ያለፈው አርብ መስከረም 18፤2011ዓም የባንኩን ሁኔታ አስመልክቶ ከፍተኛ ኃላፊዎቹ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተገለጸው ባንኩ ባለፉት አምስት ተከታታይ ዓመታት ካበደረው 40በመቶ የሚሆነው የተበላሸ ብድር መሆኑን ተናግረዋል። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ከባንኩ መረጃ አቀባዮች ባገኘው መረጃ መሠረት በሁለት ዓመታት ብቻ ባንኩ ለባለሃብቶች አበድሮ የተበላሸው ብድር መጠን 6.37 ቢሊየን ብር መድረሱን ለማወቅ ተችሏል። ይህም ካለፉት አምስት ዓመታት የተበላሸ ብድር ጋር ሲነጻጸር በከፍተኛ መጠን ያደገ ሲሆን በአምስቱ ዓመታት በድምሩ ወደ 20ቢሊዮን የሚጠጋ ብር የተበላሸ ብድር ሆኗል። የኃላፊዎቹን መግለጫ የተከታተለው ሪፖርተር እንደዘገበው “በ2007 ዓ.ም. 12.5 በመቶ የነበረው የተበላሸ የብድር መጠን በ2008 ዓ.ም. ወደ 17.7 በመቶ አድጓል። በ2009 ዓ.ም. የተበላሸ የብድር … [Read more...] about የኢትዮጵያ ልማት ባንክ 20ቢሊየን ብር ብድር የተበላሸና የማይመለስ ሆኗል
Archives for September 2018
የኢህአዴግ የመጨረሻ ጉባኤ…
ኢህአዴግ መሽቶበታል። አቅሙ ክዶታል። ባልሞት ባይ ተጋዳይነት አለሁ ቢልም ዘላለማዊ ዕንቅልፉ ግን የሚቀርለት አይመስልም። የሜክሲኮውን ፒ አር አይ ፓርቲ አርአያው አድርጎ ሰባ አመታትን እጓዛለሁ ብሎ የተነሳው ድርጅት ግማሽ መንገድ እንኳን ሳይጓዝ ሊፈርስ ከጫፍ ደርሷል። ገዥው ፓርቲ ውስጥ ያለው የርዕዮተዓለም ልዩነት በማይታረቅ መንገድ የአደባባይ ሙግት ጀምሯል። ኦዲፒ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ መማል ካቆመ ቆይቷል። ሊቀመንበሩ ዓብይ አህምድም (ዶ/ር) ከትናንት ጋር የተኳረፉት ለዚህ ይመስላል። ብአዴን የምመራበትን ርዕዮተ ዓለም ዳግም አጤነዋለሁ ብሎ ዛሬ መወያየቱን ጀምሯል (ይህ ዘገባ ከተጻፈ በኋላ ብአዴን አዴፓ በሚል ህወሓት የሰጠውን ቀይሮታል)። ከዚህ በአንጻሩ ህወሓት አብዮታዊ ዲሞክራሲን ብረሳ ቀኜ ትርሳኝ ብሎ ሙጥኝ ማለትን ወዷል። ደኢህዴን ሁለት ጎራ ይዞ የለየለት ፍልሚውን … [Read more...] about የኢህአዴግ የመጨረሻ ጉባኤ…
መንገዳችን በፍጥነት ይቃና!
በብዙ ዓይነት ወንጀሎች የሚታሙት የወያኔ አዛዦች ሥልጣናቸውን እንደያዙ ከሥልጣን ወረዱ ቢባል ግራ ይሆናል፤ ነገር ግን ሆነ! በሕጋዊ ምርመራ ሳይጣራና ከሳሾቹን በፍርድ ቤት ሳይሞግት የሰው ልጅ እንደከብት ከመንገድ በጉልበተኞች እየተያዘ መታሰር የቀረ መስሎን ነበር፤ አልቀረም አሉ! ጉልበተኞች በወንጀላቸው ክብደት ከሕግ ይከለላሉ ይባል ነበር፤ አሁንም ያው ይመስላል! ያነበብሁትን በትክክል ካስታወስሁት በጥንታውያን ግሪኮች ሰርቀው መያዝ እንጂ መስረቅ ወንጀል አልነበረም (የምታስታውሱ አርሙት)፤ የምንመሳሰለው በጥንታዊነት ብቻ መስሎኝ ነበር! ከዚህ ቀደም ጸጋዬ ገብረ መድኅን (ይመስለኛል) ተረግመናል ብሎ፤ ነበር፤ እኔንም መሰለኝ! ኢትዮጵያውያን መልካቸውን፣ ነብሮች ቆዳቸውን እንዴት ይለውጣሉ ያለው መልካችንን ነበር፣ ወይስ ጠባያችንን ማለቱ ነበር! ነገሬ ሁሉ የጥንቶቹን አባትና እናት … [Read more...] about መንገዳችን በፍጥነት ይቃና!
ኢትዮጵያዊነትና የብሔር ማንነት ተደጋጋፊ ወይስ ተገዳዳሪ?
“ኢትዮጵያ አገራችን የየራሳችን አኩሪ ባህል ያለን፣ የየራሳችን መልክዓ ምድር፣ አሰፋፈር የነበረንና ያለን፣ ብሔር ብሐረሰቦችና ሕዝቦች በተለያዩ መስኮችና የግንኙነት ደረጃዎች ተሳስረን አብረን የኖርንባትና የምንኖርባት አገር በመሆንዋ ያፈራነው የጋራ ጥቅምና አመለካከት አለን ብለን ስለምናምን፣ መጪው የጋራ ዕድላችን መመሥረት ያለበት ከታሪካችን የወረስነውን የተዛባ ግንኙነት በማረምና የጋራ ጥቅማችንን በማሳደግ ላይ መሆኑን በመቀበል ጥቅማችንን፣ መብታችንንና ነፃነታችንን በጋራና በተደጋጋፊነት ለማሳደግና አንድ የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ የመገንባቱን አስፈላጊነት በማመን እኛ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ይኼንን ሕገ መንግሥት በተወካዮቻቸው አማካይነት አፅድቀነዋል።” ከላይ የተገለጸው በ1987 ዓ.ም. ከፀደቀው የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት መግቢያ ላይ የተወሰደና አገሪቱ ካለፉት 23 … [Read more...] about ኢትዮጵያዊነትና የብሔር ማንነት ተደጋጋፊ ወይስ ተገዳዳሪ?
በባንዲራና አርማ ዙርያ ያሉ ውዝግቦች
ባንዲራ የአንድ አገር ሕዝብ ማንነት መገለጫ ነው። የሰው ልጆች በታሪካቸው ውስጥ የየራሳቸውን ቡድን ወይም ወገን ከሌሎች ለመለየት ጨርቅን በተለያዩ ቀለሞች በመቀባት፣ እንጨት ላይ ሰክተው በእጃቸው ይዘው በመዞር፣ አንገታቸው ላይ በማሰር ወይም ጎልቶ እንዲታይ ከማሰብ አንጻር ረዘም ባሉ እንጨቶች ላይ እየሰቀሉ ከማንነት መገለጫም ባሻገር ይዞታን ወይም ባለቤትነትን ለማረጋገጥ ይጠቀሙበት እንደነበር የሕብረተሰብ ታሪኮች መዝግበዋል። ባገራችን ባንዲራ እንደ ኢትዮጵያ መገለጫ ሆኖ መቼ እንደቀረበ በትክክል ባይታወቅም፣ ባንዲራን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ለመጀመርያ ጊዜ ያስተዋወቁት አጼ ምኒልክ መሆናቸው በሰፊው ይነገራል። ያኔ ትክክለኛ ስሙ “ሰንደቅ ዓላማ” በመባል ቢታወቅም፣ ጣሊያኖች ኢትዮጵያን ከወረሩ በኋላ ግን “ባንዲራ” በሚለው የጣሊያንኛ ቃል ተተክቶ ዛሬ በስፋት እየተጠቀምንበት ነው። … [Read more...] about በባንዲራና አርማ ዙርያ ያሉ ውዝግቦች
የጎሳ ፖለቲካ ጣጣ፣ ‘ሀዘናችን ቅጥ አጣ’
ከአንድ ሃዘን ወደ ሌላ፤ ላለፉት ጥቂት ወራት ክልላትን እያዳረሰ ያለውና ጎሳ ላይ ያነጣጠረው ግጭት ከቡራዩ ሃዘን ሳናገግም በዚህ ሳምንት ደግሞ ዳግም ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ዞረ። በክልሉ ይኖሩ የነበሩ የኦሮሞ፣ አማራ እና የሌሎች ብሔር ተወላጆች ላይ ሌላ አስከፊ ጥቃት መፈጸሙን መርዶ ሰማን። ሰዎች ተገድለዋል፤ በአሥር ሺዎች ተፈናቅለዋል። ለዚህም ጥቃት የተለያዩ ኃይሎች እንደ ምክንያት እየተጠቀሱ ነው። ከእንዲህ ያለው አስነዋሪ እና እጅግ ኋላ ቀር ከሆነ የጎጠኝነት ስሜት እንዴት ይሆን የምንላቀቀው? በጎጥ ጥላቻ ላይ ምህለቁን የጣለው ዘር ተኮር ፖለቲካችንስ መቼ ይሆን የሚጸዳው? ከእንዲህ ያለው ቅርቃር ለመውጣት እንደ ሰው ማሰብ ብቻ ይበቃን ነበር። ከዚያም ሲያልፍ የአንድ አገር ልጆች በመሆናችን ብቻ ልንተዛዘን፣ ልንደጋገፍ እና አብረን ልንኖር በቻልን ነበር። ይህ ሁሉ ቢቀር በየጎሳ … [Read more...] about የጎሳ ፖለቲካ ጣጣ፣ ‘ሀዘናችን ቅጥ አጣ’
የጠብ ሱስ
ከጅብ ከበሮ የተሰራ አታሞ ዘወትር እንብላው፤ እንብላው ይላል የሚል ተረት ሰምቻለሁ ልበል? አዎ፤ ሳልሰማ አልቀርም። ሀሳቡም ግን ጅብ ቆዳ ሆኖ እንኳን (ቆዳ ሆኖ ብቻ አይደለም አታሞ ተለጉሞበትም) ያው የተፈጥሮ እንብላ ባይ ባህሪውን አይተውም ማለት ይመስለኛል። ያው ቢሞትም ቆዳው የጅብ ነዋ። ይህን ምሳሌ ያስታወሰኝ የሰሞኑ የአምስት የዖሮሞ ድርጅቶች ያወጡት ጠብ ያለሽ በዳቦ አይነት መግለጫ ነው። በእርግጥ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ድርጅቶች አይነተኛ ተግባር ምናልባትም ቋሚ ስራ መግለጫ ማውጣት ስለሆነ ድርጅቶቹ ያው እንደለመደው ሰብሰብ ብለው እስቲ መግለጫ እናውጣ ቢሉ ያባት ይባል ነበር። የነዚህኞቹ ግን የዘር አዋጅ እንጂ መግለጫ የሚባል ስላልሆነ በእውነቱ በጥብቅ የሚያነጋግርም የሚያስተዛዝብም ምናልባትም ደግሞ ህግ ካለም በህግ የሚያስጠይቅ ግዴለም አቅልለን እንመልከተው ካልን ደግሞ … [Read more...] about የጠብ ሱስ
“ኦሮሞ የሞተላትን አገር ጥሎ ወዴትም አይገነጠልም! ኦሮሞ ከኢትዮጵያ ውጭ አገር የለውም! አይኖረውም!” ዐቢይ አሕመድ
ህወሓት የሰየመለትን ስም፣ ዓርማና መዝሙር በማስወገድ ራሱን ነጻ ያወጣው የቀድሞው ኦህዴድ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዴፓ) የሚል ስያሜ በመውሰድ አዲስ ፓርቲ ሆኗል፤ የሚከተሉትን የኦዴፓ/ኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት በማድረግ መርጧል 1. ዶክተር አብይ አህመድ፤ 2. አቶ ለማ መገርሳ፤ 3. ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ፤ 4. አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ፤ 5. ወይዘሮ አዳነች አቤቤ፤ 6. አቶ አዲሱ አረጋ፤ 7. አቶ ሽመልስ አብዲሳ፤ 8. አቶ ፍቃዱ ተሰማ፤ 9. ዶክተር ዓለሙ ስሜ። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የሚከተሉትን 55 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላትን መርጧል፤ እስካሁን ይፋ በሆነው የምርጫ ውጤት መሰረትም፦ ዶክተር አብይ አህመድ አቶ ለማ መገርሳ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ኢንጂነር ታከለ ኡማ አቶ ሽመልስ … [Read more...] about “ኦሮሞ የሞተላትን አገር ጥሎ ወዴትም አይገነጠልም! ኦሮሞ ከኢትዮጵያ ውጭ አገር የለውም! አይኖረውም!” ዐቢይ አሕመድ