
ከኢሣት ከተባረሩ/ፈቃዳቸው ከመልቀቁ በኋላ “ኢትዮ 360” የሚል የቱቦ (የዩትዩብ) ቲቪ የተከፈተው “ሚዲያ” የወያኔ መሆኑ ተረጋገጠ። በኢትዮጵያ ለውጥ ከተካሄደ በኋላ በርቀት የተመኙት የውሃ ሽታ ሆኖ ሲቀርባቸው በዶ/ር ዐቢይ ላይ ፍጹም ጭፍን የሆነ የጥላቻ ዘገባ በመሥራት ከህወሃት በላይ አገር በማፍረስ ተግባር ተጠምደው የነበሩት ቀዳሚው አገልግሎታቸው ለህወሃት እንደነበር አብሯቸው ሲሠራ የነበረው አጋልጧል። (ጎልጉልም ይደርሰው ከነበረው መረጃ በመነሳት ሚዲያው ኢትዮጵያን ለማፍረስ ከተነሱ ኃይሎች እና ከጽንፈኛ ቡድኖች የቀጥታና ተዘዋዋሪ የጥቅም ተካፋይ እንደሆነ መዘገቡ አይዘነጋም)
ሁለቱ የህወሓት አገልጋይ የነበሩት ኤርምያስና ሃብታሙ ከኢሣት አፈንግጠው ከወጡ በኋላ በኢትዮ 360 እስካሁን ያላቋረጠ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ በዶ/ር ዐቢይ ላይ እንደከፈቱ ነው። ሃብታሙ ከህወሃት አገልጋይነቱ ወደ ተቃዋሚው ጎራ ከገባ በኋላ ወያኔ መልሶ ለመጥቀስ የሚከብድ የአካል ጉዳት ካደረሰበት በኋላ ወደ ትፋቱ መመለሱ የብዙዎች ጥያቄ እንደሆነ ነው። ከሃብታሙ በተጨማሪ በአንድ የዜና ዘገባ የጋዜጠኛነት ማዕረግ ተጎናጽፋ “ጀግና” ለመባል የበቃችው ርዕዮት እንዲሁ በህወሓት ሎሌነት፣ በዐቢይ ጥላቻ መዘፈቋ ሌላ ግራ የሚያጋባ ጉዳይ ነው።
በረከት ስምዖን ጠፍጥፎ የሠራው ኤርምያስ አሁንም ታማኝነቱን በዚያው መስመር መቀጠሉ የሚገርም ባይሆንም ከዚህ በፊት በተሰራጨ ጽሁፍ እንዲህ የተባለለት ነው። “በሕይወት በነበረበት ጊዜ ኢትዮጵያን ጠርንፎ የነበረውን ኢህአዴግን እንዲያገለግሉ የሚመለመሉ በርካታ ወዶገብ ጥቅመኞች ነበሩ። በአንድ ወቅት ተስፈኛ ካድሬዎችን ለመመልመል ሲኒየሮቹ ካድሬዎች በሄዱበት ክፍለከተማ ከተሰበሰቡት መካከል አንዱ ኤርሚያስ ለገሰ ነበር። በወቅቱ አብሮት የነበረ የቅርብ ወዳጄ እንደሚለው ከሆነ “ደርግን ገረሰስን” የሚሉት ተጋዳላዮች በወቅቱ ደረሰብን በማለት ከመድረኩ ሲያወሩ ኤርሚያስ ከሥር ሆኖ በአራት መዓዘን ያለቅስ ነበር። አገር ለመገንጠል የተነሱት የወንበዴዎች ክምችት “ቁርጠኝነታቸው፣ በቦምብ ላይ መረማመዳቸው፣ አንዱ ለሌላው ልሙት ማለቱ፣…” ነበር ኤርሚያስን ተንሰቅስቆ ያስለቀሰው፤ ይህንኑ ቃል በሌላ ጊዜ ደግሞታል። ይህንን እንስፍስፍ እጩ ካድሬ ማንነት የጠየቁ መልማዮች ወዲያውኑ በብርሃን ፍጥነት ኤርሚያስን ከክፍለከተማ አስፈነጠሩትና መድረሻውን አሁን በእስር ላይ የሚገኘው በረከት ስምዖን መ/ቤት አደረሱት”። (ሙሉው ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል)
ከኢትዮ 360 አብሮ ከሠራ በኋላ ለቅቄአለሁ የሚለው ምናላቸው ስማቸው ከተናገረውና የተጨመቀው ከዚህ በታች ቀርቧል።
- 360 የሚባለው የሚዲያ ፕሮግራም በቀጥታ ከሀገር ደህንነት ስጋት ከሆኑና ለጥፋት ከተሳሰሩ ሰዎች ጋር ውሎ ማደር ሲጀምር በቃኝ አልኩ።
- ስንጀምር በሙሉ የራስ አቅም ለመንቀሳቀስ ነበር፣ ሆኖም በተደጋጋሚ ኤርሚያስ ከህወሃት ጋር እየተገናኘ ሲመጣ መጠራጠር ጀመርኩ።
- እኔ ምናላቸው ለራሴ ክብር ያለኝ ነኝ፤ ህወሃትን የገንዘብ ምንጭ አድርጌ ምንም ሥራ መስራት አልፈልግም። ሃብታሙ በአንድ ስብሰባ ከማንም ገንዘብ ካገኘን እንወስዳለን ሲል ደነገጥኩ። ያን ቀን የእኔ 360 ቆይታዬ አበቃ አልኩ።
- የህወሃት ዋነኛ አቋም ግብፅን መደገፍንም እንደሚጨምር በማስረጃ አውቀን፤ በውስጥ የደረሱን መረጃዎች ብዙ ነገሮችን ቢያሳዩንም ከሁለቱም የማልጠብቀውን ጉዳይ ሲያበረታቱ በተለይ ርዕዮትና ኤርሚያስ ውስጤን ሰበሩት።
- ርዕዮት በተለይ የወያኔ ቁስሏ እንዳልደረቀ ትናገራለች፤ ሆኖም ዶክተር ዐቢይን የሚጎዳ ከሆነ ከህወሃት ተላላኪው አሉላ የመጣን ዕርዳታ ለመቀበል ዓይኗን አላሸችም። ይህ ጤነኛ ጉዳይ አይደለም።
- የሆነ ጊዜ የኢሳቱ ሲሳይ አጌና የህወሃት አሜሪካ ክንፍ ሚዲያ ስለማቋቋም እንዳሰበና ከፍተኛ ገንዘብ በታዋቂነት ደረጃ ላሉ ሰዎችም ለማደል እንደተዘጋጁ ሲናገር ትኩረት አልሰጠሁትም ነበር። አሁን በቀጥታ ለ360 ማኔጅመንት እየተባለ የሚጎርፈው ገንዘብ ምንጭ ላይ ማንም በእኛ ውስጥ መነጋገር አይፈልግም። 360 የዶክተር አብይ ተቃውሞን በከበሮ የሚያደምቅ ወያኔ ስፖንሰር የምታደርገው የአማርኛ ተናጋሪ ሚዲያ ነው።
- የግብፅ ጉዳይ ላይ በጋራ ዶክተር አብይን እናጥቃው በማለት አብረው ሊሰሩ የማይችሉ ፅንፈኞችና እርስ በእርስ ለመጠፋፋት የሚፈላለጉ ቡድናት ተቀናጅተው እንደሚሰሩ ሳይ ከበደኝ፤ ትንሽም ቢሆን ህሊና ያለኝ ሰው ነኝ ከሀገሬ ጥቅም ጋር አልደራደርም ብዬ ወጣሁ።
- የገንዘብ ምንጮቻችን በአብዛኛው ከቀድሞ የህወሃት ቡድን ነው። ይህንን ምንም ሳልጠራጠር እናገራለሁ ብሏል ምናላቸው ስማቸው።
ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ
golgul ድህረ-ገጽ አዘጋጆች በእጅጉ የምታስዝኑና የምትከረፉ ሆናችሁዋል ፥ እንዴት ሆኖ ነው ኢትዮ 360 የወያኔ ሚዲያ ሆኖዋል የምትሉት ? ከመንግሥት ጋር ተለጥፋችሁ የመንግሥት ተቃዋሚ የሆነን ሚዲያ ብትወነጅሉ ምን ያስደንቃል ! የወሬ ማባያ ይዛችሁ አትዝፈኑ ! ምናላቸው እንደዚህ ብሏል ብላችሁ ፍጹም ውሸት በሆነና ባልተጨበጠ ነገር አትዋሹ ! ውሸት ቅሌት ነው ! ምናላቸው ከኢትዮ 360 ያፈነገጠበት ምክንያት ወደፊት በግልጽ ይገለፃል ፥ ያገሬ ሰው “ትንሽ ቆሎ ይዘህ ወደ አሻሮ ተጠጋ ይላል ” እንደ ጎልጉል ድህረ-ገጽ ዓይነት ማለት ነው ፥ እናንተ ጎልጉሎች ደጋፊዎች እንደሆናችሁ ሁሉ ኢትዮ 360 ሚዲያም የመንግሥት ተቃዋሚ ነው ፥ መደገፍ እንዳለ ሁሉ መቃወምም አለ ! ጎልጉሎች በግልሰቦች ላይ ያላችሁ አመለካከት ፍጹም የተሳሳተና የወረደ ነው ኤርምያስ ለገሰ እንደማንኛውም ሰው በሥርዓቱ ውስጥ ለተወሰነ ጊዜ አገልግሎ በመጨርሻም አራግፎዋቸው ወጥቶዋል ፥ እናንተ በኤርምያስ ለገሰ ላይ ያላችሁ ፍጹም የተሳሳተ አመለካከት ከመንግሥት ጋር መወገናችሁን በግልጽ ያሳያል ፥ ምክንያት እርሱ መንግሥታችሁን ሲቃወም እናንተ ደግሞ የእርሱን ስም ማጥፋት የዘወትር ተግባራችሁ ነው ፥ በሥርዓቱ ውስጥ እስካሁን ያለና እየዘረፈ ያለውን ህወሃት-ኦነግ ወንጀለኞች ስታጋልጡ አትታዩም ፥ ነገር ግን ከመንግሥት ጋር ያልወገነውንና የሚቃወመወን የስም ማጥፋት ዘመቻ የምታካሂዱበት የእናንተን አፋሽ አጎንባሽነት ያሳብቅባችሁዋል ፥ ለማንኛውም ጎልጉል እውነቱን እያጋለጠች የሕዝብ ዐይንና ጆሮ ሆና በሕዝብ ዘንድ ተወዳጅና ተፈቃሪ እንድትሆን መሥራት ይኖርባችሁዋል ፥ ፍጹም ሚዛናዊ ሁኑ ፥ መንግሥትን መደገፍ ሳይሆን እውነታውን በማውጣት ለሕዝብ መረጃ መስጠት ነው ፥ እስኪ ያለ ምንም ዓይነት ጥፋት ተዋቂው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ሲታሰር መንግሥትን ተቃወሙ ፥ እውነቱን ተናገሩ ፥ መንግሥት እየሄደበት ያለው መንገድ ስህተት መሆኑን ፃፉ ፥ ኢትዮ 360 ሚዲያ ወያኔ ነው ፥ ቀለብ ይሰፈርለታል … ውሸትና ያልተጨበጠ የወሬ ጋጋታ ትርፉ መዝቀጥ ነው ።
I don’t read them,Ethiopiawi charater yelewm
I don’t see any hard evidence other than hearsay and accusations. Let Minalachew speak and provide irrefutable evidence. You get off from your high horses and stick to the journalism than being a mouth piece of others and your wishful thinking.
Dear Editor, do you really think it is such a good idea to accuse an organization or individual in such manner without presenting a single piece of evidence? You are entitled to your opinion but leveling such an accusation deserve to be accompanied with evidence so the reader can weigh the facts and make a determination. It is distressful to see you using your media to trample on the right of others and spread unfounded theories and opinions as fact. It will take away credibility from your journal and make all what you write suspect. I do not follow the media in question on a regular manner but I very much doubt all those folks that work in the organization could be associated with Woyane and any such accusation should be substantiated. Your charges are very grave and all I can say is you better have the evidence or a very good attorney, you have left yourself open to defamation and other charges.
.
ይሄ ድረ ገፅ በቀጥታ በአብይ አህመድ ተደጉሞ የሚንቀሳቀስ የኦሮሙማ ክንፍ እንደሆነ ኢትዮ 360ን በመተቸት ፀረ ኢትዮጵያ መሆኑን በሚገባ ያረጋገጠ የዘመኑ ሆድ አደር ቅጥረኞች እንደሆነ አለ ጥርጥር ያስመሰከረ የባንዶች ተረት ተረት የሚዘከርበት ደጀ ሰላም እንደሆነ የሚጠራጠር ካለ በውነት የአድር ባይ ካድሬዎችን አካሄድና አረማመድ ያልተረዳ መሆን አለበት ። ጎልጉል በውነት አይና አንጀታችሁ ይጎልጎል ከንቱዎች ።