• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ

December 13, 2022 09:20 am by Editor Leave a Comment

በሰላም ንግግሩ በተደረሰው ስምምነት መሠረት ተዓማኒ የሆነና ግልጽነት ያለው የሽግግር ፍትሕ የሚፈፀም መሆኑን የፍትሕ ሚኒስቴር ገለጸ።

በሰላም ስምምነቱ በተደረሰው ስምምነት መሠረት ተዓማኒ የሆነና ግልጽነት ያለው የሽግግር ፍትሕ ከአፍሪካ ኅብረት የሽግግር ፍትሕ የፖሊሲ ማዕቀፍ ጋር በተጣጣመ መልኩ የሚፈፀም መሆኑን የፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶክተር) ገልፀዋል።

በተደረሰው ስምምነት መሠረት ግልፅ እና ተዓማኒ የሆነ የሽግግር ፍትሕ ለማስፈን እንደሚሠራ የገለፁት ሚኒስትሩ፤ ለዚህም ከያዝነው ወር ጀምሮ ሰፊ የሆኑ ሥራዎች ሁሉንም አካላት ባሳተፈ መልኩ እንደሚሠራ ነው የገለጹት።

ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሃሳባቸው በሚሰማበት እና ወደ ሽግግር ፍትሕ ለሚደረገው ሂደት የበኩላቸውን ተሳትፎ በሚያደርጉበት ሁኔታ በሚያረጋግጥ መልኩ ተዓማኒነት ያለውና ሁሉን አቀፍ ተጠያቂነት እንዲሰፍን ይሠራል ብለዋል።

በአጠቃላይ በደህንነት ዙሪያ የተካሄዱ ስብሰባዎችን በማጠናከር ማጠናቀቅ እንደተቻለ በማንሳትም፤ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ያሉትን አከራካሪ ነገሮች በስምምነቱ የተቀመጡ ድንጋጌዎች ግልፅ በሆነ መንገድ አጥብቀው እንደሚያትቱት በኢፌዴሪ ሕግ መንግሥት በሚያዘው መልኩ የሚፈፀም መሆኑን ጠቁመዋል።

የፕሪቶሪያውም ሆነ የናይሮቢው ስምምነት ላይ ተጨባጭ ለውጥ የተመዘገበበት መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር ጌዲዮን፤ በናይሮቢ የኢትዮጵያ ከፍተኛ አመራሮች እና ወታደራዊ አዛዦች በሰላም ስምምነቱ አተገባበር ላይ ያተኮሩ ስብሰባዎች አካሂደው በስኬት መጠናቀቃቸውን አንስተዋል።

በተመሳሳይ በትግራይ ክልል በምትገኘው የሽሬ ከተማ በሁለቱም ወገን ባሉ ወታደራዊና የደህንነት አመራሮች መካከል ቀጥሎ የተካሄደው የሰላም ስምምነቱ አተገባበር ላይ ያተኮረ ስብሰባ በስኬት መጠናቀቁን በማስረዳት፤ በፕሪቶሪያ እና በናይሮቢ የተደረጉት ስምምነቶች በቅርቡም በሽሬ የተካሄዱ ውይይቶች በስኬት በመጠናቀቃቸው ለተጨማሪ ሥራ የሚያነሳሱና ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ወዳጆችና አጋር ሀገራት የሰላም ስምምነቱን በመደገፍ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ያስታወሱት የፍትሕ ሚኒስትሩ፤ በውይይቱ ሁለቱም ወገኖች እንዲገፉና ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ጉዳዩን ከእልባት ላይ ለማድረስ እንዲሁም እርቅ እና መረጋጋት እንዲመጣ የሀገራት ሚና አስተዋፅዖ እንደነበረው አንስተዋል።

የብልፅግና ፓርቲ በሰላም ስምምነቱ ላይ ያለው ቁርጠኝነት አስፈላጊ መሆኑን በማንሳትም በፓርቲው ይህን መሰል ቁርጠኝነት እና ግንዛቤ እስካለ ድረስ ምንም እንኳን እንቅፋቶች እና ተግዳሮቶች ሊኖሩ ቢችሉም በስኬት ማጠናቀቅ እንችላለን ሲሉ ገልፀዋል።

በተመሳሳይ የፖለቲካ ችግሮች ላይ እልባት ለመስጠት ሀገራዊ ምክክር አስፈላጊ መሆኑን ያነሱት ዶክተር ጌዲዮን፣ በአካታች ሁሉን አቀፍ ሀገራዊ ምክክር የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ድጋፍ አስፈላጊ በመሆኑ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። (አዲስ ዘመን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule