• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በእስክንድርና በዘመነ ሽኩቻ ፋኖ አንድ መሆን የማይችል ሆኗል – ኮሎኔል አሰግድ

July 22, 2024 01:54 pm by Editor 1 Comment

የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ዋና አዛዥ ኮሎኔል አሰግድ መኮንን እጁን ሰጠ

በአማራ ክልል በርካታ የታጣቂ ቡድን አባላት እና አመራሮች በመንግሥት የቀረበላቸውን የሰላም አማራጭ ተቀብለው ሰላማዊ ሕይወት እየመሩ መሆኑን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይል አስታውቋል፡፡

የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይሉ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች በአንዳንድ አካባቢዎች የሚታዩትን የፀጥታ ችግሮች በንግግርና በውይይት በመፍታት ዘላቂ ሰላም ለማስፈን በመንግሥት ለታጣቂ ቡድን አባላት እና አመራሮች  በተደጋጋሚ የሰላም አማራጮች ሲቀርቡ ቆይተዋል፡፡

ይሁንና በክልሎችም ሆነ በፌዴራል መንግሥት እየቀረበ ያለው የሰላም አማራጭ እንዳይሳካ እና ወደ መሬት እንዳይወርድ በተለይም ደግሞ ውጭ ሆነው በትግሉ ስም ጥቅም የሚያግበሰብሱ አንዳንድ ጽንፈኛ የዲያስፖራ አባላት ሰብስበው በሚልኩት ረብጣ ዶላር እንዲሁም ንፁሃንን አግተውና በጭካኔ ገድለው በሚጠይቁት እና በሚዘርፉት ገንዘብ ጥቅም የሰከሩ አንዳንድ የታጣቂ ቡድን አባላትና አመራሮች የሰላሙን አማራጭ ሲገፉ መቆየታቸውን የጋራ ግብረ- ኃይሉ መግለጫ  ያመላክታል፡፡

መግለጫው አያይዞም፤ ከጥቅም፣ ከጎጠኝነት እና ከገንዘብ ክፍፍል ጋር በተያያዘ በአብዛኛው በታጣቂ ቡድኑ አባላት እና በቡድኑ አመራሮች መካከል በሚፈጠር አተካራ እና የእርስ በእርስ መጠፋፋት የትግሉ ዓላማ ከመስመር ወጥቷል በሚል በራሳቸው በቡድኑ አባላት እና አመራሮችም ጭምር እየታየ እና እየተገለፀ መምጣቱ ክልሎችን ለግጭትና ለትርምስ እየዳረገ መሆኑን ጠቁሟል፡፡

ይህን ተከትሎም ይላል የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይሉ መግለጫ፤ ለመንግሥት እጃቸውን በመስጠት ወደ ሰላማዊ ህይወት እየተቀላቀሉ ያሉ የታጣቂ ቡድን አባላት እና አመራሮች ቁጥር ከግዜ ወደ ግዜ እየጨመረ መምጣቱን ገልጿል፡፡ በዛሬው ዕለትም በአማራ ክልል የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ዋና አዛዥ ኮሎኔል አሰግድ መኮንን ለመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች እጁን መስጠቱን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይሉ አስታውቋል፡፡

ግለሰቡ እጁን የሰጠው በፅንፈኛ ኃይሉ አመራሮች እና ታጣቂ ቡድን አባላት አማካኝነት በአማራ ክልል ህዝብ ላይ የሚፈፀሙ አሰቃቂ ግድያዎች፣ እገታዎች፣ አስገድዶ መድፈሮች፣ ለሕዝብ ጠቀሜታ የሚውሉ መሰረት ልማቶች ውድመት፣ አፈና እና ሌሎችም ኢ-ሰብአዊ ድርጊቶች እየተበራከቱ በመምጣታቸው እንደሆን በሰጠው ቃል ማረጋገጡን መግለጫው ጠቁሟል፡፡

የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አክሎም ኮሎኔል አሰግድ መኮንን እጁን የሰጠው ከቅርብ አጃቢው ገበየሁ ወንድማገኝ ከተባለ የቡድኑ አባል ጋር መሆኑን አስታውቆ፤ ወደ ሰላማዊ ህይወት ለመቀላቀላቸው ትግሉ በአማራ ክልል ህዝብ ስም ቢካሄድም የጠራ ጥያቄ የሌለውና ክልሉን ለምስቅልቅል እና ለልማት እጦት እየዳረገ ያለ እንዲሁም በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት ባሉ የተለያዩ ኃይሎች ፍላጎት ማስፈፀሚያ በመጠለፉ ምክንያት እንደሆነ መግለጹን መግለጫው ጠቁሟል፡፡

የጽንፈኛ ኃይሉን በሚመሩት በእስክንድር ነጋና በዘመነ ካሴ መካከል የተፈጠረው ሽኩቻ ህዝቡን የከፋ ዋጋ ከማስከፈል የዘለለ ወደ አንድ የሚመጣበት ዕድል ሊኖረው እንደማይችል መረዳቱንም ኮሎኔል አሰግድ ገልጿል፡፡  

በአማራ ክልል በተቀሰቀሰው ግጭት የክልሉ ህዝብ ለከፋ ማኀበራዊ፣ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ምስቅልቅል መዳረጉን የገለፀው ኮሎኔል አሰግድ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ ሊፈቱ ይገባል የሚል አቋም እንዳለው ተናግሯል፡፡ ተሳስተውና ተደናግረው ቡድኑን የተቀላቀሉ የፅነፈኛ ቡድኑ አባላትና አመራሮች መንግሥት ያቀረበውን የሰላም አማራጭ ተጠቅመው እጃቸውን እንዲሰጡም አሳስቧል፡፡

በመጨረሻም የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይል የሰላምን አማራጭ በመግፋት አሁንም በትጥቅ ትግል በሚገፉ ኃይሎች ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን እየገለፀ፤ በዚህ አጋጣሚ የሰላም አመራጭን ተቀብለው ለሚመጡ የታጣቂ ቡድን አመራሮች እና አባላት ግብረ ኃይሉ የሚያደርገውን ድጋፍና እና ትብብር  አጠናክሮ እንደሚቀጥል የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ለኢቢሲ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: amhara region, amhara terrorists, Aseged, Fake Fano, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    July 23, 2024 11:39 am at 11:39 am

    አሁን በዘመነና በእስክንድር ነጋ መካከል ባለው አለመስማማት የፋኖ ችግር እነርሱ ብቻ ናቸው ማለትም በአንድ እጅ እንደ ማጨብጨብ ነው። የፍልሚያው ሂደት ራሱ ለህዝብም እታገላለሁ ለሚለውም ዋጋ ቢስ ነው። ከተማ ያዝን፤ እከሌን ገደልን ወዘተ የሚለው ጥሩንባ ራሱ በራሱ እንደሚጮህ ጅራፍ ነው። የስንት የድሃ ልጆች ህይወት ተቀጥፎ ተያዘ የተባለው ከተማ ከሰዓታት በህዋላ ይለቀቃል። በምትኩ መከላከያ ሲገባ የሞተና የቆሰለበትን ለመበቀል አብልተሃል፤ አስጠልለሃል፤ ደግፈሃል በማለት ልክ እንዳለፈው ታሪካችን እንበለ ፍርድ ሰው ይረሽናል። ይህ እንግዲህ ሁለቱ ሃይሎች ሲፋለሙ የሞተውን የቆሰለውን፤ የፈረሰውን አይጨምርም። ታዲያ የቱ ላይ ነው ለአማራ ህዝብ ፋኖ የቆመው? ገድሎ ማስገደልና የህዝብን ሰላም ማደፍረስ የነጻነት ምልክት አይደለም። ይህ ሲባል ብልጽግና ምጡቅ ነው ሁሉ ነገሩ ሚዛናዊ ነው እያልኩ አይደለም። ብዙ የሚቀረው ነገር አለ? ግን በዘርና በቋንቋ እንዲሁም በክልል ተሸንሽና እኔ እበልጥ እኔ እበልጥ በማለት መንደሮች በሚፋለሙባት ምድር ሃገርን ማስተዳደርም ሆነ ያለፈውን ቁርሾ አሁን ካለው ገመና ጋር አቻችሎ ለህዝብ የሚጠቅም ነገር መስራት ቀላል አይደለም። የህዝቡ አስተሳሰብ ከጎሰኝነትና ከክልል እስካልወጣ ድረስ በዚህም በዚያም እያሳበብን መፋተጋችን አይቆምም። ለዚህ ነው ፋኖ ለሰላሙ ጥሩ ምላሽ በመስጠትና በመደራደር ወደ ሰላም እንዲመለስ በተደጋጋሚ የመከርነው። ጦርነት አውዳሚና ሃገር አፍራሽ ለመሆኑ በፊት ሃገር ከነበሩት በዚህም በዚያም አሁን የፍርስራሽ ክምር ከሚታይባቸው ሃገሮች መማር እንችላለን።
    ኮ/ሌ አሰገድ እጅም ሰጠ ወይም ተማረከ እሱ ወሬ አይደለም፡፤ ግን የጀመረው ፊልሚያ መንገድ የተሳሳተ የአማራን ዝህብ የሚያስጨርስ የእርስ በእርስ ውጊያ ነው በማለት ፋኖን መለየቱ በጎ ነገር ነው። ሌሎችም ይህኑ ተከትለው በሰላም ቢመለሱ ለአማራ ህዝብ እፎይታ ይሆናል ባይ ነኝ። የአማራ ክልል በሚባሉት ስፍራዎች ህግ የለም፤ ዘራፊው ብዙ ነው፤ ታግተህ ክፈል ስትባል አይ የለኝም ስትላቸው ቤ/ክ ሂደህ ለምነህም ቢሆን አምጣ የሚሉ ድርቡሾች እንደ አሸን ፈልተውባታል። ሰው በጠራራ ጸሃይ ይዘረፋል፤ ይገደላል፤ ይታፈናል። ባጭሩ ህግ የሚባል ነገር የለም። ይህ ደግሞ የገቢያ ግርግር ለሌባ ይመቻል እንዲሉ ሌባው ይሰርቃል፤ ደም የተቃባው ቀን ጠብቆ ደሜን መለስኩ ይላል፤ ሴቶች ያለውዴታ ይደፈራሉ፤ እረ ስንቱ ይወራል። ሂዶ ማየትና መታዘብ መልካም ይመስለኛል። ይህ ሁሉ የሆነው ሁሉ ታጣቂና ተኳሽ በመሆኑ ስርዓት አልበኝነት ከላይ እስከታች ሰፍኗል። ለዚህም ዋናው ምክንያት የፋኖና የብልጽግና ፊልሚያ ነው። በሃበሻ ምድር ግፍ መፍሰስ የሚቆመው መቼ ነው? ዛሬ ላይ ምጡቅ ሃሳብ ነው ብለህ ላይ ታች ያልክበት ጉዳይ ነገ የገለባ ክምር ሆኖ ብታገኘው ምን ይሰማሃል? የኢትዮጵያ ችግር ብዙ ነው። በሱዳን በኩል ያለው የእርስ በእርስ ውጊያ ወደ ኢትዮጵያ ሊዛመት የሚችልበት ሁኔታዎች አሉ፤ በሱማሊያ ጠብ የለሽ በዳቦ አይነት ከግብጽ፤ ከቱርክና ከኤርትራ ጋር በማበር ውጊያ ሊከፍቱ ይችላሉ። አሁን እርስ በእርሱ መርዝ እንደ ቀመሰ ውሻ የሚናከሰው ወያኔም መውጫ ኮሪዶር በሱዳን በኩል ካገኘ ከሱዳን አማጽያን ጋር ተዳብሎ በግብጽ እየተረዳ ውጊያ ሊጀምር ይችላል። ለዚህ ነው ተው ህዝባችን አታምክኑት ብዙ ፈተና የሚጠብቀው ህዝብ ነው። ባለችው ጊዜ እንኳን ሰርቶ ለፍቶና ግሮ ይኑር። አንተም ተው አንቺም ተይ ይሁን ነገሩ የምንለው። የብሄር ታጣቂዎች ለራስ ሲቆርሱ አያሳንሱ አይነቶች ስለሆኑ ለሃገርም ቆመናል ለሚሉትም ህዝብ አይጠቅሙም። በሰላም ለሰላም እንስራ። ሌላውን ሁሉ የብሄርተኞች ጥሩንባ የመርዶ ጥሩንባ እንደሆነ ሰምቶ ለለቅሶው አለመውጣት አዋቂነት ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule