• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኤርሚያስ ለገሰ “የወያኔ የፕሮፖጋንዳ ሰራተኛ እያለ የለመደው የቁጥር ጫወታ አለቀቀውም”

March 17, 2021 09:54 pm by Editor 6 Comments

የቀድሞው ኢህአዴግ ካድሬዎች እና የህወሓት ጀነራሎች ሂሳብ አስተማሪው ኤርሚያስ ለገሰ ሆን ብሎ በቁጥር ሊጫወት ሞክሯል፡፡ አላማው ኢዜማ የክልል ምክር ቤት ወንበሮችን ሊያሸንፍ እንደማይችል አስመስሎ መሳል ነው፡፡ ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ ሆኖበት ነው፡፡

ኤርምያስ ሹመት አስቦ የለውጡ ደጋፊ የነበረ ጊዜ የተናገረው

የወያኔ የፕሮፖጋንዳ ሰራተኛ እያለ የለመደው የቁጥር ጫወታ አለቀቀውም፡፡ ምናልባት እንዲገባው ከዚህ በፊት ከነበረው የተቃዋሚዎች ዕጩዎች ቁጥር በ11% እድገት አሳይተናል እንበለው ይሆን?? ምንም እንኳን [ለእንደዚ አይነቱ አውቆ አበድ መፍትሄው] ንቆ መተው ቢሆንም ያቀረበውን የተንኮል መረጃ እንደ እውነት ሊወስዱ የሚችሉ ቅኖችን ከስህተት ለማዳን ዝርዝር መረጃውን ከዚህ በታች አቅርቤዋለሁ፡፡

ምርጫ የሚደረገው በዘጠኝ ክልሎች እና በሁለት ከተማ አስተዳደሮች ነው፡፡ ከዚህ ውስጥ፦

አዲስ_አበባ – ለክልልም ሆነ ለተወካዮች ምክር ቤት ሙሉ ዕጩዎችን ያስመዘገበው ብቸኛው ፓርቲ ኢዜማ ብቻ ነው፡፡ (ከአብን እና ከመኢአድ ጋር በጋር ዕጩዎችን አቅርቦ በስሙ የሚወዳደሩት ባልደራስም ሆነ ገዢው ፓርቲ ሙሉ ዕጩዎችን አላቀረቡም!)

ደቡብ ክልል – በፌደራልም ሆነ በክልል ምክር ቤት በሁሉም ወንበሮች እንወዳደራለን።

አማራ ክልል – በፌደራልም ሆነ በክልል ምክር ቤት ሙሉ በሙሉ እንወዳደራለን።

ጋምቤላ – ያለው የክልል ም/ቤት ወንበር 155 ነው በ114 የክልል ም/ቤት ተወዳዳሪ አቅርበናል የተቀሩት 41 ላይ በምዝገባ ችግር ስለተፈጠረብን ለምርጫ ቦርድ አቤቱታ አቅርበናል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሙሉ በሙሉ እንወዳደራለን።

ሀረሪ – 36 ወንበር ነው ያለው – በአንደኛው ምርጫ ክልል ሙሉ 18 ዕጩዎች ያቀረብን ሲሆን በሌላኛው ምርጫ ክልል ለአደሬ ብሄረሰብ ብቻ የተተወውን 9 ወንበር ጨምረን ዕጩ አቅርበናል የጎደለን 4 የክልል ምክር ቤት ዕጩ ብቻ ነው፡፡ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም ለአደሬ ብሔረሰብ የተተወውን ወንበር ጭምር ዕጩ አቅርበንበታል፡፡

ሲዳማ – ካሉት 19 ወረዳዎች በ16ቱ አብላጫውን ዕጩዎች አቅርበናል በተቀሩት በ3ቱም ዕጩ ብናዘጋጅም በምርጫ ቦርድ ምክኒያት አልተመዘገቡም ቅሬታ ለምርጫ ቦርድ አስገብተናል።

አፋር – በተቃዋሚዎች ታሪክ ለመጀመሪያ ግዜ ለክልል ምክር ቤት 50 ሲደመር 1 ወንበር ማሸነፍ የሚያስችል ዕጩዎች አቅርበናል በሕዝብ ተወካዮ ምክር ቤትም አባላ ከምትባል ወረዳ እና በትግራይ ድንበር አካባቢ ካለ አንድ ወረዳ ውጪ በሁሉም ዕጩ አቅርበናል።

ቤኒሻንጉል_ጉምዝ – በፀጥጻ ችግር ምክኒያት በ4 ወረዳዎች ዕጩ ማቅረብ አልቻልንም በ5 ወረዳዎች የተወካዮ ምክር ቤት እና ከፊል የክልል ምክር ቤት ዕጩ አቅርበናል።

ኦሮሚያ – በሕዝብ ተወካዮችም ሆነ በክልል ምክር ቤት ዕጩዎችን ለማስመዝገብ ከፍተኛ ተግዳሮት ገጥሞናል ለምርጫ ቦርድ በዝርዝር ቅሬታ ያቀረብን በመሆኑ መልስ ስናገኝ ዝርዝሩን እመለስበታለሁ።

ሱማሌ – ለክልል ምክር ቤት ያቀረብናቸው ዕጩዎ 50 ሲደመር አንድ አይሞሉም ለፓርላማም ያቀረብናቸው 11 ዕጩዎን ብቻ ነው። (13 ቦታ ላይ ዕጩ አላቀረብንም)

በክልል ምክርቤት ብቻችንን የክልል መንግስት የመመስረት ዕድል የሌለን በኦሮሚያ፤ በሶማሌ እና በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ብቻ ነው፡፡ እነሱንም የፀጥታው ችግር ሲስተካከል አሻሽለን በሚቀጥለው አናሻሽላለን፡፡

ሰውን ተስፋ አስቆርጦ በምርጫው ተስፋ እንዲቆርጥ ለማድረግ ያደረከው ጥረት ለዛሬ አልተሳካም፡፡ ከቻልክ ከቻልክ የራስህን ፓርቲ ለማጠንከር ሞክር፤ የእኛን ለኛ ተውልን፡፡

ኢዜማ የተስፈኞች ቤት ነው፡፡ እንኳን ባንተ አይነቱ ከሩቅ ተኳሽ አጠገባችን ባሉት ገዳዮቻችን እንኳን ተስፋ አንቆርጥም፡፡

ኢዮብ መሳፍንት፤ የኢዜማ ዓለም አቀፍ አባላት ተጠሪና የሕግ ባለሙያ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Right Column Tagged With: ermias legesse, ezema, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. ነፃ ሕዝብ says

    March 18, 2021 01:21 pm at 1:21 pm

    ኢዮብ መሳፍንት ፦ ድንቄም ሶሻሊዝም ነበር ያሉት እማማ ዝናሽ ! ኢዜማ የተረኞቹ ፋሽስቶችና አፓርታይዳዊ አገዛዝ ኦሮሙማው ምርኩዝ ወይም የነዳያን ስብስብ ፓርቲ ነው ፥ ኢዜማ በአማራ ሕዝብ ጥላቻ የሰከረና መድረሻውም ሆነ መነሻው አማራ ጠል መሆኑን በሰሞኑ “አማራ መጣልህ” ቅስቀሳ በግልፅ አሳይቶዋል ፥ ኢዜማ ከዘመነኞቹ ደናቁርት ኦሮሙማዎች አስተሳሰብ ያልተለየ ድሁር መሆኑን እየተመለከትን ነው ፥ ሌላው የኢዜማ ዓለም አቀፍ አባላት ተጠሪና የሕግ ባለሙያ ነኝ ብሎ ወደ ነገረን ኢዮብ መሳፍንት ሳመራ የቀድሞው ኢህአዴግ ካድሬዎች እና የህወሓት ጀነራሎች ሂሳብ አስተማሪው ኤርምያስ ለገሰ እያልክ ለመሸርደድ የሞከርከው የቅሽምናህን ጥግ ያመለክታል ፥ ሂሳብ ማስተማር የሚቻለው እውቀት ሲኖር ብቻ ነው ፥ ኤርምያስ የሚናገረው እውነትና ተአማኝነት ያለው ነው ፥ ኢዜማዎች ፋሽስቱና ነፍሰ_ገዳዩ አብይ አህመድ አሊ የሚጠላውን ሰው እናንተም በኢዜማ አመካኝታችሁ የጥላቻ ድሪቶ ለመደረት ትሞክራላችሁ ፥ አየህ ጌታው ጎባጣ ከሆነ አሽከሩም ጌታውን ለመምሰል ጎባጣ ሆኖ ለመሄድ ይሞክራል ይባላል ፥ ፋሽስቱና አፓርታይዳዊ አገዛዝ ኦሮሙማው በፀረ_አማራነት የቆመበትን ዕኩይ ዓላማ ኢዜማ እንደ አስፈፃሚ ሆኖ አዲስ አበባ ላይ “አማራ መጣልህ” እያለ ቅስቀሳውን መጀመሩ የኦሮሙማውን ድኩማን አስተሳሰብ ተጋሪ ሆኖዋል ፥ ስለዚህ ኤርምያስ የመሰለውንና የታዘበውን በሚዲያው ለማለት ሞክሮዋል ፥ ኦሮሙማውን ወይም አብይን መስሎ በጥላቻ ታጭቆ መልስ መስጠትና ያልተፃፈ ማንበብ አስፈላጊም አይመስለኝም ፥ እኔ በግሌ ኢዜማ የብል*ግና ሌላኛው ክንፍ አድርጌ የምቆጥረው ፥ ነፍሰ_ገዳዩና አስገዳዩ አብይ ሲያስነጥሰው ኢዜማ ማሃረብ አቅራቢ እንጂ ተቃዋሚ ፓርቲ ተብሎ ሊጠራ አይገባውም ፥ ለዚህም ማሳያው በተከታታይ በአማራ ሕዝብ ላይ የሚደረገውን የዘር ማጥፋት ወንጀል ተቃውሞ አንድም ጊዜ መግለጫ ሲያወጣ አላየሁም ፥ አልሰማሁም ፥ ኢዜማ አ/አበባ ላይ አማራ መጣልህ ፥ ባህርዳር ላይ ግን አማራ ጀግና እያሉ መቀሳፈት ለውርደት ይዳርጋል ፡፡

    Reply
    • Mr Frank Talk says

      April 29, 2021 02:43 am at 2:43 am

      This guy doesn’t seem to know what he is talking g about. He is simply bent on using all the hateful words and phrases and tarnish the images of our PM and our beloved country. He must be one of the Juntas running for their lives or Egyptian agents wanting to destroy Ethiopia.

      Reply
  2. TVPDF says

    March 19, 2021 11:51 am at 11:51 am

    የፓለቲካ ዝሙት ገና ብዙ ዋጋ ያስከፍለዋል። ይልቅስ ለእርሱ የሚያዋጣው ከፓለቲካ ርቆ ንስሓ ገብቶ አንድ የእርዳታ ሰጪ ድርጅት መስርቶ ችግረኛ ቢረዳ ይሻለዋል። ከሕዝብ ወጥቶ ሕዝብን ማምታታት ነውር ነው።
    TVPDF

    Reply
  3. George says

    March 20, 2021 06:52 am at 6:52 am

    ምንድር ነዉ ነገሩ? ዋና ቁምነገሩ ላይ ከማተኮር ይልቅ ፤ሙያዉንና በአንድ ወቅት የተሰማራበትን ሥራ እንደወንጀል ተቆጥሮ በግለሰቡ ዙሪያ ማተኮር የሀሳብ ድህነት በገጠማቸዉ ተሞአጉዋቾች የሚከወን ልክስክስ ተግባር ነዉ፡፡
    ከሁሉ በላይ የሚደንቀዉ ደግሞ “የኢዜማ ዓለም አቀፍ አባላት ተጠሪና የሕግ ባለሙያ” ነኝ በሚል ግለሰብ መፈጸሙ ነዉ፡፡
    ግለሰቡ ተሸከምኩት ከሚለዉ ሀላፊነትና ሙያ ለተመለከተዉ ሁሉ የገዘፈ ቢሆንም ግለሰቡ የሰጠዉ አስተያት ግን ፤ምን ነካዉ የሚያሰኝ ድርጊት ነዉ፡፡ በመሆኑም፤ኤርምያስ ለገሠ ማንም ጠበቃ ሳያስፈልገዉ ኢዮብ መሳፍንት በፈጸመዉ በዚህ ልክስክስ ተግባር ከበቂ በላይ ምላሽ መስጠት እንደሚችል ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚገነዘብ ቢሆንም ፤እንደተመልካች ዝም ብሎ ማለፍ ተገቢ ባለመሆኑ የተወሰኑ ነገሮችን ለማለት ተገደድሁ፡፡ ኢዮብ መሳፍንት ለምን እንዲህ አለ ? ለሚለዉ ጥያቄ ብዙ መልስ የሚሆኑ ሀሳቦችን መሰንዘር ቢቻልም፤ ዋናዉ ግን በኢዜማ በኩል “አለሁ የእናንተ ጠበቃ ” በማለት ሙገ ሳን ለማግኘት የአድርባዮች ዓይነተኛ ጠባይ ነዉ፡፡
    ኤርምያስ ለገሠ ከኢሕአደግ ጋር በነበረበት ወቅት የሰራዉን ሁሉ አንድ በአንድ ዘርዝሮ ይቅርታ ጠይቆአል፡፡አሁን ምን ይጠበስ ተብሎ ነዉ በመደጋጋም መነሳቱ፡፡ የብልጽግና አባላትና የመንግስት አመራሮች ሁሉም ከኢሕአደግ የመጡ ናቸዉ፡፡በአንድ ወቅት ጠ/ሚኒስትሩ በአጋጣሚ ቅርታ ለማለታቸዉ በስተቀር ፤ ደንቡን በጠበቀ መልኩ /formal procedure/ ይቅርታ አልጠየቁም፡፡እናወዳደር ካልን፤ ኤርምያስ ለገሠ ከፈጸመዉ ጉዳት ይልቅ ጠ/ሚኒስትሩ የኢንሳ መሪ ሆነዉ በስለላ የፈጸሙት ወንጀል በጣም ያመዝናል፡፡ሌላም ማለት ቢቻልም ልተወዉ፡፡
    እስከዛሬ ኢዜማ ከፈጸመዉ ክህደት ሁሉ ገዝፎ የወጣዉ ደግሞ በቅርቡ ያስተዋወቀዉ “አማራ መጣልህ” የሚለዉ በተስፋ መቁረጥ የተፈጸመ ክህደትና ወንጀል ነዉ፡፡ ዞሮ ዞሮ ድርጊቱ ኢዜማን ከድጡ ወደማጡ ከመክተቱ በስተቀር ምንም የሚያስገኝለት ፓለቲካዊ ትርፍ አይኖርም፡
    ሌሎች የጎሳ ፓርቲዎች አሊያም ጽንፈኞች ቢሉት ባልደነቀን፤ የተለመደ ነዉና ፡፡
    እንደ ንጉሡ አጎንብሱ ሆነና በኢዜማ ተፈጽሞአል፡፡ በኢዘማ መባሉ ግን፤ እጹብ ድንቅ ሆኖብናል፤መጨረሻዉንም አሳዉቆናል፡፡ አሁንም፤ጊዜዉ አልረፈደምና ቢታረም መልካም ነዉ፡፡

    Reply
    • Mr Frank Talk says

      April 29, 2021 02:47 am at 2:47 am

      This is written by Ermias himself. I can see his style and language in this ‘reply’.

      Reply
  4. chacha says

    March 22, 2021 08:31 am at 8:31 am

    ወይኔ ግዜዬ ይኼን ጽሁፍ ብዬ ማንበቤ ይህን ውዳቂ ጽሁፍ በማንበቤ የበለጠ ኢዜማን እንድጠላው ነው ያደረከኝ ። ኤርሚ ሁሌም ጀግና ነው ። አአ ውስጥ ኢዜማና ህወሀት ቢወዳደሩ እንኳን ቁዘማ አንድ ወንበር አያገኝም ። ቁዘማ አአ የካደ ከሀዲ ነው

    Reply

Leave a Reply to ነፃ ሕዝብ Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule