በፖለቲካ ሳይንስ መዝገበ ቃላት ውስጥ “አብዮት” የሚለው ቃል “አዲስ ሥርዓትን በመሻት የነባሩን መንግስታዊ ወይም ማህበራዊ ሥርአት በግዳጅ ማስወገድ” በሚል የትርጉም ማዕቀፍ ላይ ሊያርፍ ይችላል፡፡ ‹የሰው ልጅ አብልጦ የሚሻው የተሻለ የፖለቲካ ሥርዓት በየአገራቱ አስካልተመሰረተ ድረስ አብዮት በየትኛውም የዓለም ክፍል አይቀሬ ክስተት› እንደሆነ የፖለቲካ ሳይንስ መምህራኑ አብዝተው ያስተምራሉ፡፡ ሰሚ የለም እንጂ፡፡ ኢህአዴግ የሚባል ገዥ መደብ ፣ ሩብ ክፍለ ዘመን ያህል አገሪቱን እንደ “መንግስት” በመራበት ተራዛሚ የአገዛዝ ዘመኑ ከፍ ሲል ከአምሮ በላይ የሆኑ፣ ስልጣን ላይ በወጣ ስብስብ ይፈፀማሉ ተብለው የማይታሰቡ ውስብስብ የፖለቲካ ሴራዎችን በመስራት ያደረሰው ሰብአዊ ውድመት፤ ዝቅ ሲል ደግሞ ከሰውነት በታች በወረደ የዝቅተኝነት ስሜት በዜጎች ላይ እያደረሰ ያለው የማህበረ ኢኮኖሚ … [Read more...] about የአብዮቱ አይቀሬነትና ጥቁምታዎቹ!
Archives for August 2015
በሞስሊሙ ማኅበረሰብ መሪዎች ላይ የተወሰነውን እስራት ሸንጎ ያወግዛል
ሰኞ ሐምሌ 27፣ 20017 (ኦገስት 3፣ 2015) በሞስሊሙ ማኅበረሰብ መሪዎች ላይ የህወሓት/ኢህአዴግን ፍላጎት በማስፈጸም የሚታወቀው ፍርድ ቤት ከሰባት ዓመት እስከ 22 ዓመት የሚደርስ እስራት እንደበየነባቸው ይፋ ሆኗል። የሞስሊሙ ኅብረተሰብን የተቃውሞ ድምጽ መሠረት በማድረግ በሰላማዊ መንገድ መፍትሄ በማፈላለግ ተግባር ላይ ተሰማርተው የነበሩት እነአቡበከር አህመድ የታሰሩት ከሁለት ዓመት በፊት የህወሓት/ኢህአዴግ መንግሥት በሙስሊሙ ማኅበረሰብ እምነት ውስጥ ጣልቃ በመግባት አመራሩን ለመቆጣጠርና እሱ የሚፈልገውን የእምነት ፈርጅ ኢትዮጵያውያን ሞሰሊሞች በግዴታ እንዲቀበሉ ያውጠነጠነውን ሃላፊነት የጎደለው ተግባር እምቢ ማለታቸውን ተከትሎ እንደነበር ይታወሳል። (ሙሉውን የሸንጎ መግለጫ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) “ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ … [Read more...] about በሞስሊሙ ማኅበረሰብ መሪዎች ላይ የተወሰነውን እስራት ሸንጎ ያወግዛል
የሰላም ትግሉ ያቸንፋል
የሰላማዊ ትግል ተግባራዊነትና ስኬት መለኪያው ምንድን ነው? በዚህ ልጀምር ጽሑፌን። በርግጥ መጀመር ያለበት፤ ሰላማዊ ትግል ምንድን ነው? የት ተተገበረ? እንዴት ተተገበረ? ከትጥቅ አመጹ በምን ተሽሎ ይገኛል? እዚህ ሰላማዊ ትግል፤ እዚያ ግን የትጥቅ ትግል የሚባለው እንዴት ነው? በሚሉት ነበር። ነገር ግን፤ አንባቢዬ በትክክል እንደሚረዱት፤ አሁን የያዝነው፤ በተጨባጩ በሀገራችን ባለው የፖለቲካ ሀቅ፤ ምን ላይ ነው ያለነው? ምን ማድረጉ ለትክክለኛው ሕዝባዊ ድል አመርቂ ውጤት ያስገኝልናል? ከሚለው በመነሳት ነው። እንግዲህ መሠረታዊው መነሻ፤ አሁን ያለንበት የሀገራችን የፖለቲካ ሀቅ ነው፤ ማለት ነው። እዚህ ላይ ነው እኔ፤ ሽንጤን ገትሬ፤ “ሰላማዊ ትግሉ ያቸንፋል!” በማለት የቆምኩት። እናም ላስረዳ! ገዥው ወገንተኛ አምባገነን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት፣ ከሕዝቡ ተነጥሎ … [Read more...] about የሰላም ትግሉ ያቸንፋል
ሁለቱ ትግሎች
ብርሃኑ ነጋ ዱር ገባ! አንዳርጋቸው ጽጌ መፅሃፍ ጨረሰ! ኦባማ በዴሞክራሲያዊ መንገድ መመረጣችንን እውቅና ሰጠ! እነዚህ እንግዲህ የሰሞኑ ፖለቲካዎች ናቸው። ያለወትሯቸው በአሜሪካ ድምፅ ላይ ለቃለመጠይቀ የቀረቡት ዶ/ር ቴድሮስ አድኅኖም ያልበላቸውን ሲያኩ ተደምጠዋል። አድማጭ ልብ ሊለው የሚገባ ጉዳይ አለ። ዶፍተሩ ስለ ብርሃኑ ነጋም ሆነ ስለ አንዳርጋቸው ጽጌ የተናገሩት ሳይጠየቁ ነበር ይኼ እንግዲህ “የማርያምን ... ምን የበላ …” እንደሚባለው ነው። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) “ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በዚህ ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይዘገባሉ፡፡ ይህ በጎልጉል … [Read more...] about ሁለቱ ትግሎች
ከሳሽ ሲከሰስ
(ኢትዮጵያ ውስጥ ፍትሕ ቢኖር እኛ ኢትዮጵያን ሙስሊሞች እንዲህ ብለን እንከስ ነበር!) የፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 የተመለከተውን በመተላለፍ የተከፈተ ክስ የቀ/ቁ/001/2006 የወ/መ/ቁ. 01/0001/06 ለኢትዮጵያ ህዝብ በሙሉ በመላው ዓለም ከሳሽ ….. ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች (የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ) ተከሳሾች… 1/ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግስት የሽብር ቡድኑ አጠቃላይ አስፈጻሚ 2/ የህውኃት/ኢህአዴግ ማዕከላዊ ኮሚቴ የሽብር ቡድኑ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ 3/ የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ (በሌሉበት) የሽብር ቡድኑ የቀድሞ አመራር 4/ ጠ/ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ የሽብር ቡድኑ አመራር 5/ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የሽብር ቡድኑ ወታደራዊ ክንፍ 6/ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ቢሮ የሽብር ቡድኑ መረጃ ክፍል 7/ … [Read more...] about ከሳሽ ሲከሰስ
አዱሊስ/Adulis
ባለ 21 ገጽ የአዱሊስን ልዩ ዕትም ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ:: … [Read more...] about አዱሊስ/Adulis
በሳውዲ “ድምጻችን ይሰማ” ላይ የተቃጣው ሴራ ከሸፈ
ሳውዲ ኢትዮጵያውያን ሙስሊም የትግል አንድነት ላይ የተቃጣው የህወሃት/ኢህአዴግ ሴራ መክሸፉ ተሰማ! ከዕርዳታ አሰባሰብ ጋርም በተያያዘ የተፈጸመው ተግባር ለሕዝብ ይፋ ሆኗል፡፡ የህወሃት/ኢህአዴግ ካድሬዎች መቀመጫቸውን ሳውዲ አረቢያ ጅዳ ከተማ ካደረጉ ወዲህ የህዝበ ሙስሊም እንቅስቃሴ ለማፈን የተለያዩ ስልቶችን ነድፈው ከአካባቢው የመንግስት ሹማምንቶች ጋር ሲንቀሳቀሱ እንደ ነበር ይታወቃል። እነዚህ ምስለኔዎች ለአገዛዙ ባላቸው ታማኝነት ከጅዳ እስከ ሪያድ በዘለቀ የስለላ መረባቸው በሳውዲ “ድምጻችን ይሰማ የሙስሊሞች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ” በሚያደርገው ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ የሚሳተፉ ሙስሊም ወገኖቻቸውን ስም ዝርዝር ለኢህአዴግ በማቅረብ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ግፊት ሲያደርጉ የነበረ ከነፍሳቸው ይልቅ ለጥቅም ያደሩ መሆናቸውን አያሌ የእምነቱ ተከታዮች ይገልጻሉ፡፡ በተለይ እነዚህ … [Read more...] about በሳውዲ “ድምጻችን ይሰማ” ላይ የተቃጣው ሴራ ከሸፈ
የፌዝ ችሎት
በኢትዮጵያ የሙስሊሙ ማህበረሰብ ችግሮች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት የታሰሩበትን ፖለቲካዊ ጉዳይ ህጋዊ ለማስመሰል የተሰየመው የፊዝ ችሎት ለአመታት የከረመበትን ተውኔት ከ 7 አመት እስከ 22 አመት እስር በመፍረድ አጠናቋል፡፡ የፍርዱን ዜና ተከትሎ የሚሰማው የሚነበበው ስሜት ከዚህ በተቃራኒ ፍትሀዊ የሆነ ፍርድ የጠበቁ ሰዎች እንደነበሩ የሚያመለክት ነው፡፡ ከወያኔ የፌዝ ችሎት ይህን ማሰብ ወያኔን አለማወቅ ወይንም ትናንትን መርሳት ይመስለኛል፡፡ ይህ ደግሞ ትግሉ በሚጠይቀው ጽናትና ቁርጠኝት እንዳይካሄድ የሚያደርግ ነው፡፡ ወያኔ በፍትህ ሲያላግጥ በህግ ሽፋን ወንጀል ሲፈጽም እውነትን በጠመንጃው ሲረግጥ ወዘተ ይህ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ በሀሰት ወንጅሎ፣ በትእዛዝ የሚፈርዱ ዳኞች ሰይሞ፣ የፌዝ ችሎት አቋቁሞ፣ ኣቃቤ ህግ ሳይሆን አቃቤ ወያኔ አቁሞ ፣ በፍትህ ላይ ትያትር ሲሰራ እኛ … [Read more...] about የፌዝ ችሎት
ቴድሮስ አድሃኖም “ኢህአዴግ ቂመኛ አይደለም” አሉ
የኢህአዴግ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቴድሮስ አድሃኖም “ኢህአዴግ ቂመኛ አይደለም” ሲሉ ከቪኦኤ አማርኛው ክፍል ባልደረባ ትዝታ በላቸው ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ አስታወቁ። ሚኒስትሩ ድርጅታቸውን ከደርግ ጋር በማነጻጸር ከቂም የጸዳ እንደሆነ ሲያስረዱ ጋዜጠኛዋ አማርኛ ተናጋሪዎች ላይ በቂም በቀል ስለተፈጸመውና እየተፈጸመ ስላለው ግፍ ጥያቄ አላቀረበችም። ሚኒስትሩ ኢህአዴግ በህግ የበላይነት ስለማመኑ በመረጃ አልተሞገቱም። በዘር፣ በብሄርና በጎሳ ላይ ተንጠልጥሎ ከሁለት አስርተ ዓመታት በላይ በስልጣን ላይ የቆየው ኢህአዴግ፣ በ፩፱፰፫ ስልጣን ከያዘ ጀምሮ በገሃድ አማርኛ ተናጋሪዎችን ከሌሎች ብሄረሰቦች ጋር በማናከስ፣ ቂም በማቋጠር፣ የስርአተ ማህበሮችን ችግሮች ከነፍጥ ጋር በማያያዝ እያላከከባቸው፣ “ነፍጠኛ” የሚል ስም በመስጠት የህዝብ ንብረት በሆነው መገናኛ የጥላቻ ዘመቻ በማራገብ … [Read more...] about ቴድሮስ አድሃኖም “ኢህአዴግ ቂመኛ አይደለም” አሉ