• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መንገዳችን በፍጥነት ይቃና!

September 30, 2018 02:02 am by Editor Leave a Comment

በብዙ ዓይነት ወንጀሎች የሚታሙት የወያኔ አዛዦች ሥልጣናቸውን እንደያዙ ከሥልጣን ወረዱ ቢባል ግራ ይሆናል፤ ነገር ግን ሆነ! በሕጋዊ ምርመራ ሳይጣራና ከሳሾቹን በፍርድ ቤት ሳይሞግት የሰው ልጅ እንደከብት ከመንገድ በጉልበተኞች እየተያዘ መታሰር የቀረ መስሎን ነበር፤ አልቀረም አሉ! ጉልበተኞች በወንጀላቸው ክብደት ከሕግ ይከለላሉ ይባል ነበር፤ አሁንም ያው ይመስላል! ያነበብሁትን በትክክል ካስታወስሁት በጥንታውያን ግሪኮች ሰርቀው መያዝ እንጂ መስረቅ ወንጀል አልነበረም (የምታስታውሱ አርሙት)፤ የምንመሳሰለው በጥንታዊነት ብቻ መስሎኝ ነበር!

ከዚህ ቀደም ጸጋዬ ገብረ መድኅን (ይመስለኛል) ተረግመናል ብሎ፤ ነበር፤ እኔንም መሰለኝ! ኢትዮጵያውያን መልካቸውን፣ ነብሮች ቆዳቸውን እንዴት ይለውጣሉ ያለው መልካችንን ነበር፣ ወይስ ጠባያችንን ማለቱ ነበር!

ነገሬ ሁሉ የጥንቶቹን አባትና እናት ይህንን የተሸከምነውን ጉድና ነውር ጫኑብን ለማለት እንዳመስላችሁ፤ እነሱ ሊጭኑብን የፈለጉት ክብርንና ኩራትን ነበር፤ ነገር ግን አህያ ወላጆቻችንን እያገለገለች ዱላን የመቻል ትእግስትዋና በዘመናት ለከፈለችው መስዋዕትነት ክብርንና ኩራትን ስትወርስ አበሻ ‹‹አባባ እግርዎትን!›› (ከቃሊቲ የደረጀ ሀብተ ወልድ ትምህርት ቤት የተገኘ እውቀት!) እያለ መለቃቀሙን መረጠ!

የወደቀ ከማንሣት የጣሉትን ማንሣት የሚያኮራና የሚያስከብር ይመስለኛል፤ የጣሉትን ማንሣት ራስን የማረም እርምጃም ነው፤ ራስን ማረም ራስን ማቃናት ነው፡፡

ላለፉት ሦስት ወራት የኢትዮጵያ ሕዝብ በፍቅር፣ በምሕረትና በይቅርታ፣ በመረዳዳትና በተስፋ ንግግሮችና በማይናቁ ድርጊቶች አንገቱን ቀና፣ ደረቱን ነፋ ማድረግ ጀምሮ ነበር፤ ለአዲስ ሥራና ለአዲስ እድገት በአዲስ መንፈስና ደበአዲስ ኃይል ታጥቆ እየተሰናዳ ነበር፤ ለማ መገርሳና ዓቢይ አህመድ የእግዚአብሔር መልእክተኞች መስለው የታዩበት ጊዜ ነበር፤ ነገር ግን በአጭር ጊዜ ውስጥ ላባቸው እየረገፈ ለብዙው ሰው ከመሬት መነሣት እያቃታቸው እየመሰለ ነው፡፡

የአገሩ ችግር ውስብስብ መሆኑ እየታወቀ ብዙ ቡድኖች የበለጠ ውስብስብ እያደረጉት ነው፤ ምክንያቱ የተሰወረ አይደለም፤ የሥልጣን ሰይፍና የጠገራ ብር ቀልቀሎ ነው፤ ሁለቱንም እየተስገበገቡ በመሻማት እርስበርሳቸው ለመጠፋፋት የሚተራመሱት ከራሳቸው በላይ ነፋስ ነው!

ለማና ዓቢይ አዲሱ የፖለቲካ ፍልስፍነናቸው ከሁለት ሺህ ዓመታት በላይ ዕድሜ እንዳለው ያውቃሉ፤ ሁላችንም እናውቃለን፤ ለማና ዓቢይ በስንት ወራት የሁለት ሺህ ዓመታቱን ትምህርት ሊያገባድዱ እንዳቀዱ የሚያውቁት እነሱና የላካቸው አምላክ ብቻ ነው፤ እንደጅምራቸው ከሆነ ግን ለማና ዓቢይም እንደክርስቶስ ከሁለት ሺህ ዓመታት በላይ ሳያስፈልጋቸው አይቀርም! እግዚአብሔር አቋራጩን መንገድ ይግለጽላቸው፡፡

ሕግና ሰይፍ የባሕርይ ዝምድና አላቸው፤ ዝምድናቸውም በጣም የጠነከረ ከመሆኑ የተነሣ አንዱ በሌለበት ሌላኛውም የለም፡፡

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
መስከረም 2011

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column, prof mesfin

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule