
ቁጭ ብዬ ናሽናል ጂኦግራፊክ ስመለከት ጅቦች አየሁ። አንድ ጎረምሳ አንበሳ ይተናኮላሉ። አንበሳው እየገላመጠ መንጋጋውን እያጓራ ያሳያቸዋል። ራሱን ለመከላከል ብዙም ያልተጨነቀው አንበሳ እየተቆጣና እየተገላመጠ ሲራመድ ጅቦቹ የልብ ልብ ተሰማቸው። ጅቦች አንበሳን ሊበሉ ቋመጡ። በመካከሉ አንዱ ጅብ ዘልቆ ሲገባ አንበሳው ተወናጭፎ መቀመጫው አካባቢ ነከሰው። ይህኔ የተነከሰው ጅብ ጩኸቱን አምባረቀ።
አንበሳው በጣም ተናዶ ጉልበቱን ማሳየት ሲጀምር ጅቦች አፈገፈጉ። ይህን ጊዜ የተነከሰውን ጅብ መቀመጫ የማየት ዕድል የገጠማቸው ጅቦች አንበሳውን ትተው “ወንድማቸውን” ያሳድዱ ጀመር። አባረው ያዙት። አንበሳው በነከሰው በኩል የሚፈሰውን ደም ተከትለው በደቦ በሉት። ጅብ ሌላው ጅብ ላይ ደም ካየ አይምርም። ደም ሲደማ ሆዱ እንደሚሞላ ስለሚያውቅ ማድማት ወይም በደማው በኩል ገብቶ መከተት፤ ደም ካለው ቤተሰብ፣ ዘመድ፣ ወንድም፣እናት፣ አባት፣ የሚባል የጅብ ዓይነት የለም።
ይህን እያየሁ ስለ 360 የሰማሁት መረጃ ተገናኘልኝ። 360 የአንድ መንጋ ስብሰብ ነው። በዚህ መንጋ ውስጥ አስር የሚጠጉ እንደየደረጃቸው የሚለይዩ ጅቦች አሉ። ዋናው ራሱን “እኔ ባለሙያ ነኝ” የሚለው ጅብ ኤርሚያስ ለገሰ ነው። የመተትና ድግምት ዓይነት ስሜት እንጂ ዕውቀት የማይታይበት ሁለተኛው ጅብ ሃብታሙ አያሌው ነው። የተቀሩት እነደየአቅሚቲ ለአካለ ሤራ ትንተና ያልደረሱ ፍልፈሎች ናቸው። እነሱን ከዚህ በኋላ አላነሳቸውም።
ልክ ወገናቸው ላይ ደም ሲያዩ ተረባርበው እንደበሉት የጅብ መንጋዎች፣ 360 የሚባለው የመርዝ ማከፋፈያ የዩቲዩብ ክፍለ ጊዜ የተመሰረተው ኢትዮጵያ ለውጡን ተቋማዊ ለማድረግና ያለፈውን የሰላሳ ዓመታት ትብትብ ለመበጣጠስ ስትባዝን ነው። ይህ ቡድን ጀሌዎቹን ሰብስቦ ዘመቻውን የጀመረው ለውጡ ትህነግ የሚባለው ቡድን እየፈረሰና እያነተበው በመሄድ ላይ ሳለ እንደ ስሙ 360 ዲግሪ በመዞር ነው።
ይህ የሤራ ተንታኝ ጀሌ ሰሞኑንን “ገቢ ቀነሰ” በሚል መበላላት ሊጀምር እንደሆነ ተሰምቷል። አንድ ሳይገባው ገንዘብ ያዋጣና ይረዳቸው የነበረ እንዳለው “የምናገኘው ገቢና ብዛታችን አልተመጣጠነም” በሚል የመለየት ጥያቄ ያነሱ አሉ። ዋናው ምክንያቱ አልጠግብ ባይነት ነው።
አሁን ባለው ወቅታዊ ሁኔታ እጃቸውን ለ360 የሚዘረጉ እጆች እየታጠፉ ነው። የባለቤቶቹ ዓላማና ፍላጎት የማይታወቅው የመረጃ ቴሌቪዥን ባለቤቶች ካልሆኑ በቀር አብዛኛው የሚታወቀው ድጋፍ ደርቋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ “መረጃ ቲቪ” ብሎ ፍጹም የሆነ ሽብርና መርዝ ኢትዮጵያ ላይ እየረጩ ያሉት የሚዲያው ባለቤቶች ዛሬ ድረስ በያዙት አቋም መቀጠላቸው በበርካቶች ዘንድ አሳዛኝ እንደሆነ እየተገለጸ ነው። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የመረጃ ቲቪ ባለቤቶች ዓላማቸው ምን እንደሆነ፣ ምን እንደሚፈልጉና እንዲህ ባለ አገርን የማፈራረስ ጉዳይ ውስጥ ለምን መግባት እንደፈለጉ ለመጠየቅና ዘመቻ ለመጀመር ዲሲ አካባቢ ያሉ ወገኖች እየመከሩ መሆኑ ተሰምቷል።
ወደተነሳሁበት ጉዳይ ስመለስ … የ360 ፊት አውራሪና የባልደራስ ምክትል ሊቀመንበር ኤርሚያስ ለገሰ “አሁንስ በቃኝ” ሲል የሰሙ እንደሚሉት እሱ፣ ሃብታሙና ብሩክ ለብቻቸው ሊወጡና ሌላ የሚዲያ ፕላትፎርም ሊዘረጉ ወይም ሌሎቹን በማሰናበት እንዳለ ሊቆጣጠሩት አስበዋል።
ኤርሚያስ ለገሰ፤ “ለምኖ ያጣ ለማኝ ተሳድቦ ይሄዳል”
ኤርሚያስ “እኔ ፕሮፌሽናል ነኝ፤ ሌላም ሥራ መሥራት እችላለሁ” የሚል የካድሬ ትምክህት ወጥሮት ሌሎችን ያጣጥላል። “አንድ ጽሁፍ ጽፋ ኢህአዴግ አስሮ ያጀገናት” እያለ በጀርባዋ የሚያጣጥላት ርዕዮት አለሙም ሆነ ሌሎች የሚያዘጋጁት ፕሮግራም ልክ እሱ በየዕለቱ እንደሚመራው የማራከሻ ፕሮግራም ያህል ገቢ ስለሌለው እኩል ጥቅም ሼር ማግኘት የለባቸውም ባይ ነው። ሃብታሙም በቤቱ ራሱን አዋቂ አድርጎ ይህንኑ ዓላማ አራማጅ ሆኗል።
ዲሲ አካባቢ በሰው ቤት ቤዝመንት (ምድር ቤት) ሆኖ የኢንተርኔት ኮኔክሽኑ እያስቸገረው የኢትዮጵያን ወቅታዊ ፖለቲካ እተነትናለሁ የሚለውን ሃብታሙ አያሌውን ኤርሚያስ የሚፈልገው ለጥቅሙ ነው። የኦርቶዶክሱንና በዚያ ጎራ ያለውን ሕዝብ ለመሳብ በኮሙኒስቱ በረከት ስምዖን ተጠፍጥፎ የተሠራው ኤርሚያስ የግድ ሃብታሙ ያስፈልገዋል። የራሱን አውቃለሁ ባይነት እያስጠበቀና ከዚህና እዚያ ያነበባቸውን በእንግሊዝኛ እየጠቃቀሰ “… ይህንን እኔ በሦስት ከፍዬ ነው የማየው … ከዚህ አራት መሠረታዊ ነጥቦችን ማውጣት ይቻላል …” እያለ ሤራ የሚተነትነው የሃብታሙን አቅመቢስነት በአደባባይ ሲያሰጣው ነው እንጂ የንቀቱን መጠን ሃብታሙም ሳይረዳው አልቀረም። እሱም በተገላቢጦሽ ለኅልውናው ኤርሚያስ ስለሚያስፈልገው አብሮ መጓዙ ግድ ሆኖበታል።
ስብሃት ነጋ ከተወሸቀበት ጉድጓድ በወጣበት ጊዜ ስብሃትን እንደሚያውቀው በስፋት ሲናገረው የነበረው ሃብታሙ እንዲያውም በአንድ ስብሰባ ላይ አስተያየት ሲሰጥ የሰማው ስብሃት ነጋ “እንዴ ይሄ የእኛ ልጅ አይደለም እንዴ?” ማለቱን በገሃድ ተናግሯል። እንደ ኤርምያስ የሤራ ትንተና ብቃት እንዳለው ለማስመስከር መከራውን የሚየው ሃብታሙ ከዚህ በፊት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ድምፅ ከብልጽግና ስብሰባ ሾልኮ ወጣ ተብሎ አንድ ቂሎ የተባለ ሚዲያ የፖሰተውን አለቅጥ ሲብጠለጥል ኤርሚያስ ግን በንቀት እያየው አንዳችም አልተናገረም ነበር። በኋላ ኦዲዮው ስህተት መሆኑን ያወጣው ሚዲያ ራሱ ይቅርታ ሲጠይቅ እነ ሃብታሙ ግን “ዐቢይ ባይለውም ሊለው የሚችል ነገር ነው” በማለት ነበር ሸምጥጠው የካዱት። ኤርሚያስ ግን ከሃብታሙ ጋር ከመቆም ይልቅ ከዚህ ራሱን ገለል ነበር ያደረገው።
ትህነግ ወደ መንበሩ እንዲመልስ መንግሥትን በፈጠራ፣ የመንግሥት ባለሥልጣናትን በተለይም የጠቅላይ ሚንስትሩን ንግግር በመቀንጨብ ለጥፋት ፖለቲካ በማዋል፣ ሲያካሂዱ የቆዩትን ዘመቻ፣ ‘እረኛውን ምታ’ የሚለውን የዲጂታል ወያኔ መሪ ቃል በማንገብ ሲታትርና እየታተረ ያለው 360 በመጨረሻ በጥቅም ምክንያት ተቧድኗል።
ኤርሚያስ “አዲስ አበባ እሄዳለሁ፤ የዐቢይ አማካሪ እሆናለሁ” በማለት ብዙ ከተቦጠረቀና ለዚህም እንዲረዳው በማለት ለዶ/ር ዐቢይ ያለ የሌለውን አድናቆት ሲያወርድ ከቆየ በኋላ ሁሉም የእምቧይ ካብ ሲሆንበት ዐቢይን ማናናቅ ጀመረ። መገለባበጥ ብርቁ ያልሆነው የበረከት ልጅ “አዲስ አበባ ከኦሮሚያ መሬት እየነጠቀች ያለቅጥ እየሰፋች ነው” በማለት የኦሮሞ ጥናት ማኅበር ላይ በገሃድ ከተናገረ በኋላ እንደለመደው የባልደራስ የውጪ አስተባባሪና ምክትል ሊቀመንበር ሆኖ በመግባት ለነእስክንድር የፖለቲካ ጉዞ ትልቅ ዕንቅፋት ፈጣሪ ሆነ።





መተቸትና ጉድፍን መንቀስ የጋዜጠኛነት ሥራ መሆኑ ቢታመንም፣ 360 በየቀኑ የባለሥልጣናት ንግግርና መግለጫ ላይ ተጣብቆ ሃሜት እየዘራ፣ ጥላቻና መለያየትን እያባባሰ፣ በተለይም አማራ ክልልን ለመናድ ከወቅቱ የትህነግ ተላላኪ ከሚባሉት ታምራት ላይኔ፣ ሻለቃ ዳዊትና ያሬድ ጥበቡ ጋር ሆነው የጀመሩት ዘመቻ በገሃድ አስፈርጇቸዋል። ርዕዮት ከሚባለው የታወረ የትህነግ ሚዲያ ጋር እንደ ኮሶ ተጣብተው በመናበብ መስራታቸው በርካታ ዜጎችን አሳዝኗል። በግልጽም “በቃችሁ” ያሉዋቸው እንዳሉም ተሰምቷል።
በዚህና በሌሎች ገፊ ምክንያቶች ኤርሚያስ ጭራሹኑ “ሌላ ሥራ እጀምራለሁ” ማለት የጀመረ ሲሆን፣ እንደ ጅቦቹ በከርስ ጉዳይ መከፈላቸው ግን የማይቀር እየሆነ መጥቷል። ሃብታሙና ኤርሚያስ የ360 ገቢ 50 ከመቶ እንደሚገባቸው ያቀረቡት ጥያቄ በሌላው የቡድኑ አባላት ዘንድ ተቀባይነት ስላጣ አማራጩ መበተንና ተቧድኖ መሥራት ሆኗል። ይሳካላቸው አይሳካላቸው አይታወቅም እንጂ ዕርቅ መውረድ አለበት የሚሉ ጥቂቶች እንዳሉም ተሰምቷል።
ደም እንደታየበትና በጅቦች እንደተበላው ጅብ፣ ኢትዮጵያ ዝላለች በሚል በከርሳቸው ተታለው አገራቸውን ለመብላት የተነሱት እነ ኤርሚያስ መጨረሻቸው እርስ በርስ መበላላት እንደሚሆን ይጠበቃል።
አያሌው ለገሠ ነኝ
“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።
በየሱስ ስም! በአሁኑ ስዓት እውነታውን ይዘው መሬት ላይ የሚወርድ ወቅታዊ ጭብጥ ያለው መረጃ የሚያቀርቡት እነ ሃብታሙ ናቸው ወዳጄ። btw ሴራ ተንታኞች አይደሉም። ምን አይነት እርባና ቢስ ኮተት ነው የፃፍከው በጌታ!
ህዝብ ሚከታተለውን ያውቃል ወዳጄ፣ ከመሃይማን ጎራ ወይም ከመሃይማን አለቃ ብልፅግና/ብአዴን ፍርፋሪ ተቀባይ ካልሆንክ 360ን መጥላት ህመም ነው፣ ታከመው!
አንተ አጋሰስ ካንተ አይነቱ አጨብጫቢ ጋር ሳይመሳሰሉ የሚተቹትን ሁሉ ችለው ፡ እውነቱን እየተናገሩ ያሉት ኤርሚ እና ሀብቴ ናቸው፡ አንተ መሰሎችህ ደሞ ባለስልጣናት እንዴት ይሰደባሉ እያልችሁ ባለጊዜ አጨብጭቡ ፡ አንተን ብሎ ጸሃፊ