• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢህአዴግ የመጨረሻ ጉባኤ…

September 30, 2018 06:26 pm by Editor Leave a Comment

ኢህአዴግ መሽቶበታል። አቅሙ ክዶታል። ባልሞት ባይ ተጋዳይነት አለሁ ቢልም ዘላለማዊ ዕንቅልፉ ግን የሚቀርለት አይመስልም።

የሜክሲኮውን ፒ አር አይ ፓርቲ አርአያው አድርጎ ሰባ አመታትን እጓዛለሁ ብሎ የተነሳው ድርጅት ግማሽ መንገድ እንኳን ሳይጓዝ ሊፈርስ ከጫፍ ደርሷል። ገዥው ፓርቲ ውስጥ ያለው የርዕዮተዓለም ልዩነት በማይታረቅ መንገድ የአደባባይ ሙግት ጀምሯል።

ኦዲፒ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ መማል ካቆመ ቆይቷል። ሊቀመንበሩ ዓብይ አህምድም (ዶ/ር) ከትናንት ጋር የተኳረፉት ለዚህ ይመስላል። ብአዴን የምመራበትን ርዕዮተ ዓለም ዳግም አጤነዋለሁ ብሎ ዛሬ መወያየቱን ጀምሯል (ይህ ዘገባ ከተጻፈ በኋላ ብአዴን አዴፓ በሚል ህወሓት የሰጠውን ቀይሮታል)። ከዚህ በአንጻሩ ህወሓት አብዮታዊ ዲሞክራሲን ብረሳ ቀኜ ትርሳኝ ብሎ ሙጥኝ ማለትን ወዷል። ደኢህዴን ሁለት ጎራ ይዞ የለየለት ፍልሚውን ቀጥሏል።

የኢህአዴግ እህት ድርጅቶችን የተካረረ አቋም ለተመለከተ ሰው ኢህአዴግ በመፍረስ ጫፍ ላይ መሆኑን በውሉ ይረዳል። የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር አንድ የፖለቲካ ፕሮግራም ያስተሳሰረው ድርጅት መሆኑ ይታወቃል። ይህ ፕሮግራም ሁሉንም እህት ድርጅቶች ለአንድ ዓላማ ያሰለፈ የህልውና መገለጫ ተደርጎ የሚቆጠር ነው።

አብዮታዊ ዲሞክራሲ የሚል የዳቦ ስም ያለው ይህ የግንባሩ መሰሶ ከተናጋ ቤቱ መናዱ እንደማይቀር ዕሙን ነው። ለዚህ ደግሞ የድርጅቱ መተዳደሪያ ደንብ ትልቅ ምስክር ነው።

ኢህአዴግ በመተዳደሪያ ደንቡ ላይ “ኢህአዴግ የሚመራባቸው አጠቃላይ የአደረጃጀት መርሆዎች” በሚል ንዑስ ርዕስ ስር “ኢህአዴግ ለአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ አላማ ተግባራዊነት የሚንቀሳቀስ ድርጅት ስለሆነ በአባልነት ሊቀበልና ሊያሰባስብ የሚችለው አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ አላማን በግልፅ በፕሮግራማቸው ላይ የቀረፁ ድርጅቶችን ብቻ ነው”ይላል። የገዥው ፓርቲ የአባልነት መሰፈርት የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ፕሮግራምን ዓላማ ማድረግ ብቻ ሳይሆን በውሉ ለተግባራዊነቱ መረባረብን ይጠይቃል። ይህ የፓርቲው ምሰሶ ዛሬ እንደ ደመራ በአንድ አቅጣጫ ዘሟል። የሚጠበቀውም መቼና በየት በኩል ይወድቃል የሚለው ብቻ ነው።

በየት በኩል ይወድቃል?

ኢህአዴግ በወረቅት ላይ ለጋስ ፓርቲ ከሚባሉት ተርታ የሚሰለፍ ነው። በዚህ ምክንያትም ማንም እህት ድርጅት ከኢህአዴግ አባልነት በፈለገው ጊዜ መውጣት እንደሚችል በመተዳደሪያ ደንቡ ላይ አስፍሯል። በድርጅቱ ህግ አንቀጽ 13/2 ሀ. “ማንኛውም የግንባሩ አባል የሆነ ድርጅት ለግንባሩ ምክር ቤት አሳውቆ በፈለገው ጊዜ ድርጅቱን መልቀቅ ይችላል” ይላል። ዛሬ ኢህአዴግ ቤት ያለው መፈራራት ማን ቀድሞ እንዲህ ያለውን ኃላፊነት ይወስዳል የሚለው ነው። ነገርየው ደመራው በየት በኩል ይወድቃል የሚልን ጉጉት ያጭራል።  ከዚህ ከፍ ሲልም ከኢህአዴግ ቤት የወጣ ድርጅት ከማን ጋር ተጣምሮ መንግስት ሊመሰርትስ ይችላል የሚል ጥያቄም ያስከትላል።

ብዙዎች ኢህአዴግ ከወደቀ የሚወደቀው በኦዴፓ አልያም በብአዴን (በአሁኑ አዴፓ) በኩል ነው የሚል ሀሳብ ይሰነዝራሉ። ኢህአዴግ ከፈረሰ በኋላም በጥምረት መንግስት የመመስረት ያላቸው ክልል ተሻጋሪ አጀንዳ ያላቸው ፓርቲዎች እነሱ ናቸው ይላሉ። ይህ ግን ከፖለቲካ ካፒታል ጽንሰ ሀሳብ አንጻር ከተመለከትነው ትልቅ ስህተት የሚሆን ይመስለኛል። ሁለቱ ድርጅቶች የየአካባቢያቸውን ህዝብ ድጋፍ ለማግኘት የሚሄዱበት መንገድ ለየቅል ነው። የሁለቱ ክልል ፖለቲካ ልሂቃን የብሄርተኝነት አረዳዳም በሁለት ጫፍ ላይ የቆመ ነው።

ሊበራሊዝም ርዕዮተ ዓለም ጥላ ሁኖ ያስተሳስራቸዋል የሚለው ግምትም ከብሄር ወደ መደብ ላልተሸጋገረ ህዝብ ፖለቲከኛ የሚያዋጣ አይደለም። ከዚህ አንጻር ሁለቱ ፓርቲዎች ከኢህአዴግ ቤት ከመውጣት በላይ አንድ ሊያደርጋቸው የሚችል የፖለቲካ ርዕዮትን የመንደፍ ከባድ የቤት ስራ ይጠብቃቸዋል።

በእኔ ግምት የኢህአዴግን የዘንድሮውን ጉባዔ ለየት የሚያደርገው በዚህ አጣብቂኝ መኃል መገኘቱ ነው። ዛሬ ላይ ቢያንስ አንድ ነገርን በእርግጠኝነት መናገር የሚቻል ይመስለኛል። ኢህአዴግ በ2013 ዓ.ም የሚያደርገው ጉባዔ እንደቀደመው ጊዜው አራት እህት ድርጅቶቹን ይዞ የሚካሄድ አይሆንም።

ይህ ከዛሬ ነባራዊ ሁኔታ በመነሳት የሚደረግ የፖለቲካ እንድምታ ነው። ይህ የእንድምታ ፍካሬ ግን ብቸኛ አይደለም። የገዥው ፓርቲ አፈለኛ አመራር ከርዕዮተ-ዓለም በላይ የስልጣን ጥቅም ያስተሳሰረው ከሆነ ኢህአዴግ የጣር ድምጽ እያስማም ቢሆን ሊጓዝ ይችላል። እንዲህ ያለው መንገድ ግን የኢትዮጵያን ፖለቲካ በተቃዋሚዎች ብቻ ሳይሆን በኢህአዴግ ውስጥ ባለ አለመግባባትም ወደለየለት ምስቅልቅል ይወስደዋል። የሀገር ህልፈትንም ሊያስከትል ይችላል። (ማዕረግ ጌታቸው በድሬቲዩብ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule