• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከገዥው ወገን የምንለይበት

June 23, 2015 09:04 am by Editor Leave a Comment

እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለትግሬዎች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለኦሮሞዎች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለአማራዎች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለሶማሌዎች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለአፋሮች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለኦጋዴኖች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለአኙዋኮች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለሲዳማዎች ጥብቅና እቆማለሁ፤ የሚል ግለሰብም ሆነ ድርጅት፤ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ይልቅ ከአምባገነኑ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ጋር የበለጠ የጋራ የሆኑ መቀራረቢያ ጉዳዮች ስላሉት፤ ሰፈሩን ወደዚያ ቢያቀና ይቀለዋል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ ከአምባገነኑ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት ጋር መሠረታዊ ልዩነቱ፤ እያንዳንዳችን ኢትዮጵያዊያን፤ “እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ። በሀገሬ በኢትዮጵያ የማደርገው ማንኛውም የፖለቲካ ተሳትፎ፤ በኢትዮጵያዊነቴ ብቻ ነው። በኢትዮጵያዊነቴ ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ባልተለዬ ሁኔታ፤ እኩል በፖለቲካ ምኅዳሩ፤ የግለሰብ ዴሞክራሲያዊ መብቴ ተከብሮልኝ፤ በማንኛውም የሀገሬ ክልል፤ የመኖር፣ ሀብት የማፍራት፣ በአካባቢውና በሀገር አቀፍ የፖለቲካ ሂደት ተሳትፎ የማድረግ ሙሉ መብት አለኝ።” ስንል፤ አምባገነኑ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት ደግሞ፤ “የለም ኢትዮጵያ የትግሬዎች፣ የአማራዎች፣ የኦሮሞዎች፣ የደቡቦች፣ የሶማሌዎች፣ የአፋሮች፣ የአኝዋኮች ነች። ግለሰብ ኢትዮጵያዊ የሚባል የለም። እናም የፖለቲካ ተሳትፎ የሚደረገው በነዚህ ክልሎች ዙሪያ እንጂ፤ በኢትዮጵያዊነት አይደለም።” የሚለው ነው።

ከዚህ በመነሳት፤ አምባገነኑ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት፤ አስተዳደሩን በዚህ ላይ ተከለ። በሂደቱም የተለያዩ ለየብቻቸው የተካተቱ ክልሎችን መሠረተ። አያንዳንዱ የዚህ ገዢ ቡድን ተቀጥላ ጥገኛ የክልል የፖለቲካ ድርጅት፤ የራሱን የክልሉ ተወላጆች ብቻ በክልሉ ለመክተትና ለማስተዳደር ሙሉ መብት አገኘ። እናም በገዥው ቡድን ፈቃድና ፍላጎት፤ ሌሎችን ከክልሉ ማባረር፣ ሀብታቸውን መዝረፍ፣ መግደል፣ አይቀሬ ሆነ። በተግባርም ተፈጸመ። ሀገራችንን ፍጹም ወደማትመለስበት አዘቅት ለመክተት፤ ይኼው ገዥ ቡድን ተሯሯጠ። ተከትለው የሚሄዱት የሕዝቡን ድምጽ ማፈን፣ ሀገሪቱን እስር ቤት ማድረግ፣ አንገቱን ሰብሮ የማይገዛውን ማሰር፣ ማባረርና መግደል፤ ተዥጎደጎዱ። ለዚህ ተቃውሞ፤ ኢትዮጵያዊያን የተለያዩ ድርጅቶችን መሥርተው በመታገል ላይ ናቸው። እንግዲህ በዚህ ትግል፤ ሁለት ሰፈሮች ብቻ በገሃድ አሉ። አንደኛው የሕዝቡ ሰፈር ነው። ሌላው የአምባገነኑ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት ሰፈር ነው። የግለሰብ ሆነ የድርጅት ጉዳይ እዚህ ቦታ የለውም። የግለሰብ እምነት ወይንም የድርጅት መርኀ-ግብር፤ ከሁለቱ መርጠን ባንዱ ሰፈር እንድንሰለፍ ያደርገናል። የሰልፉ መለያ ደግሞ፤ የፖለቲካ ፍልሰፍናችን እና ከዚህ የሚመነጨውና በተግባር ለማዋል የምንፈልገው የአስተዳደር መመሪያ ነው።

ይህ ነው የአሁኑ የሀገራችን የኢትዮጵያ የፖለቲካ እውነታ። ይሄን በጁ ያልጨበጠ ማንኛውም ሂደት፤ መዳረሻው ተመልሶ ያው ነው። የድርጅት መሪዎችም ሆኑ ታጋይ ግለሰብ ኢትዮጵያዊያን፤ መሠረታዊ የሆነውን የልዩነት ነጥብ በማንገት፤ ትግሉን መልክ ሠጥተን መሄድ አለብን። አማራ ነኝና ከሌሎች የበለጠ ለአማራዎች እኔ ነኝ ተቆርቋሪ፣ ለኦሮሞዎችም፣ ለትግሬዎችም፣ ለሶማሌዎችም፣ ለአፋሮችም፣ ለአኙዎኮችም፣ ለሲዳማዎችም እኔ ነኝ ተቆርቋሪ የሚለው አባባል፤ የኢትዮጵያዊነት ጠላት ነው። እንደ ኢትዮጵያዊ ካላሰብን፤ ኢትዮጵያዊነት በውስጣችን የለም። እንደ ኢትዮጵያዊ ካልታገልን፤ ኢትዮጵያ የለችም። በሀገራችን፤ ለኢትዮጵያዊያን ሉዓላዊነት፣ ለሀገራችን ዳር ደንበር መከበር፣ ለያንዳንዳችን ዴሞክራሲያዊ መብት የምንታገለው በኢትዮጵያዊነታችን ነው። አንዳችን ከሌላችን ጎን የምንሰለፈው፣ የያንዳንዳችን ጉዳይ የሌላችን በመሆኑ ነው። አለዚያ፣ አንተም ለራስህ እኔም ለራሴ ከሆነ፤ ትግሉ ለኢትዮጵያዊያንና ለኢትዮጵያ ሳይሆን፤ በየኪሳችን ለያዝነው ዘውድ ነው። መነሻችን ይሄ ከሆነ፤ መድረሻችን ኢትዮጵያ ናት።

ይሄን እንድጽፍ ያስገደደኝ፤ ስለሰላማዊ ትግል የመጀመሪያውን ክፍል ባቀረብኩበት ወቅት፤ ከሌሎች የተላኩልኝ አፀፋዎች ነው። የገዥውን ስም ለምን “ትግሬዎች” ትላለህ የሚለው በተደጋጋሚ የቀረበልኝ ቢሆንም፤ ባሁኑ ሰዓት ቁንጮው ላይ ደረሰ።

እናም ይሄን ጻፍኩ። እኔ ራሳቸውን እንዲጠሩበት በመረጡት ስም ነው የጠራኋቸው። ለኔ ካላይ እንደገለጽኩት የኢትዮጵያ ሕዝብ አንድ ነው። ኢትዮጵያ አንድ ናት። ኢትዮጵያ የኢትዮጵያዊያን ናት። በትግራይ ያሉት ኢትዮጵያዊያን፤ ትግሬዎች ይባላሉ። በአፋር ያሉት ኢትዮጵያዊያን አፋሮች ይባላሉ። ታዲያ ትግሬዎችን ነፃ አወጣለሁ ብሎ የተነሳ ግንባር፤ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ነኝ ሲል፤ ሌላ ምን ብዬ ልጠራው ነው። የትግራይ ሕዝብ፣ የአማራ ሕዝብ፣ የኦሮሞ ሕዝብ ካልኩማ፤ ሰፈሬ ከገዥው አምባገነን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር አይሆንም ወይ? ለኔ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንጂ የትግራይ ሕዝብ፣ የአማራ ሕዝብ፣ የኦሮሞ ሕዝብ፣ የሶማሌ ሕዝብ፣ የሲዳማ ሕዝብ፣ የአኝዋክ ሕዝብ፣ የቤንሻንጉል ሕዝብ፣ የወላይታ ሕዝብ የለም። እናም፤ የትግራይ ሕዝብ ነፃ አውጪ ግንባር ብዬ አልጽፍም። ለምን ይሄን ጽፍክ የሚለኝ ካለ፤ ሄዶ ስም ያወጣውን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ይጠይቅ።

በሀገራችን ያለው ትግል፤ ሀገርን ከአምባገነን ፀረ-ኢትዮጵያ የሆነ ጠላታችን አንጻር፤ ልዩነታችን በግልጽ ወጥቶ፣ ተሰላፊዎች ባደባባይ ታውቀን የቆምንለት እንጂ፤ አንዳችን ሌላችንን የምንለማመጥበት ጉዳይ አይደለም። ትግሉ የመላ ሕዝቡ እንጂ፤ የዚህ ወይንም የዚያ ወገን የግል ጉዳይ አይደለም። ታጋዩን የሕዝብ ወገን ወደ አንድ ማሰባሰቡ የትግሉ የመጀመሪያ ግዴታ ነው። በርግጥ መተባበር የዲፕሎማቲክ ሥራ እንጂ፤ አንተም ባፈተተህ የሚባልበት ሂደት አይደለም። በቅርቡ የተለያዩ ታጋይ ድርጅቶች ቢያንስ ተገናኝተው ለመነጋገር ይችሉ እደሆነ በማሰብ፤ ጥረት አድርጌ ነበር። ይሰበሰቡና መፍትሔ ያቀርቡልናል የሚል ብዥታ አልነበረኝም። ነገር ግን፤ በሂደቱ ሁላችን ሀገራችን ያለችበትን አደጋ በመመልከትና ቅድሚያ ለሀገር ብለን፤ በድርጅት ያሉትም ሆነ ግለሰብ ታጋዮች፤ የመሰባሰቡን ሂደት ያቀላጥፉታል ብዬ ነበር። አልተሳካም። ትግሉ ከገዥው አምባገነን ጋር የምንፋለምበትን ጉዳይ በቅርብ በልብ አንግተን፤ የጠራና ፀሐይ የሞቀውን ልዩነታችንን ባደባባይ አንግተን የተነሳንበት ግብግብ ነው። ይሄን ላስደስት፤ ያንን ላቆላምጥ የሚባልበት አይደለም። በተለይ በሥልጣን ላይ ያለን መንግሥት ለመለወጥ የሚደረግ ትግል፤ የጠራ አመለካከት ከሌለው፤ ትግሉ ውጤታማ አይሆንም። ጠላት ማነው፣ የምንታገለው ለምንድን ነው? ግባችን ምንድን ነው? መመለስ ያለባቸው ጥያቄዎች ናቸው። በዚህ ትግል፤ ጠርተው የሚወጡ ጽንሰ-ሃሳቦች አሉ። እኒህ የትግሉን ሂደት ይተረጉሙታል። ግንዛቤን ያዳብራሉ። በሥልጣን ላይ ያለውን ገዢ ቡድን ማንነቱን ለመግለጽ የምንጠቀምበት ስም፤ ራሱን ግልጽ አድርጎ የሚጠራበትና የሚጠራበት መሆኑ፤ በትግሉ ላይ ትልቅ አስተዋፅዖ አለው። የምናየው የትግል አሰላለፍ ትርጉሙ የሚመነጨው፤ ከግንዛቤያችን ላይ በመቆም ነው።

በአንድ በኩል ጠላታችን የሚታወቀው ራሱ ነኝ ብሎ ባወጣው ስም እንጂ፤ እኛ በምናወጣለት ስም አይደለም። በሌላ በኩል ደግሞ በመካከላችን እብሪተኛን እብሪተኛ ማለት ካልቻልን፤ ታጋዮች ሳንሆን ወሬኞች ነን። ከሁሉም በላይ የሀገሬ ጉዳይ ብሎ ያልተነሳ ታጋይ፤ የሕዝቡ ወገን ሊሆንም ሆነ ታግሎ የሕዝቡን ድል ሊያስገኝ አይችልም። ቢሳካለት ገዥውን መተካት ነው ሩጫው።

አንዱዓለም ተፈራ – የእስከመቼ አዘጋጅ

ማክሰኞ፤ ሰኔ ፲፮ ቀን ፳፻፯ ዓመተ ምህረት

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule