• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በእስክንድርና በዘመነ ሽኩቻ ፋኖ አንድ መሆን የማይችል ሆኗል – ኮሎኔል አሰግድ

July 22, 2024 01:54 pm by Editor 1 Comment

የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ዋና አዛዥ ኮሎኔል አሰግድ መኮንን እጁን ሰጠ

በአማራ ክልል በርካታ የታጣቂ ቡድን አባላት እና አመራሮች በመንግሥት የቀረበላቸውን የሰላም አማራጭ ተቀብለው ሰላማዊ ሕይወት እየመሩ መሆኑን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይል አስታውቋል፡፡

የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይሉ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች በአንዳንድ አካባቢዎች የሚታዩትን የፀጥታ ችግሮች በንግግርና በውይይት በመፍታት ዘላቂ ሰላም ለማስፈን በመንግሥት ለታጣቂ ቡድን አባላት እና አመራሮች  በተደጋጋሚ የሰላም አማራጮች ሲቀርቡ ቆይተዋል፡፡

ይሁንና በክልሎችም ሆነ በፌዴራል መንግሥት እየቀረበ ያለው የሰላም አማራጭ እንዳይሳካ እና ወደ መሬት እንዳይወርድ በተለይም ደግሞ ውጭ ሆነው በትግሉ ስም ጥቅም የሚያግበሰብሱ አንዳንድ ጽንፈኛ የዲያስፖራ አባላት ሰብስበው በሚልኩት ረብጣ ዶላር እንዲሁም ንፁሃንን አግተውና በጭካኔ ገድለው በሚጠይቁት እና በሚዘርፉት ገንዘብ ጥቅም የሰከሩ አንዳንድ የታጣቂ ቡድን አባላትና አመራሮች የሰላሙን አማራጭ ሲገፉ መቆየታቸውን የጋራ ግብረ- ኃይሉ መግለጫ  ያመላክታል፡፡

መግለጫው አያይዞም፤ ከጥቅም፣ ከጎጠኝነት እና ከገንዘብ ክፍፍል ጋር በተያያዘ በአብዛኛው በታጣቂ ቡድኑ አባላት እና በቡድኑ አመራሮች መካከል በሚፈጠር አተካራ እና የእርስ በእርስ መጠፋፋት የትግሉ ዓላማ ከመስመር ወጥቷል በሚል በራሳቸው በቡድኑ አባላት እና አመራሮችም ጭምር እየታየ እና እየተገለፀ መምጣቱ ክልሎችን ለግጭትና ለትርምስ እየዳረገ መሆኑን ጠቁሟል፡፡

ይህን ተከትሎም ይላል የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይሉ መግለጫ፤ ለመንግሥት እጃቸውን በመስጠት ወደ ሰላማዊ ህይወት እየተቀላቀሉ ያሉ የታጣቂ ቡድን አባላት እና አመራሮች ቁጥር ከግዜ ወደ ግዜ እየጨመረ መምጣቱን ገልጿል፡፡ በዛሬው ዕለትም በአማራ ክልል የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ዋና አዛዥ ኮሎኔል አሰግድ መኮንን ለመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች እጁን መስጠቱን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይሉ አስታውቋል፡፡

ግለሰቡ እጁን የሰጠው በፅንፈኛ ኃይሉ አመራሮች እና ታጣቂ ቡድን አባላት አማካኝነት በአማራ ክልል ህዝብ ላይ የሚፈፀሙ አሰቃቂ ግድያዎች፣ እገታዎች፣ አስገድዶ መድፈሮች፣ ለሕዝብ ጠቀሜታ የሚውሉ መሰረት ልማቶች ውድመት፣ አፈና እና ሌሎችም ኢ-ሰብአዊ ድርጊቶች እየተበራከቱ በመምጣታቸው እንደሆን በሰጠው ቃል ማረጋገጡን መግለጫው ጠቁሟል፡፡

የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አክሎም ኮሎኔል አሰግድ መኮንን እጁን የሰጠው ከቅርብ አጃቢው ገበየሁ ወንድማገኝ ከተባለ የቡድኑ አባል ጋር መሆኑን አስታውቆ፤ ወደ ሰላማዊ ህይወት ለመቀላቀላቸው ትግሉ በአማራ ክልል ህዝብ ስም ቢካሄድም የጠራ ጥያቄ የሌለውና ክልሉን ለምስቅልቅል እና ለልማት እጦት እየዳረገ ያለ እንዲሁም በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት ባሉ የተለያዩ ኃይሎች ፍላጎት ማስፈፀሚያ በመጠለፉ ምክንያት እንደሆነ መግለጹን መግለጫው ጠቁሟል፡፡

የጽንፈኛ ኃይሉን በሚመሩት በእስክንድር ነጋና በዘመነ ካሴ መካከል የተፈጠረው ሽኩቻ ህዝቡን የከፋ ዋጋ ከማስከፈል የዘለለ ወደ አንድ የሚመጣበት ዕድል ሊኖረው እንደማይችል መረዳቱንም ኮሎኔል አሰግድ ገልጿል፡፡  

በአማራ ክልል በተቀሰቀሰው ግጭት የክልሉ ህዝብ ለከፋ ማኀበራዊ፣ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ምስቅልቅል መዳረጉን የገለፀው ኮሎኔል አሰግድ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ ሊፈቱ ይገባል የሚል አቋም እንዳለው ተናግሯል፡፡ ተሳስተውና ተደናግረው ቡድኑን የተቀላቀሉ የፅነፈኛ ቡድኑ አባላትና አመራሮች መንግሥት ያቀረበውን የሰላም አማራጭ ተጠቅመው እጃቸውን እንዲሰጡም አሳስቧል፡፡

በመጨረሻም የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይል የሰላምን አማራጭ በመግፋት አሁንም በትጥቅ ትግል በሚገፉ ኃይሎች ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን እየገለፀ፤ በዚህ አጋጣሚ የሰላም አመራጭን ተቀብለው ለሚመጡ የታጣቂ ቡድን አመራሮች እና አባላት ግብረ ኃይሉ የሚያደርገውን ድጋፍና እና ትብብር  አጠናክሮ እንደሚቀጥል የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ለኢቢሲ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: amhara region, amhara terrorists, Aseged, Fake Fano, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    July 23, 2024 11:39 am at 11:39 am

    አሁን በዘመነና በእስክንድር ነጋ መካከል ባለው አለመስማማት የፋኖ ችግር እነርሱ ብቻ ናቸው ማለትም በአንድ እጅ እንደ ማጨብጨብ ነው። የፍልሚያው ሂደት ራሱ ለህዝብም እታገላለሁ ለሚለውም ዋጋ ቢስ ነው። ከተማ ያዝን፤ እከሌን ገደልን ወዘተ የሚለው ጥሩንባ ራሱ በራሱ እንደሚጮህ ጅራፍ ነው። የስንት የድሃ ልጆች ህይወት ተቀጥፎ ተያዘ የተባለው ከተማ ከሰዓታት በህዋላ ይለቀቃል። በምትኩ መከላከያ ሲገባ የሞተና የቆሰለበትን ለመበቀል አብልተሃል፤ አስጠልለሃል፤ ደግፈሃል በማለት ልክ እንዳለፈው ታሪካችን እንበለ ፍርድ ሰው ይረሽናል። ይህ እንግዲህ ሁለቱ ሃይሎች ሲፋለሙ የሞተውን የቆሰለውን፤ የፈረሰውን አይጨምርም። ታዲያ የቱ ላይ ነው ለአማራ ህዝብ ፋኖ የቆመው? ገድሎ ማስገደልና የህዝብን ሰላም ማደፍረስ የነጻነት ምልክት አይደለም። ይህ ሲባል ብልጽግና ምጡቅ ነው ሁሉ ነገሩ ሚዛናዊ ነው እያልኩ አይደለም። ብዙ የሚቀረው ነገር አለ? ግን በዘርና በቋንቋ እንዲሁም በክልል ተሸንሽና እኔ እበልጥ እኔ እበልጥ በማለት መንደሮች በሚፋለሙባት ምድር ሃገርን ማስተዳደርም ሆነ ያለፈውን ቁርሾ አሁን ካለው ገመና ጋር አቻችሎ ለህዝብ የሚጠቅም ነገር መስራት ቀላል አይደለም። የህዝቡ አስተሳሰብ ከጎሰኝነትና ከክልል እስካልወጣ ድረስ በዚህም በዚያም እያሳበብን መፋተጋችን አይቆምም። ለዚህ ነው ፋኖ ለሰላሙ ጥሩ ምላሽ በመስጠትና በመደራደር ወደ ሰላም እንዲመለስ በተደጋጋሚ የመከርነው። ጦርነት አውዳሚና ሃገር አፍራሽ ለመሆኑ በፊት ሃገር ከነበሩት በዚህም በዚያም አሁን የፍርስራሽ ክምር ከሚታይባቸው ሃገሮች መማር እንችላለን።
    ኮ/ሌ አሰገድ እጅም ሰጠ ወይም ተማረከ እሱ ወሬ አይደለም፡፤ ግን የጀመረው ፊልሚያ መንገድ የተሳሳተ የአማራን ዝህብ የሚያስጨርስ የእርስ በእርስ ውጊያ ነው በማለት ፋኖን መለየቱ በጎ ነገር ነው። ሌሎችም ይህኑ ተከትለው በሰላም ቢመለሱ ለአማራ ህዝብ እፎይታ ይሆናል ባይ ነኝ። የአማራ ክልል በሚባሉት ስፍራዎች ህግ የለም፤ ዘራፊው ብዙ ነው፤ ታግተህ ክፈል ስትባል አይ የለኝም ስትላቸው ቤ/ክ ሂደህ ለምነህም ቢሆን አምጣ የሚሉ ድርቡሾች እንደ አሸን ፈልተውባታል። ሰው በጠራራ ጸሃይ ይዘረፋል፤ ይገደላል፤ ይታፈናል። ባጭሩ ህግ የሚባል ነገር የለም። ይህ ደግሞ የገቢያ ግርግር ለሌባ ይመቻል እንዲሉ ሌባው ይሰርቃል፤ ደም የተቃባው ቀን ጠብቆ ደሜን መለስኩ ይላል፤ ሴቶች ያለውዴታ ይደፈራሉ፤ እረ ስንቱ ይወራል። ሂዶ ማየትና መታዘብ መልካም ይመስለኛል። ይህ ሁሉ የሆነው ሁሉ ታጣቂና ተኳሽ በመሆኑ ስርዓት አልበኝነት ከላይ እስከታች ሰፍኗል። ለዚህም ዋናው ምክንያት የፋኖና የብልጽግና ፊልሚያ ነው። በሃበሻ ምድር ግፍ መፍሰስ የሚቆመው መቼ ነው? ዛሬ ላይ ምጡቅ ሃሳብ ነው ብለህ ላይ ታች ያልክበት ጉዳይ ነገ የገለባ ክምር ሆኖ ብታገኘው ምን ይሰማሃል? የኢትዮጵያ ችግር ብዙ ነው። በሱዳን በኩል ያለው የእርስ በእርስ ውጊያ ወደ ኢትዮጵያ ሊዛመት የሚችልበት ሁኔታዎች አሉ፤ በሱማሊያ ጠብ የለሽ በዳቦ አይነት ከግብጽ፤ ከቱርክና ከኤርትራ ጋር በማበር ውጊያ ሊከፍቱ ይችላሉ። አሁን እርስ በእርሱ መርዝ እንደ ቀመሰ ውሻ የሚናከሰው ወያኔም መውጫ ኮሪዶር በሱዳን በኩል ካገኘ ከሱዳን አማጽያን ጋር ተዳብሎ በግብጽ እየተረዳ ውጊያ ሊጀምር ይችላል። ለዚህ ነው ተው ህዝባችን አታምክኑት ብዙ ፈተና የሚጠብቀው ህዝብ ነው። ባለችው ጊዜ እንኳን ሰርቶ ለፍቶና ግሮ ይኑር። አንተም ተው አንቺም ተይ ይሁን ነገሩ የምንለው። የብሄር ታጣቂዎች ለራስ ሲቆርሱ አያሳንሱ አይነቶች ስለሆኑ ለሃገርም ቆመናል ለሚሉትም ህዝብ አይጠቅሙም። በሰላም ለሰላም እንስራ። ሌላውን ሁሉ የብሄርተኞች ጥሩንባ የመርዶ ጥሩንባ እንደሆነ ሰምቶ ለለቅሶው አለመውጣት አዋቂነት ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule