• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አልቃሻው ሚኒስትር ደኤታ” ኤርምያስ ለገሠ

December 9, 2019 12:17 am by Editor 5 Comments

በሕይወት በነበረበት ጊዜ ኢትዮጵያን ጠርንፎ የነበረውን ኢህአዴግን እንዲያገለግሉ የሚመለመሉ በርካታ ወዶገብ ጥቅመኞች ነበሩ። በአንድ ወቅት ተስፈኛ ካድሬዎችን ለመመልመል ሲኒየሮቹ ካድሬዎች በሄዱበት ክፍለከተማ ከተሰበሰቡት መካከል አንዱ ኤርሚያስ ለገሰ ነበር። በወቅቱ አብሮት የነበረ የቅርብ ወዳጄ እንደሚለው ከሆነ “ደርግን ገረሰስን” የሚሉት ተጋዳላዮች በወቅቱ ደረሰብን በማለት ከመድረኩ ሲያወሩ ኤርሚያስ ከሥር ሆኖ በአራት መዓዘን ያለቅስ ነበር። አገር ለመገንጠል የተነሱት የወንበዴዎች ክምችት “ቁርጠኝነታቸው፣ በቦምብ ላይ መረማመዳቸው፣ አንዱ ለሌላው ልሙት ማለቱ፣…” ነበር ኤርሚያስን ተንሰቅስቆ ያስለቀሰው፤ ይህንኑ ቃል በሌላ ጊዜ ደግሞታል።

ይህንን እንስፍስፍ እጩ ካድሬ ማንነት የጠየቁ መልማዮች ወዲያውኑ በብርሃን ፍጥነት ኤርሚያስን ከክፍለከተማ አስፈነጠሩትና መድረሻውን አሁን በእስር ላይ የሚገኘው በረከት ስምዖን መ/ቤት አደረሱት። በሚመለመልበት ጊዜ ምን ሆኖ ያለቅስ እንደነበር ሲጠየቅ የመለሰውም ከላይ የተባለው የታጋዮቹ ማንነት እንደሆነ ተናግሯል። ምናልባት ድብቅ መረጃዎችን የሚያጋልጠው ስዩም ተሸመ ከእኔ የበለጠ መረጃ ካለው ጀባ ሊል ይችላል።

በዚህ ዓይነት ራሱን ከጥቅም ጋር በማቆራኘት የፈለገውን ሲያደርግ የኖረው ኤርሚያስ ከጠ/ሚ/ር ዐቢይ መንግሥት ላይ በኢህአዴግ/ህወሓት ዘመን የተማረውን የሤራ ፖለቲካ በ360 ሚዲያ ላይ በየቀኑ እየተናገረ አገር በማፍረስ ተግባር ላይ ይገኛል።

በነገራችን ላይ 360 በገንዘብ ከደጎሙትና ከሚደጉሙት አገር አፍራሾች መካከል እነማን እንዳሉበት አንዳንድ መረጃዎች አሉ። ለዛሬ በይደር ይቆይ።

ከዚህ ሌላ ግን ኤርሚያስ ከቴዎድሮስ ጋር በዚሁ 360 ላይ ቀርቦ ሳየው አዘንኩ። ያዘንኩት በኤርሚያስ የካድሬነት ባህርይ ሳይሆን ቴዎድሮስ ማን እንደሆነ ጠንቅቆ እያወቀ ከእርሱ ጋር አብሮ በመሰለፉ ነው። ቴዎድሮስ አዲስ አበባ ከነበረበት ጊዜ ጀምሮ ከወላዋይና እጅግ መሰሪ ባህርዩ በተጨማሪ ተፈጥሮ የነሳቸው ትልቅ ነገር ስላለ በዚያ ላይ ለመጨመር ብዙም አልፈልግም። ነገር ግን በቴዎድሮስ ባህርይ እጅግ ያዘኑት ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ በፌስቡክ ገጻቸው የጻፉትን የሐዘንና የምክር መልዕክት አንባቢያን ሄደው እንዲያነቡት እጋብዛለሁ።

ኤርሚያስ በአዲስ አበባ ላይ የነበረው አመለካከት ምን እንደነበር አውቅ የነበረ ቢሆንም አሁን ግን ከስዩም ተሾመ ጋር ተናጅሶ ከእኔ በበለጠ የመጻፍና የማቀናበር ብቃት ስዩም ያወጣውን መረጃ እዚህ ላይ ለመድገም ተገድጃለሁ።

ይድረስ ለአቶ ኤርሚያስ ለገሰ ዋቅጅራ‼

አቶ ኤርሚያስ ለገሰ (Ermias Legesse Wakjira) ትላንት ከቴድሮስ ፀጋዬ ጋር Ethio 360 Media ላይ ባደረጉት ውይይት እኔን በስም በመጥራት “እጅግ በጣም አደገኛ የሆነ ቡድን አካል እንደሆንኩ ተናግሯል። ከዚህ በተጨማሪ በመረጃና እስከ 500 ሺህ ብር የሚደርስ የገንዘብ ድጋፍ የሚደረግለት የዶ/ር አብይ ጭፍን ደጋፊ እንደሆንኩ በይፋ ተናግሯል። ያው እንደምታውቁት የዚያች ሚጥሚጣ (መኪና) ነገር ብዙ ጣጣ ይዞ መጥቷል።

የመጀመሪያው እንደ ኤርሚያስ ላሉ ሰዎች ወሬ ለመጠረቅ ያመቻቸዋል፣ ሁለተኛው ደግሞ ቀሪውን ሂሳብ መክፈል ተስኖኛል። ይሄው ትላንትና ደሞወዜን ሙጥጥ አድርጌ ከፍዬም ገና 15ሺህ ዕዳ ይቀርብኛል። ይህን ለመክፈል ደግሞ ምን እንዳደረኩ Ben Abera ብትጠይቁት ይነግራችኋል። ስለዚህ አቶ ኤርሚያስ እንደዛሬው ሳይሆን ቀድሞ የነበረንን ወዳጅነት አስበህ ቀሪውን ብትከፍልልኝ መልካም ነው። በዚህ መልኩ የእኔን ስም በማጥፋት የሰራኸው ቪዲዮ ብቻ በትንሹ $500 ዶላር ያስገኛል። እሱን ብትልክልኝ ይበቃኛል።

ወደ ዋናው ነጥብ ልመለስና፤ ኤርሚያስ በዚህ ልክ የወረደ ነገር የተናገረው ተበሳጭቶ ነው። ያበሳጨሁት ደግሞ አንዴ በአሽሙር፣ ሌላ ግዜ ደግሞ ስሙን በመጥቀስ ስለፃፍኩበት ነው። ባለፈው “በማን የሚመራው ቄሮ በሽብርተኝነት ሊፈረጅ ይገባል?” የሚል ነገር ለጥፎ ስመለከት “OMG” ብዬ ኮሜንት አደረኩለት። በውስጥ መስመር መጥቶ “ፅሁፉ ምን ችግር አለው?” አለኝ። እኔም “ቄሮ ማለት ሁሉም ወጣት የኦሮሞ ወጣት ነው። አንድን በሽብርተኝነት ለመፈረጅ ማሰብ በራሱ እብደት ነው” ብዬው ነበር። ነገር ግን ልንግባባ አልቻልንም።

በመጨረሻ “የፀረ ሽብር” አዋጁ ተግባራዊ በማድረግ ሂደት ተሳታፊ እንደነበር በመጥቀስ ከላይ ለጠየቀው ጥያቄ መልሱን ታውቃለህ ብዬ ነቆርኩት። ቀጠለና የኤርሚያስ ስም ሳልጠቅስ ታከለ ኡማ ስልክ ደውሎ ስልጣን ለምኖ ሲያጣ ቀንደኛ ተቃዋሚና የባልደራስ ምክትል እንደሆነ በመጠቆም ሾጥ አረኩት። ነገር ግን ስሙ ስላልተጠቀሰ እሱ መሆኑን የሚያውቁት በጣም ጥቂት ሰዎች ናቸው። ይሁን እንጂ እነ ኤርሚያስ አሁን ባሉበት ሁኔታ ፀብ በደላላ እየፈለጉ ነው። ስሙን ሳልጠቅስ በታናገርኩት ተናድዶ “ስዩም ተሾመ” እያለ በስም ጠቅሶ ሞልጮኛል። እኔ ለራሴ ዛቻና ማስፈራሪያ ይመቸኛል! ስድብና ስም ማጥፋት ይደላኛል።

ኤርሚያስ ስለ እኔ በተናገረው ነገር በጣም እርግጠኛ እንደሆነ ከማንም ጋር ፊት ለፊት ለመከራከር ዝግጁ መሆኑን ገልጿል። አሁን የምጠይቀው፤ 1ኛ) በተናገርከው መሰረት ከእኔ ጋር ክርክር ትገጥማለህ? 2ኛ) አንተ እንደፈለክ ዘርጥጠኝ፣ እኔም እንደፈለኩ ልዘርጥጥህና ተላልጠን ይዋጣልን? ወይስ 3ኛ) በድፍረት ስሜን ስላጠፋህ ይቅርታ ትጠይቀኛለህ? ወዳጄ ልቤ ሆይ፣ ሦስቱም አማራጮች ለእኔ ልዩነት የላቸውም። ስለዚህ የሚበጅህን መርጠህ ታሳውቀኝ ዘንድ እልምንሃለሁ።

ከሠላምታ ጋር፤

ስዩም ተሾመ፤ ስዩመ እግዚያብሔር ዘ-ይምነገደ ኢትዮጵያ

ስም ይህንን ከጻፈ በኋላ ከኤርሚያስ ምላሽ ማግኘቱን ባላውቅም የሚከተለውን መረጃ አተመ፤ ይህ መረጃ በማንበብ ብቻ የኤርሚያስን ማንነት ለመናገር ይቻላል፤ ከላይ እንዳልኩት ይህ የኤርሚያስ አቋም በምንም ዓይነት መስፈርት ከእስክንድር ነጋ ጋር የባልደራስ ምክትል መሆን የሚያስችለው ሳይሆን ከጃዋር ጋር እንዲቆም ወይም መቆም እንዳለበት ግልጽ ማስረጃ የሚሰጥ ነው። እኔ በግሌ ኦሮሚያ በአዲስ አበባ ላይ ልዩ ጥቅም አላት ምናምን የሚባለውን እንደማልቀበል ራሱ ኤርሚያስ ያውቃል፤ ነገር ግን ኤርሚያስ ይህንን ጉድ ተሸክሞ በምን መስፈርት እነ ታከለ ዑማን፣ እነ ለማ መገርሳን፣ እነ ዐቢይ አሕመድን ተረኛና ኦሮሞ እያለ እንደሚከሳቸው ለራሱም የሚያሳፍረው ይመስለኛል፤ የስዩም ተሸመ ጽሁፍ እንዲህ ይነበባል፤

“ዓሳ ጎርጓሪ ዘንዶ ያወጣል ቁ.1” ለኤርሚያስ ለገሰ

ቆይ ቆይ… አቶ ኤርሚያስ ለገሰ (Ermias Legesse Wakjira) የባልደራሱ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ ነው። ባለፈው አመት የባልደራስ ምክር ቤት ዋና ሰብሳቢና መስራች ከሆነው አቶ እስክንድር ነጋ ጋር ነፃ ውይይት ፕሮግራም ላይ በእንግድነት ቀርቦ “የኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ላይ ልዩ ጥቅም የሚባል ነገር የለውም፤ ‘ልዩ ጥቅም’ የሚለው እሳቤ በራሱ በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ላይ የተጋረጠ የዘር/ብሔር መድልዎ ነው” በሚል ሃሳብ አቅርቧል። በእርግጥ በአዲስ አበባ እና ኦሮሚያ ዙሪያ ያለኝን አቋም በፅሁፍና ቃለምልልስ በተደጋጋሚ ገልጬያለሁ። በተመሣሣይ አቶ እስክንድር ነጋ “የኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ላይ ልዩ ጥቅም አለው” የሚለውን እሳቤ አምርሮ እንደሚቃወም የታወቀ ነው። እኔም ሆንኩ እስክንድር በዚህ ጉዳይ ላይ ያለን አቋም የዚህ ፅሁፍ ትኩረት አይደለም። ከዚያ ይልቅ የፅሁፉ ዋና ትኩረት “ከቅርብ ግዜ ወዲህ የባልደራስ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ የሆነው አቶ ኤርሚያስ ለገሰ በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ያለው አቋም ምንድነው?” የሚለው ነው።

ንግግሩን ቃል በቃል ባላስታውስም፣ አቶ ኤርሚያስ ለገሰ የባልደራስ ምክትል ከመሆኑ ቀደም ብሎ “እናቴ ስትኖር አዲስ አበቤ፣ ስትሞት ደግሞ ኦሮሞ እንድትሆን አልፈልግም!” ማለቱ አይዘነጋም። ከዚህ አንፃር “የኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ከተማ ላይ ያለው ልዩ ጥቅም ሊከበርለት ይገባል” የሚለውን እሳቤ አምርሮ እንደሚቃወም መገመት ይቻላል። ነገር ግን ወደኋላ ሸርተት ብለን እ.አ.አ በ2016 ዓ.ም የኦሮሞ ጥናት ማህበር (Oromo Studies Association – OSA) ባዘጋጀው የምክክር መድረክ ላይ የተናገረውን ስንመለከት ደግሞ ናላችን ይዞራል። በዚህ መድረክ ላይ ኤርሚያስ ቃል በቃል “ኮተቤ፥ አቃቂ፥ ካራቆሬ፥… የአዲስ አበባ አይደሉም” በማለት ይናገራል። (ይሄን ጉድ ለመስማት የቸኮለ እዚህ ቪዲዮ ላይ ከ8:00 ደቂቃ ጀምሮ ይመልከት)።

በእርግጥ ለእኔ ወያኔ ለዘረፋ ሲል የሰራው ተንኮል እንጂ አዲስ አበባ የኦሮሚያ፣ ኦሮሚያም የአዲስ አበባ እንደሆነ አምናለሁ። ነገር ግን “የአዲስ አበባ ከተማ አሁን ካላት 54ሺህ ሄክታር መሬት ውስጥ የከተማዋ ትክክለኛ ይዞታ የሆነው 21ሺህ ሄክታር ነው” የሚለው ኤርሚያስ እንዴት የባልደራስ ምክትል የሆነው? “ልዩ ጥቅም የሚባል ነገር የለም!” ከሚለው እስክንድር ነጋ ጋር እንዴትና በምን ቋንቋ ተነጋግረው ነው የተግባቡት? አቶ ኤርሚያስን የባልደራስ ምክትል ሰብሳቢ የሆነው በአዲስ አበባ ስር የተጠቃለሉ የኦሮሚያ መሬቶችን ለማስመለስ ነው ወይስ በውስጡ ያለው የስልጣን ጥማት ህሊናውን ስለጋረደው?

በመጨረሻም ይህን የፃፍኩት የኤርሚያስን ክብርና ዝና ለመንካት አይደለም። ከዚያ ይልቅ “ዝም ብለህ የሰው አናት ላይ ፊጥ አትበል! በቅድሚያ ራስህን መርምርና ከህሊናህ ታረቅ። ይሄን ተምሬያለሁ።፣ ያንን አስተምሬያለሁ ከማለት ይልቅ በሰከነ አዕምሮ ለማሰብ ሞክር፣ በምክንያትና ዕውቀት ላይ የተመሠረተ ወጥ አቋም፣ ከግል ፍላጎትና እልህ የፀዳ አመለካከት ይኑርህ” ለማለት ያህል ነው!

እኔም ይህንን ብዬ ላብቃ፤ ኤርሚያስ በደንብ አድርገህ ታውቀኛለህ፤ በአጻጻፌም እንድታውቀኝ አድርጌአለሁ፤ እየሄድክበት ያለው መንገድ የጨለማ ነው፤ ታከለ ዑማ ስለዘጋህ ዶ/ር ዐቢይን በጭፍን በመቃወም እየሄድከበት ያለው መንገድ ከእነቴዎድሮስ ጋር እንድታብር እያደረገህ ነውና ንቃ! አልረፈደም ተመለስ! ካልፈለግህ ትራምፕን ለመጣል በወሰድከው የአሜሪካ ዜግነት ተጠቅመህ “የትራምፕ ልቃቂት” የመሳሰሉ ጽሁፎች በእንግሊዝኛ እየጻፍክ የዜግነት ድርሻህን ብትወጣ እመክርሃለሁ።

በጣም ስለምታውቀኝ ስሜን አልጠቅስልህም 🙂


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: 360, ermias, jawar, Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. ስሜን አልጠቅስልህም says

    December 9, 2019 07:40 pm at 7:40 pm

    ጎልጉል?

    የዕውነት “ካው ቦይ” ጋዜጠኝነታችሁ እየተገለጠ ነው፤ ኤርሚያስ እንዲህ አለ፤ ስዩም እንዲያ አለው፤ እስክንድር ምን ይላል፤ ቴዎድሮስ ምን መለሰለት – ይሄ ዜና ነው? ተራ ስም ማጥፋት ነው! የወስጥ ልብስና ግልገል ሱሪያቸውን በአደባባይ አጥቦ ማስጣት ተለምዷ ጎልጉልም ይተባበራል – ሕዝብ ተጨባጭ ዕውነተኛ ዜና ነው መስማትና ማንበብ የሚፈልገው እንጂ ይህን ሃሜትና ጉንጭ አልፋ ቀደዳ አደለም

    ለመሆኑ ይህ ምን ማለት ይሆን? መረጃ አለኝ ግን ይቆይ፤ ዕንቁልልጭ ነው?

    “በነገራችን ላይ 360 በገንዘብ ከደጎሙትና ከሚደጉሙት አገር አፍራሾች መካከል እነማን እንዳሉበት አንዳንድ መረጃዎች አሉ። ለዛሬ በይደር ይቆይ።”

    Reply
  2. name says

    December 13, 2019 06:57 pm at 6:57 pm

    Ewww.. How is this article anything more than gossip? Top to bottom “alu`balta”. I suppose this is what happens when technology is fallen under wrong hands. Sad..

    Reply
  3. wolde says

    January 10, 2020 07:52 pm at 7:52 pm

    betam yasazinal. Endih aynet yetechemaleke hateta.

    Reply
  4. Hale says

    January 12, 2020 04:38 pm at 4:38 pm

    Alubaltegnoch lekas zibazinke new yemtawerut kkk ye Ermin yegir etabi athonum ye Abiy mirkognoch

    Reply
  5. George says

    September 23, 2020 06:16 am at 6:16 am

    you are rubbish no. 1 !!!!!!!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule