳን አይችልም። ከላይ አስተያየት ሰጪው እንዳሉት በፎቶና በመረጃ የተደገፈ የወያኔን ወንጀል በዝርዝር በማስቀመጥ የዓለም ህዝብ እንዲያውቀው ማድረጉ ጠበንጃ አንግቶ ጋራና ተራራን ከመውጣትና ከመውረድ የተሻለ ውጤት ያስገኛል እላለሁ። ከመካከላችን ተሰግስገው ለወያኔና ለሻቢያ ወሬ አቀባዮች የሆኑትን ለይቶ በምንኖርበት ከተማ ባለስልጣናት ማስታወቅ ተገቢ ነው። በበረሃ እያሉም ሆነ አሁን በህዝባችን ላይ ወንጀል ሰርተው የተደበቁን ሁሉ በመረጃ ክስ ልንመሰርትባቸው ይገባል። ህግ ባለበት ሃገር ወያኔና ተላላኪዎቹ ማፈር አለባቸው። በተረፈ በዘርና በጎሳ በተሰመረች ሃገር አንድ የአንድን አንገት ቢቀላ እግዚኦ አያሰኝም። ወያኔ ህዝባችንን ያመቻቸው ለእልቂት ነውና! በዚህ ግጥም ልሰናበት። የግጥሙ ምንጭ አላውቀውም። የራሴ ግን አይደለም፡
    በጊዜ የምንገባው ….. ማምሸቱን የተውነው፤
    ሌባ ወም ሰይጣን .. አይደል የፈራነው፤
    ማጅራት መቺዎች… ፅልመት ተገን አርገው
    ስላሉ ገዢዎች …. እነርሱን ፈርተን ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule