• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ

December 13, 2022 09:20 am by Editor Leave a Comment

በሰላም ንግግሩ በተደረሰው ስምምነት መሠረት ተዓማኒ የሆነና ግልጽነት ያለው የሽግግር ፍትሕ የሚፈፀም መሆኑን የፍትሕ ሚኒስቴር ገለጸ።

በሰላም ስምምነቱ በተደረሰው ስምምነት መሠረት ተዓማኒ የሆነና ግልጽነት ያለው የሽግግር ፍትሕ ከአፍሪካ ኅብረት የሽግግር ፍትሕ የፖሊሲ ማዕቀፍ ጋር በተጣጣመ መልኩ የሚፈፀም መሆኑን የፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶክተር) ገልፀዋል።

በተደረሰው ስምምነት መሠረት ግልፅ እና ተዓማኒ የሆነ የሽግግር ፍትሕ ለማስፈን እንደሚሠራ የገለፁት ሚኒስትሩ፤ ለዚህም ከያዝነው ወር ጀምሮ ሰፊ የሆኑ ሥራዎች ሁሉንም አካላት ባሳተፈ መልኩ እንደሚሠራ ነው የገለጹት።

ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሃሳባቸው በሚሰማበት እና ወደ ሽግግር ፍትሕ ለሚደረገው ሂደት የበኩላቸውን ተሳትፎ በሚያደርጉበት ሁኔታ በሚያረጋግጥ መልኩ ተዓማኒነት ያለውና ሁሉን አቀፍ ተጠያቂነት እንዲሰፍን ይሠራል ብለዋል።

በአጠቃላይ በደህንነት ዙሪያ የተካሄዱ ስብሰባዎችን በማጠናከር ማጠናቀቅ እንደተቻለ በማንሳትም፤ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ያሉትን አከራካሪ ነገሮች በስምምነቱ የተቀመጡ ድንጋጌዎች ግልፅ በሆነ መንገድ አጥብቀው እንደሚያትቱት በኢፌዴሪ ሕግ መንግሥት በሚያዘው መልኩ የሚፈፀም መሆኑን ጠቁመዋል።

የፕሪቶሪያውም ሆነ የናይሮቢው ስምምነት ላይ ተጨባጭ ለውጥ የተመዘገበበት መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር ጌዲዮን፤ በናይሮቢ የኢትዮጵያ ከፍተኛ አመራሮች እና ወታደራዊ አዛዦች በሰላም ስምምነቱ አተገባበር ላይ ያተኮሩ ስብሰባዎች አካሂደው በስኬት መጠናቀቃቸውን አንስተዋል።

በተመሳሳይ በትግራይ ክልል በምትገኘው የሽሬ ከተማ በሁለቱም ወገን ባሉ ወታደራዊና የደህንነት አመራሮች መካከል ቀጥሎ የተካሄደው የሰላም ስምምነቱ አተገባበር ላይ ያተኮረ ስብሰባ በስኬት መጠናቀቁን በማስረዳት፤ በፕሪቶሪያ እና በናይሮቢ የተደረጉት ስምምነቶች በቅርቡም በሽሬ የተካሄዱ ውይይቶች በስኬት በመጠናቀቃቸው ለተጨማሪ ሥራ የሚያነሳሱና ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ወዳጆችና አጋር ሀገራት የሰላም ስምምነቱን በመደገፍ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ያስታወሱት የፍትሕ ሚኒስትሩ፤ በውይይቱ ሁለቱም ወገኖች እንዲገፉና ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ጉዳዩን ከእልባት ላይ ለማድረስ እንዲሁም እርቅ እና መረጋጋት እንዲመጣ የሀገራት ሚና አስተዋፅዖ እንደነበረው አንስተዋል።

የብልፅግና ፓርቲ በሰላም ስምምነቱ ላይ ያለው ቁርጠኝነት አስፈላጊ መሆኑን በማንሳትም በፓርቲው ይህን መሰል ቁርጠኝነት እና ግንዛቤ እስካለ ድረስ ምንም እንኳን እንቅፋቶች እና ተግዳሮቶች ሊኖሩ ቢችሉም በስኬት ማጠናቀቅ እንችላለን ሲሉ ገልፀዋል።

በተመሳሳይ የፖለቲካ ችግሮች ላይ እልባት ለመስጠት ሀገራዊ ምክክር አስፈላጊ መሆኑን ያነሱት ዶክተር ጌዲዮን፣ በአካታች ሁሉን አቀፍ ሀገራዊ ምክክር የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ድጋፍ አስፈላጊ በመሆኑ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። (አዲስ ዘመን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule