• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኤርሚያስ ለገሰ “የወያኔ የፕሮፖጋንዳ ሰራተኛ እያለ የለመደው የቁጥር ጫወታ አለቀቀውም”

March 17, 2021 09:54 pm by Editor 6 Comments

የቀድሞው ኢህአዴግ ካድሬዎች እና የህወሓት ጀነራሎች ሂሳብ አስተማሪው ኤርሚያስ ለገሰ ሆን ብሎ በቁጥር ሊጫወት ሞክሯል፡፡ አላማው ኢዜማ የክልል ምክር ቤት ወንበሮችን ሊያሸንፍ እንደማይችል አስመስሎ መሳል ነው፡፡ ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ ሆኖበት ነው፡፡

ኤርምያስ ሹመት አስቦ የለውጡ ደጋፊ የነበረ ጊዜ የተናገረው

የወያኔ የፕሮፖጋንዳ ሰራተኛ እያለ የለመደው የቁጥር ጫወታ አለቀቀውም፡፡ ምናልባት እንዲገባው ከዚህ በፊት ከነበረው የተቃዋሚዎች ዕጩዎች ቁጥር በ11% እድገት አሳይተናል እንበለው ይሆን?? ምንም እንኳን [ለእንደዚ አይነቱ አውቆ አበድ መፍትሄው] ንቆ መተው ቢሆንም ያቀረበውን የተንኮል መረጃ እንደ እውነት ሊወስዱ የሚችሉ ቅኖችን ከስህተት ለማዳን ዝርዝር መረጃውን ከዚህ በታች አቅርቤዋለሁ፡፡

ምርጫ የሚደረገው በዘጠኝ ክልሎች እና በሁለት ከተማ አስተዳደሮች ነው፡፡ ከዚህ ውስጥ፦

አዲስ_አበባ – ለክልልም ሆነ ለተወካዮች ምክር ቤት ሙሉ ዕጩዎችን ያስመዘገበው ብቸኛው ፓርቲ ኢዜማ ብቻ ነው፡፡ (ከአብን እና ከመኢአድ ጋር በጋር ዕጩዎችን አቅርቦ በስሙ የሚወዳደሩት ባልደራስም ሆነ ገዢው ፓርቲ ሙሉ ዕጩዎችን አላቀረቡም!)

ደቡብ ክልል – በፌደራልም ሆነ በክልል ምክር ቤት በሁሉም ወንበሮች እንወዳደራለን።

አማራ ክልል – በፌደራልም ሆነ በክልል ምክር ቤት ሙሉ በሙሉ እንወዳደራለን።

ጋምቤላ – ያለው የክልል ም/ቤት ወንበር 155 ነው በ114 የክልል ም/ቤት ተወዳዳሪ አቅርበናል የተቀሩት 41 ላይ በምዝገባ ችግር ስለተፈጠረብን ለምርጫ ቦርድ አቤቱታ አቅርበናል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሙሉ በሙሉ እንወዳደራለን።

ሀረሪ – 36 ወንበር ነው ያለው – በአንደኛው ምርጫ ክልል ሙሉ 18 ዕጩዎች ያቀረብን ሲሆን በሌላኛው ምርጫ ክልል ለአደሬ ብሄረሰብ ብቻ የተተወውን 9 ወንበር ጨምረን ዕጩ አቅርበናል የጎደለን 4 የክልል ምክር ቤት ዕጩ ብቻ ነው፡፡ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም ለአደሬ ብሔረሰብ የተተወውን ወንበር ጭምር ዕጩ አቅርበንበታል፡፡

ሲዳማ – ካሉት 19 ወረዳዎች በ16ቱ አብላጫውን ዕጩዎች አቅርበናል በተቀሩት በ3ቱም ዕጩ ብናዘጋጅም በምርጫ ቦርድ ምክኒያት አልተመዘገቡም ቅሬታ ለምርጫ ቦርድ አስገብተናል።

አፋር – በተቃዋሚዎች ታሪክ ለመጀመሪያ ግዜ ለክልል ምክር ቤት 50 ሲደመር 1 ወንበር ማሸነፍ የሚያስችል ዕጩዎች አቅርበናል በሕዝብ ተወካዮ ምክር ቤትም አባላ ከምትባል ወረዳ እና በትግራይ ድንበር አካባቢ ካለ አንድ ወረዳ ውጪ በሁሉም ዕጩ አቅርበናል።

ቤኒሻንጉል_ጉምዝ – በፀጥጻ ችግር ምክኒያት በ4 ወረዳዎች ዕጩ ማቅረብ አልቻልንም በ5 ወረዳዎች የተወካዮ ምክር ቤት እና ከፊል የክልል ምክር ቤት ዕጩ አቅርበናል።

ኦሮሚያ – በሕዝብ ተወካዮችም ሆነ በክልል ምክር ቤት ዕጩዎችን ለማስመዝገብ ከፍተኛ ተግዳሮት ገጥሞናል ለምርጫ ቦርድ በዝርዝር ቅሬታ ያቀረብን በመሆኑ መልስ ስናገኝ ዝርዝሩን እመለስበታለሁ።

ሱማሌ – ለክልል ምክር ቤት ያቀረብናቸው ዕጩዎ 50 ሲደመር አንድ አይሞሉም ለፓርላማም ያቀረብናቸው 11 ዕጩዎን ብቻ ነው። (13 ቦታ ላይ ዕጩ አላቀረብንም)

በክልል ምክርቤት ብቻችንን የክልል መንግስት የመመስረት ዕድል የሌለን በኦሮሚያ፤ በሶማሌ እና በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ብቻ ነው፡፡ እነሱንም የፀጥታው ችግር ሲስተካከል አሻሽለን በሚቀጥለው አናሻሽላለን፡፡

ሰውን ተስፋ አስቆርጦ በምርጫው ተስፋ እንዲቆርጥ ለማድረግ ያደረከው ጥረት ለዛሬ አልተሳካም፡፡ ከቻልክ ከቻልክ የራስህን ፓርቲ ለማጠንከር ሞክር፤ የእኛን ለኛ ተውልን፡፡

ኢዜማ የተስፈኞች ቤት ነው፡፡ እንኳን ባንተ አይነቱ ከሩቅ ተኳሽ አጠገባችን ባሉት ገዳዮቻችን እንኳን ተስፋ አንቆርጥም፡፡

ኢዮብ መሳፍንት፤ የኢዜማ ዓለም አቀፍ አባላት ተጠሪና የሕግ ባለሙያ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Filed Under: Opinions, Right Column Tagged With: ermias legesse, ezema, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. ነፃ ሕዝብ says

    March 18, 2021 01:21 pm at 1:21 pm

    ኢዮብ መሳፍንት ፦ ድንቄም ሶሻሊዝም ነበር ያሉት እማማ ዝናሽ ! ኢዜማ የተረኞቹ ፋሽስቶችና አፓርታይዳዊ አገዛዝ ኦሮሙማው ምርኩዝ ወይም የነዳያን ስብስብ ፓርቲ ነው ፥ ኢዜማ በአማራ ሕዝብ ጥላቻ የሰከረና መድረሻውም ሆነ መነሻው አማራ ጠል መሆኑን በሰሞኑ “አማራ መጣልህ” ቅስቀሳ በግልፅ አሳይቶዋል ፥ ኢዜማ ከዘመነኞቹ ደናቁርት ኦሮሙማዎች አስተሳሰብ ያልተለየ ድሁር መሆኑን እየተመለከትን ነው ፥ ሌላው የኢዜማ ዓለም አቀፍ አባላት ተጠሪና የሕግ ባለሙያ ነኝ ብሎ ወደ ነገረን ኢዮብ መሳፍንት ሳመራ የቀድሞው ኢህአዴግ ካድሬዎች እና የህወሓት ጀነራሎች ሂሳብ አስተማሪው ኤርምያስ ለገሰ እያልክ ለመሸርደድ የሞከርከው የቅሽምናህን ጥግ ያመለክታል ፥ ሂሳብ ማስተማር የሚቻለው እውቀት ሲኖር ብቻ ነው ፥ ኤርምያስ የሚናገረው እውነትና ተአማኝነት ያለው ነው ፥ ኢዜማዎች ፋሽስቱና ነፍሰ_ገዳዩ አብይ አህመድ አሊ የሚጠላውን ሰው እናንተም በኢዜማ አመካኝታችሁ የጥላቻ ድሪቶ ለመደረት ትሞክራላችሁ ፥ አየህ ጌታው ጎባጣ ከሆነ አሽከሩም ጌታውን ለመምሰል ጎባጣ ሆኖ ለመሄድ ይሞክራል ይባላል ፥ ፋሽስቱና አፓርታይዳዊ አገዛዝ ኦሮሙማው በፀረ_አማራነት የቆመበትን ዕኩይ ዓላማ ኢዜማ እንደ አስፈፃሚ ሆኖ አዲስ አበባ ላይ “አማራ መጣልህ” እያለ ቅስቀሳውን መጀመሩ የኦሮሙማውን ድኩማን አስተሳሰብ ተጋሪ ሆኖዋል ፥ ስለዚህ ኤርምያስ የመሰለውንና የታዘበውን በሚዲያው ለማለት ሞክሮዋል ፥ ኦሮሙማውን ወይም አብይን መስሎ በጥላቻ ታጭቆ መልስ መስጠትና ያልተፃፈ ማንበብ አስፈላጊም አይመስለኝም ፥ እኔ በግሌ ኢዜማ የብል*ግና ሌላኛው ክንፍ አድርጌ የምቆጥረው ፥ ነፍሰ_ገዳዩና አስገዳዩ አብይ ሲያስነጥሰው ኢዜማ ማሃረብ አቅራቢ እንጂ ተቃዋሚ ፓርቲ ተብሎ ሊጠራ አይገባውም ፥ ለዚህም ማሳያው በተከታታይ በአማራ ሕዝብ ላይ የሚደረገውን የዘር ማጥፋት ወንጀል ተቃውሞ አንድም ጊዜ መግለጫ ሲያወጣ አላየሁም ፥ አልሰማሁም ፥ ኢዜማ አ/አበባ ላይ አማራ መጣልህ ፥ ባህርዳር ላይ ግን አማራ ጀግና እያሉ መቀሳፈት ለውርደት ይዳርጋል ፡፡

    Reply
    • Mr Frank Talk says

      April 29, 2021 02:43 am at 2:43 am

      This guy doesn’t seem to know what he is talking g about. He is simply bent on using all the hateful words and phrases and tarnish the images of our PM and our beloved country. He must be one of the Juntas running for their lives or Egyptian agents wanting to destroy Ethiopia.

      Reply
  2. TVPDF says

    March 19, 2021 11:51 am at 11:51 am

    የፓለቲካ ዝሙት ገና ብዙ ዋጋ ያስከፍለዋል። ይልቅስ ለእርሱ የሚያዋጣው ከፓለቲካ ርቆ ንስሓ ገብቶ አንድ የእርዳታ ሰጪ ድርጅት መስርቶ ችግረኛ ቢረዳ ይሻለዋል። ከሕዝብ ወጥቶ ሕዝብን ማምታታት ነውር ነው።
    TVPDF

    Reply
  3. George says

    March 20, 2021 06:52 am at 6:52 am

    ምንድር ነዉ ነገሩ? ዋና ቁምነገሩ ላይ ከማተኮር ይልቅ ፤ሙያዉንና በአንድ ወቅት የተሰማራበትን ሥራ እንደወንጀል ተቆጥሮ በግለሰቡ ዙሪያ ማተኮር የሀሳብ ድህነት በገጠማቸዉ ተሞአጉዋቾች የሚከወን ልክስክስ ተግባር ነዉ፡፡
    ከሁሉ በላይ የሚደንቀዉ ደግሞ “የኢዜማ ዓለም አቀፍ አባላት ተጠሪና የሕግ ባለሙያ” ነኝ በሚል ግለሰብ መፈጸሙ ነዉ፡፡
    ግለሰቡ ተሸከምኩት ከሚለዉ ሀላፊነትና ሙያ ለተመለከተዉ ሁሉ የገዘፈ ቢሆንም ግለሰቡ የሰጠዉ አስተያት ግን ፤ምን ነካዉ የሚያሰኝ ድርጊት ነዉ፡፡ በመሆኑም፤ኤርምያስ ለገሠ ማንም ጠበቃ ሳያስፈልገዉ ኢዮብ መሳፍንት በፈጸመዉ በዚህ ልክስክስ ተግባር ከበቂ በላይ ምላሽ መስጠት እንደሚችል ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚገነዘብ ቢሆንም ፤እንደተመልካች ዝም ብሎ ማለፍ ተገቢ ባለመሆኑ የተወሰኑ ነገሮችን ለማለት ተገደድሁ፡፡ ኢዮብ መሳፍንት ለምን እንዲህ አለ ? ለሚለዉ ጥያቄ ብዙ መልስ የሚሆኑ ሀሳቦችን መሰንዘር ቢቻልም፤ ዋናዉ ግን በኢዜማ በኩል “አለሁ የእናንተ ጠበቃ ” በማለት ሙገ ሳን ለማግኘት የአድርባዮች ዓይነተኛ ጠባይ ነዉ፡፡
    ኤርምያስ ለገሠ ከኢሕአደግ ጋር በነበረበት ወቅት የሰራዉን ሁሉ አንድ በአንድ ዘርዝሮ ይቅርታ ጠይቆአል፡፡አሁን ምን ይጠበስ ተብሎ ነዉ በመደጋጋም መነሳቱ፡፡ የብልጽግና አባላትና የመንግስት አመራሮች ሁሉም ከኢሕአደግ የመጡ ናቸዉ፡፡በአንድ ወቅት ጠ/ሚኒስትሩ በአጋጣሚ ቅርታ ለማለታቸዉ በስተቀር ፤ ደንቡን በጠበቀ መልኩ /formal procedure/ ይቅርታ አልጠየቁም፡፡እናወዳደር ካልን፤ ኤርምያስ ለገሠ ከፈጸመዉ ጉዳት ይልቅ ጠ/ሚኒስትሩ የኢንሳ መሪ ሆነዉ በስለላ የፈጸሙት ወንጀል በጣም ያመዝናል፡፡ሌላም ማለት ቢቻልም ልተወዉ፡፡
    እስከዛሬ ኢዜማ ከፈጸመዉ ክህደት ሁሉ ገዝፎ የወጣዉ ደግሞ በቅርቡ ያስተዋወቀዉ “አማራ መጣልህ” የሚለዉ በተስፋ መቁረጥ የተፈጸመ ክህደትና ወንጀል ነዉ፡፡ ዞሮ ዞሮ ድርጊቱ ኢዜማን ከድጡ ወደማጡ ከመክተቱ በስተቀር ምንም የሚያስገኝለት ፓለቲካዊ ትርፍ አይኖርም፡
    ሌሎች የጎሳ ፓርቲዎች አሊያም ጽንፈኞች ቢሉት ባልደነቀን፤ የተለመደ ነዉና ፡፡
    እንደ ንጉሡ አጎንብሱ ሆነና በኢዜማ ተፈጽሞአል፡፡ በኢዘማ መባሉ ግን፤ እጹብ ድንቅ ሆኖብናል፤መጨረሻዉንም አሳዉቆናል፡፡ አሁንም፤ጊዜዉ አልረፈደምና ቢታረም መልካም ነዉ፡፡

    Reply
    • Mr Frank Talk says

      April 29, 2021 02:47 am at 2:47 am

      This is written by Ermias himself. I can see his style and language in this ‘reply’.

      Reply
  4. chacha says

    March 22, 2021 08:31 am at 8:31 am

    ወይኔ ግዜዬ ይኼን ጽሁፍ ብዬ ማንበቤ ይህን ውዳቂ ጽሁፍ በማንበቤ የበለጠ ኢዜማን እንድጠላው ነው ያደረከኝ ። ኤርሚ ሁሌም ጀግና ነው ። አአ ውስጥ ኢዜማና ህወሀት ቢወዳደሩ እንኳን ቁዘማ አንድ ወንበር አያገኝም ። ቁዘማ አአ የካደ ከሀዲ ነው

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule