• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጠቅላይ ቤተ ክህነት፤ በኦሮሚያ የተፈጸመው ኦርቶዶክሳውያንን የማጽዳት እንቅስቃሴ ነው

September 1, 2020 11:55 am by Editor Leave a Comment

የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ጥያቄዎቿን እንዲቀበላት ጠየቀች

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሱ ያሉ ተደጋጋሚ ጥቃቶች እንደሚነገረው “በሽግግር ወቅት የሚያጋጥሙ” ተብለው ብቻ የሚታለፉ ሳይሆኑ፣ የተሳሳቱ ርዕዮተ ዓለማዊ ትርክቶችንና ጂኦ ፖለቲካዊ ዳራዎችን መነሻ በማድረግ በተቀነባበረና በተደራጀ ሥልት የሚፈጸሙ ኦርቶዶክሳውያንን የማፅዳት እንቅስቃሴዎች መሆናቸውን ቤተ ክህነት ገለጸች።

የኦሮምኛ ቋንቋ ድምፃዊው ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ምክንያት በማድረግ በኦሮሚያ በተለያዩ አካባቢዎች በስድስት ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኙ 25 ወረዳዎች በሚኖሩ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን የገለጸችው ቤተ ክህነት፣ በጥቅምት ወርና በጥር ወር ከጥምቀት በዓል አከባበር ጋር በተያያዘ እንዲሁም በሃጫሉ ሞት ምክንያት በአቢያተ ክርስቲያናትና ምዕመናን ላይ የተፈጸመው ድርጊት ግልጽ እየሆነ መምጣቱንና በአጭር ጊዜ ሳይፈታ ቀርቶ በዚሁ ከቀጠለ የከፋ ፍጻሜ ሊያስከትል እንደሚችል አሳውቃለች።

በተለይ ከሰኔ 23 እስከ 24 ቀን 2012 ዓ.ም. በቤተ ክርስቲያናትና ምዕመናኑ ላይ የደረሰው አሰቃቂና ግፍ የተሞላበት ግድያ፣ አካል ማጉደል፣ ንብረት ማውደም፣ ዝርፊያና ማፈናቀል እንደ ሌላው ጊዜ በቀላሉ ሊታለፍ እንደማይችል ተገልጿል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ውይይት በማድረግ ጥቃቱ በተፈጸመባቸው አካባቢዎች በአካል ተገኝቶ የደረሰውን ጉዳት የሚያጠና ዓብይ ኮሚቴ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት እንዲቋቋም መደረጉን ቤተ ክህነት በሰጠችው መግለጫ አስታውቃለች።

በርካታ አካላት ጉዳቱ በደረሰባቸው አካባቢዎች ተጉዘው እንዳስተዋሉት ከሰኔ 23 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ ለሦስት ቀናት በተፈጸመ ጥቃት፤

  • 67 ምዕመናን በግፍ ሲገደሉ፣
  • በ38 ምዕመናን ላይ ከባድ
  • በ29 ምዕመናን ላይ ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል
  • ከ7,000 (ሰባት ሺሕ) በላይ ምዕመናን ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል
  • እጅግ በርካቶች ለተለያዩ ሥነ ልቦናዊና ሥነ አዕምሯዊ ቀውስ ተዳርገዋል
  • ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረታቸው በዘረፋና በእሳት መውደሙንም ጠቁማለች።

በኦሮሚያና በሌሎችም ክልሎች አንዳንድ አካባቢዎች በቤተ እምነቶችና በምዕመናኑ ላይ በተደጋጋሚ እየደረሱ የሚገኙ ሥልታዊ የሆኑ ግልጽ ተፅዕኖዎች በዓይነትና በመጠን እየጨመሩ መምጣታቸውን ቤተ ክህነት ጠቁማለች። አብዛኛዎቹ የክልሉ አመራሮች ለመወያየት ባሳዩት በጎ ፈቃድ ጥቃቱንና ተፅዕኖውን በተወሰነ ደረጃ ለመግታት ቢቻልም፣ በሰኔ ወር በተለይ በኦሮሚያ ላይ የተፈጸመው ከባድና አሳዛኝ መሆኑን ኮሚቴው ገልጿል።

ችግሮችን በጋራ ለመፍታት ለክልሉ መንግሥት የመፍትሔ ጥያቄዎችን ቤተ ክርስቲያን ብታቀርብም፣ ጥያቄዋ ችላ መባሉንና ክልሉ አለመቀበሉ እንዳሳዘናት ቤተ ክህነት ገልጻለች። በክልሉ ቅዱስ ሲኖዶስ ያገደው ሕገወጥ ቡድን ለቤተ ክርስቲያን በሕግ የተሰጧትን መብቶች ከመጋፋት ጀምሮ የአስተዳደር መዋቅሯን እስከ ማፍረስ ድረስ የተዳፈረው፣ የክልሉ መንግሥት ለጥያቄዎቿ አፋጣኝ ምላሽ ባለመስጠቱ መሆኑንም ቤተ ክህነት አስታውቃለች። የትናንቱን ችግር ለማከምና ነገ በከፋ መልኩ ሊመጣ የሚችለውን ለማስቀረት እንዲቻልና በጋራ ከመሥራት ውጪ መፍትሔ እንደሌለም በመጠቆም፣ የክልሉ መንግሥት ጥያቄዎቿን ተቀብሎ በጋራ ለመሥራት ዝግጁ እንዲሆን ጠይቃለች።

የተሳሳቱ አስተሳሰቦችና የሐሰት ትርክቶች በመንዛት ሆን ተብሎ የሚፈጸም ኦርቶዶክሳውያንን የማሳቀቅና የማዳከም ሃይማኖት ተኮር ጥቃትን አስቀድሞ በመከላከል፣ ፍትሕን በማስፈን ተጎጂዎችን በአግባቡ በመካስና በማቋቋም የፌዴራልና የክልል መንግሥታት ሕገ መንግሥታዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ ቤተ ክህነት ጠይቃለች።

መንግሥት “አጥፊዎችን አንታገስም፤ ተገቢውን ፍትሕ እንሰጣለን፤ የተጎዱትን እንክሳለን” ማለቱን ያስታወሰችው ቤተ ክህነት፣ መንግሥት የገባውን ቃል ይፈጽማል በማለት በትዕግሥት ብትጠብቅም በወቅቱና በብቃት ሲወጣ አለማየቷንም ጠቁማለች። በመሆኑም ከላይ የተገለጸውን ኮሚቴ በማቋቋም ጥቃቱ በደረሰባቸው አካባቢዎች በመላክ ምዕመናን የደረሰባቸውን ሁሉ መመልከት መቻሏንና ከፍተኛ ሐዘን እንደተሰማትም አስታውቃለች። አጥፊዎችን ሁሉ በቁጥጥር ሥር በማዋልና በሕግ ተጠያቂ በማድረግ የፍትሕ ርትዕ እስከ መጨረሻው እንዲሰፍን የማድረግ ኃላፊነት የመንግሥት በመሆኑ ያንን ተግብሮ ለማየት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላትም ተናግራለች። አንዳንድ የመንግሥት ባለሥልጣናትና የፖለቲካ ፓርቲዎች የግፉዓን ሰማዕታቱን መጠቃት አላግባብ ለቡድናዊና ፖለቲካ ትርፍ በመጠቀም ሐዘኗን መሳለቂያ ከማድረግ እንዲቆጠቡ አሳስባ፣ መንግሥት ተገቢውን ክትትል በማድረግ እንዲያስታግስላትም አሳስባለች። (ታምሩ ጽጌ፤ ሪፖርተር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Left Column, Religion Tagged With: jawar massacre, oromia, orthodox church

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule