• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጠቅላይ ቤተ ክህነት፤ በኦሮሚያ የተፈጸመው ኦርቶዶክሳውያንን የማጽዳት እንቅስቃሴ ነው

September 1, 2020 11:55 am by Editor Leave a Comment

የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ጥያቄዎቿን እንዲቀበላት ጠየቀች

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሱ ያሉ ተደጋጋሚ ጥቃቶች እንደሚነገረው “በሽግግር ወቅት የሚያጋጥሙ” ተብለው ብቻ የሚታለፉ ሳይሆኑ፣ የተሳሳቱ ርዕዮተ ዓለማዊ ትርክቶችንና ጂኦ ፖለቲካዊ ዳራዎችን መነሻ በማድረግ በተቀነባበረና በተደራጀ ሥልት የሚፈጸሙ ኦርቶዶክሳውያንን የማፅዳት እንቅስቃሴዎች መሆናቸውን ቤተ ክህነት ገለጸች።

የኦሮምኛ ቋንቋ ድምፃዊው ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ምክንያት በማድረግ በኦሮሚያ በተለያዩ አካባቢዎች በስድስት ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኙ 25 ወረዳዎች በሚኖሩ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን የገለጸችው ቤተ ክህነት፣ በጥቅምት ወርና በጥር ወር ከጥምቀት በዓል አከባበር ጋር በተያያዘ እንዲሁም በሃጫሉ ሞት ምክንያት በአቢያተ ክርስቲያናትና ምዕመናን ላይ የተፈጸመው ድርጊት ግልጽ እየሆነ መምጣቱንና በአጭር ጊዜ ሳይፈታ ቀርቶ በዚሁ ከቀጠለ የከፋ ፍጻሜ ሊያስከትል እንደሚችል አሳውቃለች።

በተለይ ከሰኔ 23 እስከ 24 ቀን 2012 ዓ.ም. በቤተ ክርስቲያናትና ምዕመናኑ ላይ የደረሰው አሰቃቂና ግፍ የተሞላበት ግድያ፣ አካል ማጉደል፣ ንብረት ማውደም፣ ዝርፊያና ማፈናቀል እንደ ሌላው ጊዜ በቀላሉ ሊታለፍ እንደማይችል ተገልጿል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ውይይት በማድረግ ጥቃቱ በተፈጸመባቸው አካባቢዎች በአካል ተገኝቶ የደረሰውን ጉዳት የሚያጠና ዓብይ ኮሚቴ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት እንዲቋቋም መደረጉን ቤተ ክህነት በሰጠችው መግለጫ አስታውቃለች።

በርካታ አካላት ጉዳቱ በደረሰባቸው አካባቢዎች ተጉዘው እንዳስተዋሉት ከሰኔ 23 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ ለሦስት ቀናት በተፈጸመ ጥቃት፤

  • 67 ምዕመናን በግፍ ሲገደሉ፣
  • በ38 ምዕመናን ላይ ከባድ
  • በ29 ምዕመናን ላይ ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል
  • ከ7,000 (ሰባት ሺሕ) በላይ ምዕመናን ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል
  • እጅግ በርካቶች ለተለያዩ ሥነ ልቦናዊና ሥነ አዕምሯዊ ቀውስ ተዳርገዋል
  • ከአምስት ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረታቸው በዘረፋና በእሳት መውደሙንም ጠቁማለች።

በኦሮሚያና በሌሎችም ክልሎች አንዳንድ አካባቢዎች በቤተ እምነቶችና በምዕመናኑ ላይ በተደጋጋሚ እየደረሱ የሚገኙ ሥልታዊ የሆኑ ግልጽ ተፅዕኖዎች በዓይነትና በመጠን እየጨመሩ መምጣታቸውን ቤተ ክህነት ጠቁማለች። አብዛኛዎቹ የክልሉ አመራሮች ለመወያየት ባሳዩት በጎ ፈቃድ ጥቃቱንና ተፅዕኖውን በተወሰነ ደረጃ ለመግታት ቢቻልም፣ በሰኔ ወር በተለይ በኦሮሚያ ላይ የተፈጸመው ከባድና አሳዛኝ መሆኑን ኮሚቴው ገልጿል።

ችግሮችን በጋራ ለመፍታት ለክልሉ መንግሥት የመፍትሔ ጥያቄዎችን ቤተ ክርስቲያን ብታቀርብም፣ ጥያቄዋ ችላ መባሉንና ክልሉ አለመቀበሉ እንዳሳዘናት ቤተ ክህነት ገልጻለች። በክልሉ ቅዱስ ሲኖዶስ ያገደው ሕገወጥ ቡድን ለቤተ ክርስቲያን በሕግ የተሰጧትን መብቶች ከመጋፋት ጀምሮ የአስተዳደር መዋቅሯን እስከ ማፍረስ ድረስ የተዳፈረው፣ የክልሉ መንግሥት ለጥያቄዎቿ አፋጣኝ ምላሽ ባለመስጠቱ መሆኑንም ቤተ ክህነት አስታውቃለች። የትናንቱን ችግር ለማከምና ነገ በከፋ መልኩ ሊመጣ የሚችለውን ለማስቀረት እንዲቻልና በጋራ ከመሥራት ውጪ መፍትሔ እንደሌለም በመጠቆም፣ የክልሉ መንግሥት ጥያቄዎቿን ተቀብሎ በጋራ ለመሥራት ዝግጁ እንዲሆን ጠይቃለች።

የተሳሳቱ አስተሳሰቦችና የሐሰት ትርክቶች በመንዛት ሆን ተብሎ የሚፈጸም ኦርቶዶክሳውያንን የማሳቀቅና የማዳከም ሃይማኖት ተኮር ጥቃትን አስቀድሞ በመከላከል፣ ፍትሕን በማስፈን ተጎጂዎችን በአግባቡ በመካስና በማቋቋም የፌዴራልና የክልል መንግሥታት ሕገ መንግሥታዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ ቤተ ክህነት ጠይቃለች።

መንግሥት “አጥፊዎችን አንታገስም፤ ተገቢውን ፍትሕ እንሰጣለን፤ የተጎዱትን እንክሳለን” ማለቱን ያስታወሰችው ቤተ ክህነት፣ መንግሥት የገባውን ቃል ይፈጽማል በማለት በትዕግሥት ብትጠብቅም በወቅቱና በብቃት ሲወጣ አለማየቷንም ጠቁማለች። በመሆኑም ከላይ የተገለጸውን ኮሚቴ በማቋቋም ጥቃቱ በደረሰባቸው አካባቢዎች በመላክ ምዕመናን የደረሰባቸውን ሁሉ መመልከት መቻሏንና ከፍተኛ ሐዘን እንደተሰማትም አስታውቃለች። አጥፊዎችን ሁሉ በቁጥጥር ሥር በማዋልና በሕግ ተጠያቂ በማድረግ የፍትሕ ርትዕ እስከ መጨረሻው እንዲሰፍን የማድረግ ኃላፊነት የመንግሥት በመሆኑ ያንን ተግብሮ ለማየት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላትም ተናግራለች። አንዳንድ የመንግሥት ባለሥልጣናትና የፖለቲካ ፓርቲዎች የግፉዓን ሰማዕታቱን መጠቃት አላግባብ ለቡድናዊና ፖለቲካ ትርፍ በመጠቀም ሐዘኗን መሳለቂያ ከማድረግ እንዲቆጠቡ አሳስባ፣ መንግሥት ተገቢውን ክትትል በማድረግ እንዲያስታግስላትም አሳስባለች። (ታምሩ ጽጌ፤ ሪፖርተር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Religion Tagged With: jawar massacre, oromia, orthodox church

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule