• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር

June 8, 2022 11:53 am by Editor 4 Comments

ዶ/ር አብይ አህመድ በተለያዩ መድረኮች ወልቃይት የበጌምድር አማራ መሆኑን በማያሻማ መንገድ በጠራ አገላለፅ ባረጋገጠበት መንገድ (የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር ፊርማ ነው)፤ ወልቃይት በአማራ ክልል መንግስት ስር እየተዳደረ ባለበት ሁኔታ፤ ወልቃይትን አብይ አህመድ ለወያኔ አሳልፎ ሊሰጥ ስለሆነ አማራ ከመከዳትህ በፊት ተነስ የሚሉ የግጭት ነጋዴዎች ድምፅ ማሰማት ሳይሆን ለእነሱ ጆሮ የሚሰጠው ሰው ቁጥር በዚህ ደረጃ መጠኑ መጨመሩ የሚያስደንቅና የሚያሳስብም ነው። እርግጥ ነው ጉዳዩ የማንም ሳይሆን የራሱ የመንግስት የPR ችግር የፈጠረው ነው።

ዶ/ር አብይ አህመድ ለአማራ እንቆረቆራለን ወይም እንታገላለን ከሚሉት በላይ በወልቃይት ጉዳይ የሕዝቡን የዓመታት ጥያቄና ትግል እውቅና ሰጥቶ ወልቃይት የበጌምድር አማራ መሆኑን የጠራ አቋሙን በአደባባይ አረጋግጦ ለሕዝቡ ጥያቄ የራቀ ሳይሆን መቅረቡን ያስመሰከረበትን ጉዳይ ጠላት ወያኔ ግን ወልቃይት እንዳይመለስ ወይም ለወያኔ ተላልፎ እንዲሰጥ አብይ እየሰራ እንደሆነ አድርጎ መንጋ የሚያደናግርበት ወይም በመንጋ እንዲከሰስ ዕድል የፈጠረበት ሁኔታ የጠላትን ጥንካሬ ሳይሆን የራሱ የመንግስት የመረጃ አሰጣጥ የሕዝብ ግንኙነት ድክመትን የሚያሳይ ነው።

የመላው አማራ ሕዝብ ከዳር እስከ ዳር በነቂስ ወጥቶ ወልቃይትን ብሎ ብዙ መከራና ግፍን የተቀበለበትን ጥያቄና ትግል ከሆነው አንዱ የወልቃይት ጉዳይ በዚህ ሰዓት በእጁ መዳፍ ይገኛል።

ስለወልቃይት በሕግ የቀሪውን ጉዳይ የማረጋገጥ ስራ በአማራ ክልል መንግስት እና የአማራ ኤሊት ነኝ በሚለው አካል ትክሻ ላይ የሚወድቅ ይሆናል። አብይ አህመድ እስካሁን ከተናገረው ወይም ካደረገው በላይ በዚህ ዙሪያ የሚጠበቅበት ግዴታ እንዳለበት በበኩሌ በፍፁም አይሰማኝም። ወልቃይት የበጌምድር አማራ ነው ከማለት በላይና በአማራ ክልል መንግስት ስር እንዲተዳደር ከማድረግ፣ ለቀጣይ ሂደቱን ነገሮችን ከማመቻቸት ያለፈ ከእሱ የሚጠበቅበት ነገር የለም። ከዛ ውጭ አብይ አህመድ መንደር ለመንደር ወይም ከክልል ክልል እየዞረ የወልቃይትን ጉዳይ ወረቀት ይዞ ሊያስፈፀም አይችልም። ፖስተኛም አይደለም። ማንም እጅና እግሩን አጣጥፎ ተጎልቶ ጊዜውን የሚቆጥር አብይ አህመድ ሁሉንም ነገር ፈትፍቶ እንዲያጎርሰው የሚፈልግ የጠባቂነት መንፈስ የተጠናወተው ሁሉ እጁ ላይ የገባውን ወልቃይትን ሊነጥቁኝ ነው ወይም ተላልፎ ሊሰጥብኝ እያለ ሲነፋረቅ ቢታይ ድክመቱን ከማሳየት ነውሩን ከመግለጥ ያለፈ ትርጉም ያለው ነገር ማሳየት አይችልም።

እርግጥ ነው በሰሜን ሕብረት በስመ የአቢሲኒያ አሻራን የደቡቡ ሐይል ሊንደውና ሊያጠፋው ነው በሚል የወያኔ አጀንዳን በማራገብ ከወያኔ ጋር አብረን ከቆምን ባርጌኒግ ፓወራችን ይጨምራል አብይ አህመድንም ከስልጣኑ ማስወገድ ይቻላል እያለ የሚንቀሳቀስ አካል መልሶ በመሃል የወልቃይት ጉዳይን አስመልክቶ በተቆርቋሪነት ለመንቀሳቀስ ሲሞክር መታየቱ ተጠባቂ እንጅ አዲስ ነገር አይሆንም። በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ጥላቻ የወለዳቸው በስሜት ፈረስ የሚጋልቡ የወያኔ የማደጎ ልጆች ለአላማቸው መሳካት እንደፈለጉ ሲገለባበጡ ሚግ 23 የሚያስንቁ ናቸው። በቀጣይ በየት በኩል ተገልብጠው ሊከሰቱ እንደሚችሉ መገመትም አይቻልም።

እነዚህ አካላት ዶ/ር አብይ አህመድን እንደ አንድ የሕወሓት ስራ አስፈፃሚ እኩል ነጥለው እያብጠለጠሉ ከስልጣኑ እናስወግደዋለን ብለው እየተንቀሳቀሱ መልሰው የአማራ ጥያቄ እየተመለሰ አይደለም ሲሉ፤ ወልቃይት በአብይ አህመድ ተላልፎ ሊሰጥ ነው የሚል ጩኸትም ሲያሰሙ መመልከት የሚያረጋግጥልን ጉዳይ የሞራል ቫልዩና መርህ አልባ መሆናቸውን ነው።

በመጨረሻም

ለአማራ ሕዝብ እንቆረቆራለን የምንል ሰዎች ቅድሚያ እራሳችንን እንመልከት። ከዛም ከራሳችን ጋር ሆነን የራሳችንን አጀንዳ ቀርፀን ለአማራ ሕዝብ ሁለንተናዊ ጥቅም መረጋገጥ ደፋ ቀና ለማለት ሙከራ እናድርግ። አለበለዚያ በተመለደው በጠላት አጀንዳ በስማ በለው ስንወራጭ፣ አካኪ ዘራፍ እያልን ስንፏልል፣ ውለን ብናነጋ በውጤቱ ከአንዱም ሳንሆን እንደዳከርንና አረፋችንን እንደደፈቅን አወዳደቃችንን አበላሽተን ከመውደቅ ከፍ ያለ ድል ልንነሳው የምንችለው ጠላት አይኖረንም። ከጅምሩ የተከተልነው መስመር በእኛ የተነደፈ ወይም በእኛ የቀየሰ መንገድ አይደለምና። ስለሆነም የጠላት አጀንዳን ተሸክመን በጠላት መንገድ እየተመላለስን ጠላትን ለማሸነፍ ማሰብ የሞኝነታችንን ጥግና የአወዳደቃችንን ሁኔታ ከማሳየት ያለፈ አሸናፊነታችን አያረጋግጥም።

ቶማስ ጀጃው ሞላ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Opinions Tagged With: operation dismantle tplf, wolkayit

Reader Interactions

Comments

  1. ጌታቸው አበራ says

    June 8, 2022 12:45 pm at 12:45 pm

    ጸሃፊው ያቀረበው ሃሳብ እውነት ከሆነ: ይህ ሁሉ ችግርና የጦርነት ስጋት እያለ : መንግስት ያንን አካባቢ ከታጠቁ ሃይሎች ለማጥራት የሚያደርገው ነገርና እንደምንሰማው ከሆነ : እስካሁን ለዚያ አካባቢ ምንም አይነት በጀት አለመመደቡ ለምን ይሆን? ጸሃፊው የመንግስት PR ችግር ነው ብሎ እንደጠቀሰው: መንግስት በየጊዜው ተገቢ ውሳኔዎችን እየሰጠ: ለህዝብ በተገቢው መንገድና ፍጥነት ካላሳወቀና አገሪቱን እያረጋጋ ካልሄደ: ግልፅነት የጎደለውን አካሄድና ለአገርና ለወገን የማይበጁ ደካማና አንዳንዴም “የመሰሪነት” አይነት ፀባይ ያላቸውን ድርጊቶች የሚያዩ “ሌሎች” ጸሃፊው እዚህ የጉለጸውን ሃሳብ ቢያስቡ በደፈናው ሊፈረድባቸው ይችላልን? መሪስ “እሱ ምን ያርግ” እየተባለ እንዴትስ ሊመራ ይቻለዋል? መሪነቱ የሚሆነውን ሁሉ ነገር በጊዜ ሊያደርግና ሊመራ አይደለምን ?

    Reply
  2. yelemchenu says

    June 10, 2022 09:19 am at 9:19 am

    አቢይ አህመድ ዛሬ የተናገረ ዉን ነገ ደግሞት ያውቃል ወይ ? የደመነፍስ መሪ አደለምን። የሚመራበት መሪ ዕቅድም ሆነ ፍኖተ ካርታ የሌለዉ ደንባራ መሪ አየደለምን?

    Reply
  3. 2nd-editor says

    July 13, 2022 02:22 pm at 2:22 pm

    What does western tigray mean or refer to? The demari pm repeatedly said that in parliament. May be this editor would care to enlighten us all? Apparently, the editor seems in the know. Just to add we would see how you spin this if and when western tigray returns to tplf rule. May that day never come – if it never did even that is too soon.

    Reply
    • Editor says

      July 17, 2022 05:20 pm at 5:20 pm

      Western Tigray is found only in the mind of TPLFs. But Wolkait will NEVER be under the control of TPLF thugs – EVER!!

      Editor

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule