• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢህአዴግ የመጨረሻ ጉባኤ…

September 30, 2018 06:26 pm by Editor Leave a Comment

ኢህአዴግ መሽቶበታል። አቅሙ ክዶታል። ባልሞት ባይ ተጋዳይነት አለሁ ቢልም ዘላለማዊ ዕንቅልፉ ግን የሚቀርለት አይመስልም።

የሜክሲኮውን ፒ አር አይ ፓርቲ አርአያው አድርጎ ሰባ አመታትን እጓዛለሁ ብሎ የተነሳው ድርጅት ግማሽ መንገድ እንኳን ሳይጓዝ ሊፈርስ ከጫፍ ደርሷል። ገዥው ፓርቲ ውስጥ ያለው የርዕዮተዓለም ልዩነት በማይታረቅ መንገድ የአደባባይ ሙግት ጀምሯል።

ኦዲፒ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ መማል ካቆመ ቆይቷል። ሊቀመንበሩ ዓብይ አህምድም (ዶ/ር) ከትናንት ጋር የተኳረፉት ለዚህ ይመስላል። ብአዴን የምመራበትን ርዕዮተ ዓለም ዳግም አጤነዋለሁ ብሎ ዛሬ መወያየቱን ጀምሯል (ይህ ዘገባ ከተጻፈ በኋላ ብአዴን አዴፓ በሚል ህወሓት የሰጠውን ቀይሮታል)። ከዚህ በአንጻሩ ህወሓት አብዮታዊ ዲሞክራሲን ብረሳ ቀኜ ትርሳኝ ብሎ ሙጥኝ ማለትን ወዷል። ደኢህዴን ሁለት ጎራ ይዞ የለየለት ፍልሚውን ቀጥሏል።

የኢህአዴግ እህት ድርጅቶችን የተካረረ አቋም ለተመለከተ ሰው ኢህአዴግ በመፍረስ ጫፍ ላይ መሆኑን በውሉ ይረዳል። የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር አንድ የፖለቲካ ፕሮግራም ያስተሳሰረው ድርጅት መሆኑ ይታወቃል። ይህ ፕሮግራም ሁሉንም እህት ድርጅቶች ለአንድ ዓላማ ያሰለፈ የህልውና መገለጫ ተደርጎ የሚቆጠር ነው።

አብዮታዊ ዲሞክራሲ የሚል የዳቦ ስም ያለው ይህ የግንባሩ መሰሶ ከተናጋ ቤቱ መናዱ እንደማይቀር ዕሙን ነው። ለዚህ ደግሞ የድርጅቱ መተዳደሪያ ደንብ ትልቅ ምስክር ነው።

ኢህአዴግ በመተዳደሪያ ደንቡ ላይ “ኢህአዴግ የሚመራባቸው አጠቃላይ የአደረጃጀት መርሆዎች” በሚል ንዑስ ርዕስ ስር “ኢህአዴግ ለአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ አላማ ተግባራዊነት የሚንቀሳቀስ ድርጅት ስለሆነ በአባልነት ሊቀበልና ሊያሰባስብ የሚችለው አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ አላማን በግልፅ በፕሮግራማቸው ላይ የቀረፁ ድርጅቶችን ብቻ ነው”ይላል። የገዥው ፓርቲ የአባልነት መሰፈርት የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ፕሮግራምን ዓላማ ማድረግ ብቻ ሳይሆን በውሉ ለተግባራዊነቱ መረባረብን ይጠይቃል። ይህ የፓርቲው ምሰሶ ዛሬ እንደ ደመራ በአንድ አቅጣጫ ዘሟል። የሚጠበቀውም መቼና በየት በኩል ይወድቃል የሚለው ብቻ ነው።

በየት በኩል ይወድቃል?

ኢህአዴግ በወረቅት ላይ ለጋስ ፓርቲ ከሚባሉት ተርታ የሚሰለፍ ነው። በዚህ ምክንያትም ማንም እህት ድርጅት ከኢህአዴግ አባልነት በፈለገው ጊዜ መውጣት እንደሚችል በመተዳደሪያ ደንቡ ላይ አስፍሯል። በድርጅቱ ህግ አንቀጽ 13/2 ሀ. “ማንኛውም የግንባሩ አባል የሆነ ድርጅት ለግንባሩ ምክር ቤት አሳውቆ በፈለገው ጊዜ ድርጅቱን መልቀቅ ይችላል” ይላል። ዛሬ ኢህአዴግ ቤት ያለው መፈራራት ማን ቀድሞ እንዲህ ያለውን ኃላፊነት ይወስዳል የሚለው ነው። ነገርየው ደመራው በየት በኩል ይወድቃል የሚልን ጉጉት ያጭራል።  ከዚህ ከፍ ሲልም ከኢህአዴግ ቤት የወጣ ድርጅት ከማን ጋር ተጣምሮ መንግስት ሊመሰርትስ ይችላል የሚል ጥያቄም ያስከትላል።

ብዙዎች ኢህአዴግ ከወደቀ የሚወደቀው በኦዴፓ አልያም በብአዴን (በአሁኑ አዴፓ) በኩል ነው የሚል ሀሳብ ይሰነዝራሉ። ኢህአዴግ ከፈረሰ በኋላም በጥምረት መንግስት የመመስረት ያላቸው ክልል ተሻጋሪ አጀንዳ ያላቸው ፓርቲዎች እነሱ ናቸው ይላሉ። ይህ ግን ከፖለቲካ ካፒታል ጽንሰ ሀሳብ አንጻር ከተመለከትነው ትልቅ ስህተት የሚሆን ይመስለኛል። ሁለቱ ድርጅቶች የየአካባቢያቸውን ህዝብ ድጋፍ ለማግኘት የሚሄዱበት መንገድ ለየቅል ነው። የሁለቱ ክልል ፖለቲካ ልሂቃን የብሄርተኝነት አረዳዳም በሁለት ጫፍ ላይ የቆመ ነው።

ሊበራሊዝም ርዕዮተ ዓለም ጥላ ሁኖ ያስተሳስራቸዋል የሚለው ግምትም ከብሄር ወደ መደብ ላልተሸጋገረ ህዝብ ፖለቲከኛ የሚያዋጣ አይደለም። ከዚህ አንጻር ሁለቱ ፓርቲዎች ከኢህአዴግ ቤት ከመውጣት በላይ አንድ ሊያደርጋቸው የሚችል የፖለቲካ ርዕዮትን የመንደፍ ከባድ የቤት ስራ ይጠብቃቸዋል።

በእኔ ግምት የኢህአዴግን የዘንድሮውን ጉባዔ ለየት የሚያደርገው በዚህ አጣብቂኝ መኃል መገኘቱ ነው። ዛሬ ላይ ቢያንስ አንድ ነገርን በእርግጠኝነት መናገር የሚቻል ይመስለኛል። ኢህአዴግ በ2013 ዓ.ም የሚያደርገው ጉባዔ እንደቀደመው ጊዜው አራት እህት ድርጅቶቹን ይዞ የሚካሄድ አይሆንም።

ይህ ከዛሬ ነባራዊ ሁኔታ በመነሳት የሚደረግ የፖለቲካ እንድምታ ነው። ይህ የእንድምታ ፍካሬ ግን ብቸኛ አይደለም። የገዥው ፓርቲ አፈለኛ አመራር ከርዕዮተ-ዓለም በላይ የስልጣን ጥቅም ያስተሳሰረው ከሆነ ኢህአዴግ የጣር ድምጽ እያስማም ቢሆን ሊጓዝ ይችላል። እንዲህ ያለው መንገድ ግን የኢትዮጵያን ፖለቲካ በተቃዋሚዎች ብቻ ሳይሆን በኢህአዴግ ውስጥ ባለ አለመግባባትም ወደለየለት ምስቅልቅል ይወስደዋል። የሀገር ህልፈትንም ሊያስከትል ይችላል። (ማዕረግ ጌታቸው በድሬቲዩብ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule