• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለኮፍያና ለባጅ ከ415 ሺህ ዶላር በላይ ከባንክ መውሰዱን ዋልታ አመነ

September 28, 2020 12:00 pm by Editor Leave a Comment

“ከ69 ሚሊዮን ዶላር በላይ ከመመሪያ ውጪ ከኢትዮጵያ ባንክ መባከኑ በሰነድ ተረጋገጠ” በሚል ርዕስ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቀድሞ ፕሬዝደንት አቶ ባጫ ጊና የተፈረመበትን ሰነድ ዋቢ አድርጎ ባሰናዳው ወሬ በ2010 ከብሔራዊ ባንክ መመሪያ ውጪ በትንሹ ከ69 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ መሰጠቱን ሸገር 102.1 በመጥቀስ ዘግበን ነበር፡፡

በዚሁ ዓመት በግንቦት ወር መመሪያው የውጭ ምንዛሬ እንዲያገኙ ከተፈቀደላቸው የሥራ ዘርፎች ውጪ ላሉ ወይም መመሪያው ለማይመለከታቸው 5 ድርጅቶች በድምሩ 11 ሚሊዮን 841,583 የአሜሪካ ዶላር እንደተሰጠ ከተገኘው ሰነድ በመጥቀስ በዘገባው ተመልክቷል፡፡

በዚሁ ሰነድ ላይ ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል 500,000 የአሜሪካ ዶላር እንደተፈቀደለት ተጽፏል፡፡

ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ለሸገር በላከው ማስተባበያ የውጭ ምንዛሬው የተሰጠኝ ሕጋዊ ሂደትን ተከትሎ ነው በማለት በዘገባው ላይ ቅሬታውን በጽሑፍ አቅርቧል፡፡

በዚሁ ደብዳቤ ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል የነበረው ስያሜው ከመጋቢት ወር 2009 ጀምሮ ዋልታ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኮርፖሬት አ.ማ. በሚል እንደተለወጠ የጠቀሰው ድርጅቱ በዘገባው ላይ ከባንኩ ተፈቀደለት ተብሎ የተጠቀሰው የገንዘብ መጠን ትክክል አለመሆኑንም ጠቅሷል፡፡

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የተፈረመው ሰነድ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል 5መቶ ሺህ ዶላር ተፈቅዶለታል ቢልም፣ ዋልታ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ኮርፖሬት አ.ማ በወቅቱ የተሰጠኝ የውጭ ምንዛሬ 415 ሺህ 500 ዶላር ብቻ ነው ሲል ለሸገር ነግሯል፡፡

ይህን የውጭ ምንዛሬ ያገኘሁትም በ2010 ዓ.ም ይካሄዳል ተብሎ ለነበረው የሕዝብና ቤቶች ቆጠራ 190ሺህ ኮፍያ እና 180 ሺህ ባጅ ከነማንጠልጠያው ለማቅረብ ከስታትስቲክስ ኤጀንሲ ጋር በደረስሁት ስምምነት መሠረት ነው ሲል በደብዳቤው ጠቅሷል፡፡ (@ ተህቦ ንጉሴ፤ ሸገር 102.1)

ዋልታ የሚዲያ ተቋም ከመሆኑ አኳያ ለሕዝብና ቤት ቆጠራ ኮፍያ ማሳተሚያ በሚል ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ዕጥረት ካለባት አገር ግማሽ ሚሊዮን ዶላር መውሰዱ ትልቅ ጥያቄ የሚጭር ነው።

ከዚህ ሌላ በአሁኑ ጊዜ በየክፍለሃገሩ ምርቱን ለውጭ ገበያ የሚያቀርብ የኢንዱስትሪ ፓርት ተከፍቶ ባለበት ሁኔታ ይህንን ያህል የውጭ ምንዛሪ ለኮፍያና ለባጅ ማውጣቱ ዋልታ ከጅምሩ የህወሓት ልሳን የነበረ ከመሆኑ ጋር ተዳምሮ ሌላ ጥያቄ የሚያስነሳ ነው።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: commer, tplf, walta

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule