• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጃዋር “ቄሮ”፣ ባልደረቦቹና ባለሥልጣናት በአሸባሪነት እንዲፈረጁ ተመድ የቀረበለትን ክስና ማስረጃ ተቀበለ

December 4, 2019 08:20 pm by Editor 4 Comments

“ግድያ ከተፈጸመ በኋላ አስከሬኖችን ለመቀጣጫ ተጠቅመዋል” አሉ ፕሮፌሰር ጌታቸው። ሲያስረዱም “ገድለው የሰውነትን ክፍል በመበጣጠስ ሜዳ ላይ ጥለዋል። ይህ የሆነው አንተም እንዲህ ትሆናለህ፣ ለቀህ ጥፋ፣ ሂድ፣ የሚል የመቀጣጫ ማሳያ ለመጠቀም ሲባል ነው። ይህንን ያዩ፣ የፈሩ ቤተክርስቲያን ተሸሸጉ፣ ጫካ ውስጥ ተጠለሉ። ወደ ማይታወቅ ቦታ አመለጡ”።  

ይህ የተባለው ትግሉን አጠናቆ ወደ ቤቱ የገባውና አደረጃጀት የሌለው መስዋዕትነት የከፈለውን ቄሮ ሳይሆን በጃዋር መሃመድ የሚመራ፣ ከፍተኛ ገንዘብ የሚያዘዋውር፣ የተደራጀ፣ ትዕዛዝ አመንጪ ያለው፣ አዛዥና የዕዝ ሠንሠለት ያለው፣ የማዘዣ ኮማንድ የተበጀለት … የጥፋት ኃይል በአሸባሪነት እንዲፈረጅ ጥያቄ በቀረበበት ወቅት ነው።

በማስረጃ ተደግፎ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ክስ የቀረበበት ይህ ኃይል በአሸባሪነት እንዲፈረጅና ዓለም ይህ ድርጅት ምስራቅ አፍሪቃን ሳያተራምስ እንዲከስም አስቸኳይ ምላሽ እንዲሰጥበት፣ ጉዳዩ አሳሳቢና ጊዜ የማይሰጥ መሆኑንን ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ለተመድ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ተጠሪዎች ማብራራቱን ይፋ አድርጓል።

ከመረጃ ቲቪ ባልደረባ ጋር ቃለ ምልልስ ያካሄዱት ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌና እስክንድር ነጋ እንዳሉት የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ለቀረበለት ጥያቄ ቀና የሚባል መልስ ሰጥቷል። ከቀረበለት ማስረጃ በተጨማሪ ጉዳዩን በራሳቸው አግባብ እንደሚያጣሩና አስቸኳይ ምላሽ እንደሚሰጥ ማስታወቁን ገልጠዋል።

በኢትዮጵያ ተመድ ያስቀመጣቸው የጄኖሳይድ ጥቃት ስለመኖሩ ማስረጃ፣ ሰለባዎች በማንና እንዴት እንደተጠቁ በሰነድና በመረጃ መቅረቡን ያመለከተው እስክንድር የአልሸባብ፣ የሙጃሂድና የአልቃይዳን አፈጣጠር ለምሳሌነት መነሳቱን ጠቁሟል።

የተመድ ባለሥልጣናት ስማቸው እንዳይጠቀስ በማስገንዘብ ጉዳዩን በውል እንደሚያዩት ፕሮፌሰር ጌታቸው ተናግረዋል።

ከተመድ ጋር የተደረገው ውይይት ኢትዮጵያውያን በዋሽንግቶን ዲሲ ተወያተው ያሳለፉት ውሳኔ አካል እንደሆነ ያስታወሰው እስክንድር፣ ጃዋር የሚመራው ቄሮ የፈጸመውን የዘር ማጽዳት ወንጀል የሚያጣራ ግብረኃይል መቋቋሙንና ይህም ግብረኃይል ተጨማሪ መረጃዎችን በማሰባሰብ ለባለሥልጣናቱ ተጨማሪ ግብዓት እንደሚያቀርብ ጠቁሟል።

“ጤናማ ቄሮ አለ፣ ጽንፈኛ ቄሮ አለ። ጤማዎቹ ትግላቸውን ጨርሰው ወደ ቤታቸው ገብተዋል” ሲል ማብራሪያውን የሰጠው እስክንድር፣ አሁን በጽንፈኛነት የተሰማራው ኃይል ድርጊቱን ሲፈጽም “ቄሮ ነኝ” እያለ ራሱን በመግለጽ በመሆኑ በሌላ ስም ሊጠራ እንደማይችል አመልክቷል። መሪውም ጃዋር መሆኑንና ከመንግሥት እና (ከፓርቲ) መዋቅር ውስጥም ተባባሪ እንዳላቸው አክሏል።

ፕሮፌስር ጌታቸው እንዳሉት ይህ ኃይል የራሱ ሚዲያ ያለውና የጥፋት ጥሪውን በዚሁ ሚዲያው እንደሚያሰራጭ፣ ባለቤቱም የዚሁ ኃይል መሪ እንደሆነ ጠቁመዋል። ይህንንም በማስረጃ ማቅረባቸውን ይፋ አድርገዋል። ይህንን የገለጹት ከተመድ ባለሥልጣናት ለቀረበ ጥያቄ ሲመለሱ እንደሆነም አመልክተዋል።

ጃዋር መሀመድ “ያ – ቄሮ” በማለት መመሪያ እንደሚሰጥ ሕዝብ በተደጋጋሚ ያየው ሃቅ ሲሆን፣ በሲዳማ የደረሰው ቀውስ እየተፋፋመ በተለይ ቡና ጃዋር መመሪያ ይሰጥ እንደነበር ጎልጉል ምንጮቹን ጠቅሶ መዘገቡ የሚታወስ ነው። ጃዋር ራሱን ሰላማዊ ታጋይ አድርጎ ያቅርብ እንጂ ሬዲዮ፣ ሁለት የቴሌቪዥን ጣቢያ፣ ጋዜጦች፣ መጽሄቶችና በርካታ የማኅበራዊ ሚዲያ ሠራዊት ያለው አካል መሆኑ ይታወቃል። መንግሥትን በአንድ ቀን የመገልበጥ አቅም ያለው እንደሆንም በአደባባይ የሚናገር ከመሆኑ በላይ ከመከላከያ ሚኒስትር ለማ መገርሳ ጋር በጥምረት እንደሚሠራ መረጃዎች አሉ።

ከጽንፈኛው ቄሮ ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ ስማቸው የማይነሳው አቶ በቀለ ገርባ በቄሮ አደረጃጀት ውስጥ (መሪም ናቸው ይባላል) ወሳኝ ቦታ እንዳላቸው የመረጃ ሰዎች ለውጡ በተጋጋለበት ወቅት ምስክርነት ሲሰጡ እንደነበር፣ ከለውጡም በኋላ ከጃዋር ጋር ይፋዊ አጋር መሆናቸውና በቅጽበት፣ በሚታይ ሁኔታ ወደ ጽንፈኛነት መቀየራቸው ደግሞ የዚሁ የጽንፈኛ ቡድን ቁንጮ መሆናቸውን የሚያመሳክር እንደሆነ ለጉዳዩ የሚቀርቡ የሚናገሩት የአደባባይ ምሥጢር ነው።

ይህንን ጽሁፍ እስከምናትተምናበት ድረስ ከተከሳሾቹ ወገን የተባለ ነገር የለም። ዜናውን የሰሙ አካላት ግን የተለያይ ስሜት እያንጸባረቁ ነው። ተመድ አምኖ ጊዜያዊ እርምጃ ከወሰደ በእነ ጃዋር ዙሪያ ባሉ አካላት ላይ የጉዞ ገደብ ሊጥል ይችላል፤ ገንዘባቸውም እንዲታገድ እንደሚያደርግ ይጠበቃል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, jawar massacre, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Engdasew says

    December 5, 2019 09:31 pm at 9:31 pm

    It’s right

    Reply
  2. Alem says

    December 6, 2019 03:52 am at 3:52 am

    Professor Getachew Haile has a history of
    changing facts to fit his personal agenda.
    Information he says he got is from a phone
    Conversation with his friends in Addis.
    We need to remember he resides in New York.
    Remember also he wants us to believe him
    that he talked with UN officials and the officials
    don’t want any one to know their identity.
    You believe that? That is dishonest and a wicked lie.

    Reply
  3. Tesfa says

    December 6, 2019 04:20 am at 4:20 am

    በዘመነው ዓለም በብሄር ህሳቤ ልባቸው ተነድፎ ልክ እንደ ጫካ አውሬ ለእኔ ብቻ የሚሉት እነዚህ የኦሮሞ የእብድ ስብስቦችን ሴራ ማቆም የሚቻለው እሳትን በእሳት በመመከት ብቻ ነው። በምንም ሂሳብ ይህ የጥፋት ስብስብ ልብ ኑሮት ድርጊቱን የሚያቆም አይደለም። ለምሳሌ በአሜሪካን ሃገር በፕሮፌሰርነት ማእረግ በመምህርነት ደሞዝ የሚከፈለው የጫቱ ምሁር በሩቅና በቅርብ በህዝባችን ላይ የሚጨረውን እሳት በመረጃ ለትምህርት ተቋሙ በማቅረብ ከሥራው እንዲባረር ማድረግ ሌላው ተግባር ሊሆን ይገባል። ሰው እያጋደሉ መደንፋት የለም። የወያኔን ከሥልጣን ወደ ጎን መሆን ተጠቅመው ጊዜው የእኛ ነው የሚሉን እነዚህ የጠባብ – ጠባብ ብሄርተኞች ከወያኔ ቢከፉ እንጂ አይሻሉም። በሙታን አስከሬን የሚጫወቱ። ፎቶ አንስተው በሶሻል ሚዲያዎች ላይ የሚለጥፉ ግሞች ናቸው። በአንድ ስፍራ ሰውን ተሰብስበው ከእየቤቱ እየደበደቡና እየገደሉ ከቤታቸው ካወጡ በህዋላ መኖሪያቸው ላይ እሳት ይለቃሉ። የታሰሩ የቀንድ ከብቶችም ይጮሃሉ። ከውጭ የቆሙት የሞት ጭፍሮች በላሞችና በበጎች የድረሱልኝ ጥሪ ይሳሳቃሉ። በጎናቸው አንድ ሰው እረ እባካችሁ እንስሳትን እንኳን አትግደሉ ቢላቸው በቢለዋ እንደወጉት በሥፍራው የነበሩ የአይን ምስርክሮች ተናግረዋል። ይህ ትውልድ ነው የኦሮሞን ህዝብ ነጻነት የሚያስጠብቀው። የተኩላዎች ጥርቅም።
    የሃበሻው ፓለቲካ ከመሰረቱ የተናጋ በአሽዋ ላይ የተመሰረተ ነው። አዕላፎችን በልቷል፤ ገናም ይበላል። የዛሬ 60 ዓመት የተነሱ የፓለቲካ ጥያቄዎች ዛሬም እንደ አዲስ ተነስተው ሰው ሲናቆርባቸው ማየትና መስማት ምን ያህል ፓለቲካው በአለህበት ሂድ እንደሆነ አመላካች ነው። በዚህ ላይ ወያኔና ሻቢያ በፈጠሩት የብሄር ፓለቲካ ሰው ሁሉ እየገባ ሲማገድ ማየት ተስፋ ያስቆርጣል። የምድሪቱ ችግር ፈጣሪዎች እኛውና እኛው ነን። የውጭ ጠላቶች የእኛን መከፋፈል ተመልክተው ነው የእነርሱ ጉዳይ አስፈጻሚዎች የሚያደርጉን። በፔትሮ ዶላር የሰከሩት አረቦች በሁለት ካምፕ ተከፍለው ምሥራቁን የአፍሪቃ ክፍል እያተራመሱት ይገኛሉ። ሳውዲአረቢያ ለዚህ ቀዳሚዋ ናት። ሁሉም ባይሆኑ አንዳንዶቹ የጥቃቱ ተሳታፊዎች ክርስቲያኖችን መርጠው የሚገሉትና የአምልኮ ሥፍራቸውን የሚያጋዪት በዚህ ተልእኮ ነው። ግብጽ ሌላዋ የሃገራችን በሽታ ናት። አሁን ደግሞ ቱርክም በሶማሊያና ሱዳን በኩል ስራዋን ጀምራለች። የኦሮሞ ህዝብ የወስላታ ፓለቲከኞችን ጥሪ ችላ በማለት ከሃገሩ ህዝብ ጋር በፊትም እንደኖረ ዛሬም በሰላም ለመኖር የሙታን ፓለቲከኞችን ጥሪ ችላ ካላለ የወደፊት እድሉ የጨለመ ነው የሚሆነው። በመሰረቱ የዘርና የጎሳ ፓለቲካ ለማንም አይጠቅምም። ወያኔ ለራሱ የሥልጣን ማቆያ ያመቻቸው የክልል ፓለቲካ አፓርታይድ ነው። ለእኔ ቄሮ ማለት አራጅ፤ የወገኑ አስከሬን ወድቆ እያየ በደስታ የሚፈነጥዝ፤ ኦሮሚያ ለኦሮሞ ብቻ የሚል የእብድ ስብስብ ነው። የጃዋርን የፓለቲካ አስተሳሰብ የሚከተል ሁሉ እንቁራሪት ነው። እሱ ሲጮህ አብሮ የሚጮህ። የራስ እይታና አስተሳሰብ የሌለው ኦና ጭንቅላት። ገና በምድሪቱ ላይ ሊመጣ ያለውን ገመና ሰዎች አሁን ማየት ቢችሉ እጃቸውን በአፋቸው ላይ ይጭኑ ነበር። ግን ቀኑ እስኪ ገልጠው የነብይ ጋጋታ ውስልትና ነው የሚሆነው። ዝም ብሎ ማየት ለኖረ መልካም ነው። ይብቃኝ።

    Reply
  4. Solomon says

    December 8, 2019 05:53 am at 5:53 am

    One of the risks in going to the UN is
    that the agency will investigate the validity
    of the complaint by sifting through all
    available material. That means speeches
    Eskinder made will be looked into.
    If you think Eskinder is a peaceful person
    then you are in for a big surprise.
    Remember also Jawar has a chance
    to defend himself. Another risk is that
    Professor Getachew and Eskinder are
    Amharas. Their collaboration along with
    their U.N. contact (whose identity they are
    keeping secret) will damn their effort
    as ethnically biased thus degrading
    their credibility.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule