በድርጅት ከዚያም ከፍ ብሎ በመንግስት ደረጃና በሃገር ደረጃ ግምገማ ማድረግ ወሳኝ ጉዳይ እንደሆነ ሁሉ ያምናል። የኣንድ ድርጅት ብቃትም በግምገማው ችሎታና ጥራት ሊለካ ይችላል።የኣንድ ሃገር የፖለቲካ መረጋጋት በፖለቲካ ለሂቆቹ የጠራ የሃገር የምናብ ስእልና ብስለት ሊለካም ይችላል። የፖለቲካ ቤቶች ሲኮለኮሉ፣ ፖሊሲዎች ሲቀረጹ ከፍ ያለ ግምገማን ይጠይቃል። ሃገሪቱ ያለፈችበትን የህይወት ጎዳና፣ የገጠማትን ችግር መንስዔና ውጤቶች በሰፊው መገምገም ለሚመሰረቱ የፖለቲካ ድርጅቶች መሰረትና ለሚቀረጹ ፖሊሲዎች ጥራት ወሳኝ ነው። እንግዲህ በሃገራችን ኢትዮጵያ ግምገማ በሰፊው የተወራለት ጉዳይ የሆነው በዚህ መንግስት ጊዜ ነው። ህወሃት በጫካ ኑሮው ጊዜ የነበረው ማህበራዊ ህይወትና የትግሉም ባህርይ የየቀን ውሎውን እየገመገመ እንዲሄድ የሚያስገድድ ሁኔታ ውስጥ ስለከተተው በግለሰቦች ድክመትና … [Read more...] about የ“ኢህኣዴግ” ግምገማና ፍሬው
Archives for June 2015
… አልሞት አለኝ
በስራው ላይ ልፈላሰፍ ቅኔ ልቀኝ ግጥም ልጽፍ ቸኩያለሁ አልሞት ብሎኝ የማደንቀው ሰው ነበረኝ ሳይሞትማ ሳይቀበር ስሙን ማንሳት እሱን ማክበር መስሎ ታይቶኝ ልምድን መስበር የማደንቀው ሰው እያለኝ ልጽፍለት ተቸገርኩኝ አቤት! ዕውቀት አይ! ቁመና ብልህ ደፋር ቆራጥ ጀግና ሀይማኖቱን አጠንካሪ ደግ ለጋስ ሰው አክባሪ ብዬ ልለው ቸኩያለሁ አልሞት ብሎኝ ታሞ እያየሁ ዛሬ ቢያጣ ዛሬ ቢርበው በቁም ሆኖ ከምረዳው ከማከብረው ከማደንቀው እደርሳለሁ ሲሞትልኝ ከምድር በታች ሲውልልኝ ያንጊዜ ነው ስሙ ገኖ የሚነሳው እሱን ሆኖ የብዕር ጫፍ የሚመዘዝ እንባ የሚረጭ የሚተከዝ ሚጻፍለት ሚደነቀው ታሪክ ገኖ ሚነበበው ገንዘብ ከኪስ ሚመዘዘው ለሟች በድን አካሉ ነው ያን አይቼ ልምድ አብቶኝ የቆየ ወግ አንቆ ይዞኝ የማደንቀው ሰው … [Read more...] about … አልሞት አለኝ
የነፃነት መውጫው መንገድ፣ ታጋዩ፣ ሕዝቡን ጠንካራ ምሽጉ ማድረግ ሲችል ነው
የአንድ ለነፃነት የሚታገል ኃይል የመጀመሪያ ተግባሩ፣ ጠንካራ ምሽግ መገንባት ነው። ምሽግ ሲባልም መሬትን ጎርዶ ራስን መቅበር፣ ወይም ደግሞ በኮንክሪት መከታ እና ጠለላ ገንብቶ ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚወነጨፉ አውዳሚ የጦር መሣሪያ አረሮችን መከላከል አይደለም። ጠንካራ ምሽግ ሲባል፣ ታጋዩ ኃይል ነፃ አወጣዋለሁ የሚለውን ሕዝብ፣ ዓላማውን አሳውቆ፣ አሳምኖ እና አደራጅቶ የታጋዩ ኃይል የቀለብ፣ የመረጃ እና የሰው ኃይል ምንጭ ማድረግ መቻል ነው። በአጭሩ ሕዝቡን ባሕር፣ ታጋዩን ዓሣ ማድረግ መቻል «ለነፃነት እታገላለሁ» የሚል ኃይል የአደረጃጀት ስልት ሊሆን ይገባል። ይህን ያላደረገ ታጋይ ሌሎችን ነፃ ሊያወጣ ቀርቶ፣ ራሱም ነፃ አይሆንም። ራሱን ነፃ ያላወጣ ደግሞ፣ ብዙኃኑን ወደ ነፃነት ጎዳና ሊመራ አይቻለውም። ለነፃነት የሚታገሉ ኃይሎች ደረጃ በደረጃ ሊያሟሏቸው የሚገቧቸው ሁኔታዎች … [Read more...] about የነፃነት መውጫው መንገድ፣ ታጋዩ፣ ሕዝቡን ጠንካራ ምሽጉ ማድረግ ሲችል ነው
“ወንድ ከወንድ፤ ሴትም ከሴት ይጋቡ” ጠቅላይ ፍርድቤት
* “ፍቅር ፍቅር ነው” ኦባማ ወንድ ከወንድ፤ ሴትም ከሴት ጋር ጋብቻ መፈጸም ይችላሉ፤ ለእነርሱ የጋብቻ ሠርቲፊኬት መከልከል ሕገመንግሥቱን ይጥሳል በማለት የአሜሪካው ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መጋባት እንደሚችሉ ወሰነ፡፡ ለጋብቻ ቅድስናና ክቡርነት የሚከራከሩ “የእግዚአብሔርን ሕግ ምድራዊ ፍርድ ቤት ይህን መለወጥ አይችልም” በማለት ውሳኔውን አጥብቀው ተቃውመዋል፡፡ በምንም መልኩ ይገለጽ ፍቅር ፍቅር ነው በማለት ፕሬዚዳንት ኦባማ ውሳኔውን ደግፈዋል፡፡ ዋናውን (ዓቃቤ ፍትህ) ጨምሮ ዘጠኝ የፍትህ ዳኞች የያዘው የአሜሪካው ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዚህ የሰዶማውያን ጋብቻ ላይ ውሳኔ እንዲያስተላልፍ ጉዳዩ ከቀረበለት ጊዜያት ተቆጥረዋል፡፡ በአሜሪካ የፍትሕ ሥርዓት ምዕራፍ ከፋች የተባለለት ውሳኔ አርብ ዕለት ሲተላለፍ የፍትሕ ዳኞቹ በአምስት ለአራት በመወሰን ነው ያጸደቁት፡፡ … [Read more...] about “ወንድ ከወንድ፤ ሴትም ከሴት ይጋቡ” ጠቅላይ ፍርድቤት
አለም አቀፍ ድጋፍ የተቸረው “ልማታዊ” አንባገነናዊነት በኢትዮጵያ
"የአፍሪቃ ድሃ ባይጠግብም እንኳ ቀምሶ ካደረ ይበቃዋል" አይነት ንቀት የተሞላው የምዕራቡ አለም ምልከታ ከመቼውም ጊዜ በከፋ መልኩ አፍጦና አግጦ እየታየ ነው፡፡ በርሃባችንና በእርስ በእርስ መናቆራችን ለዘመናት ሲነግዱበትም ሲማረሩበትም ቆይተዋል፡፡ ዛሬ ዛሬ የመጫወቻው ካርድ ተቀይሮ ለአፍሪቃ አንባገነኖች አንድ ቃል ተለጥፎላቸው ካሳላፍነው ታሪክ ምናልባትም በከፋ መልኩ ጉዟችንን ቀጥለናል፤ የኋሊት ይሁን ወደፊት እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ ነገር ግን የምዕራቡ አለም “ልማታዊ” በሚል ካባ የተከናነበውን የለየለት አንባገነናዊነት ሙሉ ድጋፋቸውን እየሰጡ ለመሆኑ የኦባማን የኢትዮጵያ ጉዞ ጨምሮ በርካታ ምልክቶችን እያየን ነው፡፡ ከምርጫው በፊትም ሆነ ከተጠናቀቀ በኋላ የአውሮፓ ኅብረትና የአሜሪካን መንግስት ያሳዩትም ድጋፍ የእዚሁ መገለጫ ነው፡፡ በአፋኝ አገዛዝ ውስጥ ላለ ሕዝብ ዲሞክራሲን፣ … [Read more...] about አለም አቀፍ ድጋፍ የተቸረው “ልማታዊ” አንባገነናዊነት በኢትዮጵያ
“የአማራ ክልል ዳኞች አቤቱታ”
ከአዘጋጆቹ፡- ማንነታቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የፌስቡክ ወዳጃችን “የአማራ ክልል ዳኞችን ድምፅ አስተጋቡልን” በማለት በውስጥ መስመራችን የላኩልንን ከዚህ በታች አቅርበነዋል፡፡ ጋዜጠኝነት “ወንጀል” በሆነባት ኢህአዴግ በሚገዛት አገራችን በስም የተጠቀሱትን ሹመኛ ለመጠየቅና ሁኔታውን ለማረጋገጥ አንችልም፡፡ ሆኖም ግን መረጃው ስህተት ነው የሚል የኢህአዴግ አካል ምላሽ ከሰጠን ለሕዝብ እናቀርባለን፡፡ “የአማራ ክልል ዳኞችን ድምፅ አስተጋቡልን”!!!!! ደመወዝና ጥቅማጥቅም ስላነሰን ከእነ ልጆቻችን ተራብን፣ ተጠማን፣ ብለን ሀሳብ እንዳንሰጥ “ችግር አለባቸው” እየተባልን ከነአካቴው ከስራ ልንወገድ ሆነ፡፡ ጎን ለጎን ሌላ ስራ ፈጥረን እንዳንሰራ ዳኛ በንግድ ስራ መሰማራት አይችልም ተባልን፡፡ ኧረ የት እንድረስ!!! ደመወዝና ጥቅማጥቅም ይስተካከልላቸው ተብሎ ከክልሉ ዳኞች አስተዳደር … [Read more...] about “የአማራ ክልል ዳኞች አቤቱታ”
“አንዳርጋቸው የነጻነት ታጋይ እንጂ አሸባሪ አይደለም”
የግንቦት 7 ዋና ፀሀፊ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በየመን የፀጥታ ሃይሎች ታግተው ለዘረኛውና አፋኙ የወያኔ ቡድን ተላልፈው የተሰጡበትን አንደኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ በኖርዌይ ደረጃ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ በወጣቶች ክፍል አስተባባሪነት በጁን 23/ 2015 በእንግሊዝ ኢምባሲ ፊት ለፊት እልህና ቁጭት የተሞላበት ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂዷል። በሰልፉ ላይ ከተለያዩ የኖርዌይ ከተሞች የተገኙ በርካታ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በኖርዌጅያን የሰአት አቆጣጠር ከ13፡30 ስዓት ጀምሮ ታላቋ ብርታኒያ ለዜጋዋ አቶ አንዳርጋቸው ልዩ ትኩረት አድርጋ ከዘረኛው ወያኔ ነጻ በማውጣት ወደ ቤተሰቡ እንዲመለስ ለማሳሰብ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው የነጻነት ታጋዩን አንዳርጋቸውን በተመለከተ የተለያዩ መፎክሮችን … [Read more...] about “አንዳርጋቸው የነጻነት ታጋይ እንጂ አሸባሪ አይደለም”
ከገዥው ወገን የምንለይበት
እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለትግሬዎች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለኦሮሞዎች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለአማራዎች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለሶማሌዎች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለአፋሮች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለኦጋዴኖች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለአኙዋኮች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለሲዳማዎች ጥብቅና እቆማለሁ፤ የሚል ግለሰብም ሆነ ድርጅት፤ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ይልቅ ከአምባገነኑ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ጋር የበለጠ የጋራ የሆኑ መቀራረቢያ ጉዳዮች ስላሉት፤ ሰፈሩን ወደዚያ ቢያቀና ይቀለዋል። የኢትዮጵያ ሕዝብ ከአምባገነኑ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት ጋር መሠረታዊ … [Read more...] about ከገዥው ወገን የምንለይበት
“ደብረማርቆስና ባህርዳር ላይ ሰላማዊ ሰልፍ ልታደርጉ ነው የምትሄዱት” ፖሊስ
• ከአዲስ አበባ ወደ ጎጃም ለሌላ ለቅሶ በመሄድ ላይ የነበሩ ዜጎች ተደብድበው ተመልሰዋል የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ሰኔ 8/2007 ዓ.ም ደብረማርቆስ ከተማ የተገደለው የሳሙኤል አወቀ ለቅሶ እንዳይደርሱ ታገዱ፡፡ አመራሮቹና አባላቱ ሰኔ 13/2007 ዓ.ም በጠዋት ከአዲስ አበባ ተነስተው የሳሙኤል አወቀ ቤተሰቦች ወደሚገኙበት ምስራቅ ጎጃም ዞን ግንደወይን እያቀኑ በነበረበት ወቅት አባይ ድልድይ ላይ በፌደራል ፖሊስ ታፍነው ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ ጎሃ ፂዮን ከተማ ውስጥ እስከ ምሽቱ 2 ተኩል ድረስ ታግተው ውለዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላትን ወደ ለቅሶ እንዳይሄዱ ያገዱት ከአዲስ አበባ የሄዱና ከቦታው ተዘጋጅተው ሲጠብቁ የነበሩ የፌደራል ፖሊሶች እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል፡፡ አመራሮቹና አባላቱ ለፖሊስ ቃል ሲሰጡ ከሳሙኤል አወቀ ጋር የነበራቸውን … [Read more...] about “ደብረማርቆስና ባህርዳር ላይ ሰላማዊ ሰልፍ ልታደርጉ ነው የምትሄዱት” ፖሊስ
“ከ10 ሌባ መሀል አንተ ንጹህ ሆነህ ሙስናን መታገል አትችልም” የፍትህ መምሪያ ሀላፊ
* “ግድያው ከሟች የፖለቲካ አቋም ጋር የሚገናኝ አይደለም፤ የመንግስትም እጅ የለበትም” ህወሃት/ብአዴን/ኢህአዴግ * “ለሞት ያበቃቸው ክስተት ግን ግለሰባዊ ግጭት” የህወሃት/ብአዴን ሹመኛ * “የሰማያዊ ፓርቲ አባልነትህን የማታቋርጥ ከሆነ አንተን ማስደፋት ቀላል ነው!” የደብር ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ * “የሰማያዊ ፓርቲ አባልነቴን አንተ አታስቆመኝም፡፡ አገሬም ኢትዮጵያ ነው! ከኢህአዴግ ጋር ስታገልም ይህን ሁሉ አውቃለሁ፡፡ የፈለግከውን ማድረግ ትችላለህ!” ሳሙኤል አወቀ እንዲህ ዓይነቱ በማስረጃ የተደገፈ ክስተት እያለ ሠንደቅ ጋዜጣ አነጋግሬ አመጣሁ ባለው ዜና ላይ የሳሙኤል ግድያ "ልማታዊ" ነው ይላል:: ለመሆኑ ራሱ ሳሙኤል አወቀ ምን ይላል? ሳሙኤል ሚያዝያ 3 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 8 የነገረ ኢትዮጵያ እትም ላይ በምስራቅ ጎጃም ዞን … [Read more...] about “ከ10 ሌባ መሀል አንተ ንጹህ ሆነህ ሙስናን መታገል አትችልም” የፍትህ መምሪያ ሀላፊ