• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መንገዳችን በፍጥነት ይቃና!

September 30, 2018 02:02 am by Editor Leave a Comment

በብዙ ዓይነት ወንጀሎች የሚታሙት የወያኔ አዛዦች ሥልጣናቸውን እንደያዙ ከሥልጣን ወረዱ ቢባል ግራ ይሆናል፤ ነገር ግን ሆነ! በሕጋዊ ምርመራ ሳይጣራና ከሳሾቹን በፍርድ ቤት ሳይሞግት የሰው ልጅ እንደከብት ከመንገድ በጉልበተኞች እየተያዘ መታሰር የቀረ መስሎን ነበር፤ አልቀረም አሉ! ጉልበተኞች በወንጀላቸው ክብደት ከሕግ ይከለላሉ ይባል ነበር፤ አሁንም ያው ይመስላል! ያነበብሁትን በትክክል ካስታወስሁት በጥንታውያን ግሪኮች ሰርቀው መያዝ እንጂ መስረቅ ወንጀል አልነበረም (የምታስታውሱ አርሙት)፤ የምንመሳሰለው በጥንታዊነት ብቻ መስሎኝ ነበር!

ከዚህ ቀደም ጸጋዬ ገብረ መድኅን (ይመስለኛል) ተረግመናል ብሎ፤ ነበር፤ እኔንም መሰለኝ! ኢትዮጵያውያን መልካቸውን፣ ነብሮች ቆዳቸውን እንዴት ይለውጣሉ ያለው መልካችንን ነበር፣ ወይስ ጠባያችንን ማለቱ ነበር!

ነገሬ ሁሉ የጥንቶቹን አባትና እናት ይህንን የተሸከምነውን ጉድና ነውር ጫኑብን ለማለት እንዳመስላችሁ፤ እነሱ ሊጭኑብን የፈለጉት ክብርንና ኩራትን ነበር፤ ነገር ግን አህያ ወላጆቻችንን እያገለገለች ዱላን የመቻል ትእግስትዋና በዘመናት ለከፈለችው መስዋዕትነት ክብርንና ኩራትን ስትወርስ አበሻ ‹‹አባባ እግርዎትን!›› (ከቃሊቲ የደረጀ ሀብተ ወልድ ትምህርት ቤት የተገኘ እውቀት!) እያለ መለቃቀሙን መረጠ!

የወደቀ ከማንሣት የጣሉትን ማንሣት የሚያኮራና የሚያስከብር ይመስለኛል፤ የጣሉትን ማንሣት ራስን የማረም እርምጃም ነው፤ ራስን ማረም ራስን ማቃናት ነው፡፡

ላለፉት ሦስት ወራት የኢትዮጵያ ሕዝብ በፍቅር፣ በምሕረትና በይቅርታ፣ በመረዳዳትና በተስፋ ንግግሮችና በማይናቁ ድርጊቶች አንገቱን ቀና፣ ደረቱን ነፋ ማድረግ ጀምሮ ነበር፤ ለአዲስ ሥራና ለአዲስ እድገት በአዲስ መንፈስና ደበአዲስ ኃይል ታጥቆ እየተሰናዳ ነበር፤ ለማ መገርሳና ዓቢይ አህመድ የእግዚአብሔር መልእክተኞች መስለው የታዩበት ጊዜ ነበር፤ ነገር ግን በአጭር ጊዜ ውስጥ ላባቸው እየረገፈ ለብዙው ሰው ከመሬት መነሣት እያቃታቸው እየመሰለ ነው፡፡

የአገሩ ችግር ውስብስብ መሆኑ እየታወቀ ብዙ ቡድኖች የበለጠ ውስብስብ እያደረጉት ነው፤ ምክንያቱ የተሰወረ አይደለም፤ የሥልጣን ሰይፍና የጠገራ ብር ቀልቀሎ ነው፤ ሁለቱንም እየተስገበገቡ በመሻማት እርስበርሳቸው ለመጠፋፋት የሚተራመሱት ከራሳቸው በላይ ነፋስ ነው!

ለማና ዓቢይ አዲሱ የፖለቲካ ፍልስፍነናቸው ከሁለት ሺህ ዓመታት በላይ ዕድሜ እንዳለው ያውቃሉ፤ ሁላችንም እናውቃለን፤ ለማና ዓቢይ በስንት ወራት የሁለት ሺህ ዓመታቱን ትምህርት ሊያገባድዱ እንዳቀዱ የሚያውቁት እነሱና የላካቸው አምላክ ብቻ ነው፤ እንደጅምራቸው ከሆነ ግን ለማና ዓቢይም እንደክርስቶስ ከሁለት ሺህ ዓመታት በላይ ሳያስፈልጋቸው አይቀርም! እግዚአብሔር አቋራጩን መንገድ ይግለጽላቸው፡፡

ሕግና ሰይፍ የባሕርይ ዝምድና አላቸው፤ ዝምድናቸውም በጣም የጠነከረ ከመሆኑ የተነሣ አንዱ በሌለበት ሌላኛውም የለም፡፡

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
መስከረም 2011

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column, prof mesfin

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule