• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መንገዳችን በፍጥነት ይቃና!

September 30, 2018 02:02 am by Editor Leave a Comment

በብዙ ዓይነት ወንጀሎች የሚታሙት የወያኔ አዛዦች ሥልጣናቸውን እንደያዙ ከሥልጣን ወረዱ ቢባል ግራ ይሆናል፤ ነገር ግን ሆነ! በሕጋዊ ምርመራ ሳይጣራና ከሳሾቹን በፍርድ ቤት ሳይሞግት የሰው ልጅ እንደከብት ከመንገድ በጉልበተኞች እየተያዘ መታሰር የቀረ መስሎን ነበር፤ አልቀረም አሉ! ጉልበተኞች በወንጀላቸው ክብደት ከሕግ ይከለላሉ ይባል ነበር፤ አሁንም ያው ይመስላል! ያነበብሁትን በትክክል ካስታወስሁት በጥንታውያን ግሪኮች ሰርቀው መያዝ እንጂ መስረቅ ወንጀል አልነበረም (የምታስታውሱ አርሙት)፤ የምንመሳሰለው በጥንታዊነት ብቻ መስሎኝ ነበር!

ከዚህ ቀደም ጸጋዬ ገብረ መድኅን (ይመስለኛል) ተረግመናል ብሎ፤ ነበር፤ እኔንም መሰለኝ! ኢትዮጵያውያን መልካቸውን፣ ነብሮች ቆዳቸውን እንዴት ይለውጣሉ ያለው መልካችንን ነበር፣ ወይስ ጠባያችንን ማለቱ ነበር!

ነገሬ ሁሉ የጥንቶቹን አባትና እናት ይህንን የተሸከምነውን ጉድና ነውር ጫኑብን ለማለት እንዳመስላችሁ፤ እነሱ ሊጭኑብን የፈለጉት ክብርንና ኩራትን ነበር፤ ነገር ግን አህያ ወላጆቻችንን እያገለገለች ዱላን የመቻል ትእግስትዋና በዘመናት ለከፈለችው መስዋዕትነት ክብርንና ኩራትን ስትወርስ አበሻ ‹‹አባባ እግርዎትን!›› (ከቃሊቲ የደረጀ ሀብተ ወልድ ትምህርት ቤት የተገኘ እውቀት!) እያለ መለቃቀሙን መረጠ!

የወደቀ ከማንሣት የጣሉትን ማንሣት የሚያኮራና የሚያስከብር ይመስለኛል፤ የጣሉትን ማንሣት ራስን የማረም እርምጃም ነው፤ ራስን ማረም ራስን ማቃናት ነው፡፡

ላለፉት ሦስት ወራት የኢትዮጵያ ሕዝብ በፍቅር፣ በምሕረትና በይቅርታ፣ በመረዳዳትና በተስፋ ንግግሮችና በማይናቁ ድርጊቶች አንገቱን ቀና፣ ደረቱን ነፋ ማድረግ ጀምሮ ነበር፤ ለአዲስ ሥራና ለአዲስ እድገት በአዲስ መንፈስና ደበአዲስ ኃይል ታጥቆ እየተሰናዳ ነበር፤ ለማ መገርሳና ዓቢይ አህመድ የእግዚአብሔር መልእክተኞች መስለው የታዩበት ጊዜ ነበር፤ ነገር ግን በአጭር ጊዜ ውስጥ ላባቸው እየረገፈ ለብዙው ሰው ከመሬት መነሣት እያቃታቸው እየመሰለ ነው፡፡

የአገሩ ችግር ውስብስብ መሆኑ እየታወቀ ብዙ ቡድኖች የበለጠ ውስብስብ እያደረጉት ነው፤ ምክንያቱ የተሰወረ አይደለም፤ የሥልጣን ሰይፍና የጠገራ ብር ቀልቀሎ ነው፤ ሁለቱንም እየተስገበገቡ በመሻማት እርስበርሳቸው ለመጠፋፋት የሚተራመሱት ከራሳቸው በላይ ነፋስ ነው!

ለማና ዓቢይ አዲሱ የፖለቲካ ፍልስፍነናቸው ከሁለት ሺህ ዓመታት በላይ ዕድሜ እንዳለው ያውቃሉ፤ ሁላችንም እናውቃለን፤ ለማና ዓቢይ በስንት ወራት የሁለት ሺህ ዓመታቱን ትምህርት ሊያገባድዱ እንዳቀዱ የሚያውቁት እነሱና የላካቸው አምላክ ብቻ ነው፤ እንደጅምራቸው ከሆነ ግን ለማና ዓቢይም እንደክርስቶስ ከሁለት ሺህ ዓመታት በላይ ሳያስፈልጋቸው አይቀርም! እግዚአብሔር አቋራጩን መንገድ ይግለጽላቸው፡፡

ሕግና ሰይፍ የባሕርይ ዝምድና አላቸው፤ ዝምድናቸውም በጣም የጠነከረ ከመሆኑ የተነሣ አንዱ በሌለበት ሌላኛውም የለም፡፡

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
መስከረም 2011

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column, prof mesfin

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule