• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጠቅላይ ቤተ ክህነት፤ በኦሮሚያ የተፈጸመው ኦርቶዶክሳውያንን የማጽዳት እንቅስቃሴ ነው

September 1, 2020 11:55 am by Editor Leave a Comment

የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ጥያቄዎቿን እንዲቀበላት ጠየቀች

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሱ ያሉ ተደጋጋሚ ጥቃቶች እንደሚነገረው “በሽግግር ወቅት የሚያጋጥሙ” ተብለው ብቻ የሚታለፉ ሳይሆኑ፣ የተሳሳቱ ርዕዮተ ዓለማዊ ትርክቶችንና ጂኦ ፖለቲካዊ ዳራዎችን መነሻ በማድረግ በተቀነባበረና በተደራጀ ሥልት የሚፈጸሙ ኦርቶዶክሳውያንን የማፅዳት እንቅስቃሴዎች መሆናቸውን ቤተ ክህነት ገለጸች።

የኦሮምኛ ቋንቋ ድምፃዊው ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ምክንያት በማድረግ በኦሮሚያ በተለያዩ አካባቢዎች በስድስት ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኙ 25 ወረዳዎች በሚኖሩ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን የገለጸችው ቤተ ክህነት፣ በጥቅምት ወርና በጥር ወር ከጥምቀት በዓል አከባበር ጋር በተያያዘ እንዲሁም በሃጫሉ ሞት ምክንያት በአቢያተ ክርስቲያናትና ምዕመናን ላይ የተፈጸመው ድርጊት ግልጽ እየሆነ መምጣቱንና በአጭር ጊዜ ሳይፈታ ቀርቶ በዚሁ ከቀጠለ የከፋ ፍጻሜ ሊያስከትል እንደሚችል አሳውቃለች።

በተለይ ከሰኔ 23 እስከ 24 ቀን 2012 ዓ.ም. በቤተ ክርስቲያናትና ምዕመናኑ ላይ የደረሰው አሰቃቂና ግፍ የተሞላበት ግድያ፣ አካል ማጉደል፣ ንብረት ማውደም፣ ዝርፊያና ማፈናቀል እንደ ሌላው ጊዜ በቀላሉ ሊታለፍ እንደማይችል ተገልጿል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ውይይት በማድረግ ጥቃቱ በተፈጸመባቸው አካባቢዎች በአካል ተገኝቶ የደረሰውን ጉዳት የሚያጠና ዓብይ ኮሚቴ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት እንዲቋቋም መደረጉን ቤተ ክህነት በሰጠችው መግለጫ አስታውቃለች።

በርካታ አካላት ጉዳቱ በደረሰባቸው አካባቢዎች ተጉዘው እንዳስተዋሉት ከሰኔ 23 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ ለሦስት ቀናት በተፈጸመ ጥቃት፤

  • 67 ምዕመናን በግፍ ሲገደሉ፣
  • በ38 ምዕመናን ላይ ከባድ
  • በ29 ምዕመናን ላይ ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል
  • ከ7,000 (ሰባት ሺሕ) በላይ ምዕመናን ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል
  • እጅግ በርካቶች ለተለያዩ ሥነ ልቦናዊና ሥነ አዕምሯዊ ቀውስ ተዳርገዋል
  • ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረታቸው በዘረፋና በእሳት መውደሙንም ጠቁማለች።

በኦሮሚያና በሌሎችም ክልሎች አንዳንድ አካባቢዎች በቤተ እምነቶችና በምዕመናኑ ላይ በተደጋጋሚ እየደረሱ የሚገኙ ሥልታዊ የሆኑ ግልጽ ተፅዕኖዎች በዓይነትና በመጠን እየጨመሩ መምጣታቸውን ቤተ ክህነት ጠቁማለች። አብዛኛዎቹ የክልሉ አመራሮች ለመወያየት ባሳዩት በጎ ፈቃድ ጥቃቱንና ተፅዕኖውን በተወሰነ ደረጃ ለመግታት ቢቻልም፣ በሰኔ ወር በተለይ በኦሮሚያ ላይ የተፈጸመው ከባድና አሳዛኝ መሆኑን ኮሚቴው ገልጿል።

ችግሮችን በጋራ ለመፍታት ለክልሉ መንግሥት የመፍትሔ ጥያቄዎችን ቤተ ክርስቲያን ብታቀርብም፣ ጥያቄዋ ችላ መባሉንና ክልሉ አለመቀበሉ እንዳሳዘናት ቤተ ክህነት ገልጻለች። በክልሉ ቅዱስ ሲኖዶስ ያገደው ሕገወጥ ቡድን ለቤተ ክርስቲያን በሕግ የተሰጧትን መብቶች ከመጋፋት ጀምሮ የአስተዳደር መዋቅሯን እስከ ማፍረስ ድረስ የተዳፈረው፣ የክልሉ መንግሥት ለጥያቄዎቿ አፋጣኝ ምላሽ ባለመስጠቱ መሆኑንም ቤተ ክህነት አስታውቃለች። የትናንቱን ችግር ለማከምና ነገ በከፋ መልኩ ሊመጣ የሚችለውን ለማስቀረት እንዲቻልና በጋራ ከመሥራት ውጪ መፍትሔ እንደሌለም በመጠቆም፣ የክልሉ መንግሥት ጥያቄዎቿን ተቀብሎ በጋራ ለመሥራት ዝግጁ እንዲሆን ጠይቃለች።

የተሳሳቱ አስተሳሰቦችና የሐሰት ትርክቶች በመንዛት ሆን ተብሎ የሚፈጸም ኦርቶዶክሳውያንን የማሳቀቅና የማዳከም ሃይማኖት ተኮር ጥቃትን አስቀድሞ በመከላከል፣ ፍትሕን በማስፈን ተጎጂዎችን በአግባቡ በመካስና በማቋቋም የፌዴራልና የክልል መንግሥታት ሕገ መንግሥታዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ ቤተ ክህነት ጠይቃለች።

መንግሥት “አጥፊዎችን አንታገስም፤ ተገቢውን ፍትሕ እንሰጣለን፤ የተጎዱትን እንክሳለን” ማለቱን ያስታወሰችው ቤተ ክህነት፣ መንግሥት የገባውን ቃል ይፈጽማል በማለት በትዕግሥት ብትጠብቅም በወቅቱና በብቃት ሲወጣ አለማየቷንም ጠቁማለች። በመሆኑም ከላይ የተገለጸውን ኮሚቴ በማቋቋም ጥቃቱ በደረሰባቸው አካባቢዎች በመላክ ምዕመናን የደረሰባቸውን ሁሉ መመልከት መቻሏንና ከፍተኛ ሐዘን እንደተሰማትም አስታውቃለች። አጥፊዎችን ሁሉ በቁጥጥር ሥር በማዋልና በሕግ ተጠያቂ በማድረግ የፍትሕ ርትዕ እስከ መጨረሻው እንዲሰፍን የማድረግ ኃላፊነት የመንግሥት በመሆኑ ያንን ተግብሮ ለማየት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላትም ተናግራለች። አንዳንድ የመንግሥት ባለሥልጣናትና የፖለቲካ ፓርቲዎች የግፉዓን ሰማዕታቱን መጠቃት አላግባብ ለቡድናዊና ፖለቲካ ትርፍ በመጠቀም ሐዘኗን መሳለቂያ ከማድረግ እንዲቆጠቡ አሳስባ፣ መንግሥት ተገቢውን ክትትል በማድረግ እንዲያስታግስላትም አሳስባለች። (ታምሩ ጽጌ፤ ሪፖርተር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, Religion Tagged With: jawar massacre, oromia, orthodox church

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule