• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ

December 13, 2022 09:20 am by Editor Leave a Comment

በሰላም ንግግሩ በተደረሰው ስምምነት መሠረት ተዓማኒ የሆነና ግልጽነት ያለው የሽግግር ፍትሕ የሚፈፀም መሆኑን የፍትሕ ሚኒስቴር ገለጸ።

በሰላም ስምምነቱ በተደረሰው ስምምነት መሠረት ተዓማኒ የሆነና ግልጽነት ያለው የሽግግር ፍትሕ ከአፍሪካ ኅብረት የሽግግር ፍትሕ የፖሊሲ ማዕቀፍ ጋር በተጣጣመ መልኩ የሚፈፀም መሆኑን የፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶክተር) ገልፀዋል።

በተደረሰው ስምምነት መሠረት ግልፅ እና ተዓማኒ የሆነ የሽግግር ፍትሕ ለማስፈን እንደሚሠራ የገለፁት ሚኒስትሩ፤ ለዚህም ከያዝነው ወር ጀምሮ ሰፊ የሆኑ ሥራዎች ሁሉንም አካላት ባሳተፈ መልኩ እንደሚሠራ ነው የገለጹት።

ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሃሳባቸው በሚሰማበት እና ወደ ሽግግር ፍትሕ ለሚደረገው ሂደት የበኩላቸውን ተሳትፎ በሚያደርጉበት ሁኔታ በሚያረጋግጥ መልኩ ተዓማኒነት ያለውና ሁሉን አቀፍ ተጠያቂነት እንዲሰፍን ይሠራል ብለዋል።

በአጠቃላይ በደህንነት ዙሪያ የተካሄዱ ስብሰባዎችን በማጠናከር ማጠናቀቅ እንደተቻለ በማንሳትም፤ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ያሉትን አከራካሪ ነገሮች በስምምነቱ የተቀመጡ ድንጋጌዎች ግልፅ በሆነ መንገድ አጥብቀው እንደሚያትቱት በኢፌዴሪ ሕግ መንግሥት በሚያዘው መልኩ የሚፈፀም መሆኑን ጠቁመዋል።

የፕሪቶሪያውም ሆነ የናይሮቢው ስምምነት ላይ ተጨባጭ ለውጥ የተመዘገበበት መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር ጌዲዮን፤ በናይሮቢ የኢትዮጵያ ከፍተኛ አመራሮች እና ወታደራዊ አዛዦች በሰላም ስምምነቱ አተገባበር ላይ ያተኮሩ ስብሰባዎች አካሂደው በስኬት መጠናቀቃቸውን አንስተዋል።

በተመሳሳይ በትግራይ ክልል በምትገኘው የሽሬ ከተማ በሁለቱም ወገን ባሉ ወታደራዊና የደህንነት አመራሮች መካከል ቀጥሎ የተካሄደው የሰላም ስምምነቱ አተገባበር ላይ ያተኮረ ስብሰባ በስኬት መጠናቀቁን በማስረዳት፤ በፕሪቶሪያ እና በናይሮቢ የተደረጉት ስምምነቶች በቅርቡም በሽሬ የተካሄዱ ውይይቶች በስኬት በመጠናቀቃቸው ለተጨማሪ ሥራ የሚያነሳሱና ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ወዳጆችና አጋር ሀገራት የሰላም ስምምነቱን በመደገፍ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ያስታወሱት የፍትሕ ሚኒስትሩ፤ በውይይቱ ሁለቱም ወገኖች እንዲገፉና ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ጉዳዩን ከእልባት ላይ ለማድረስ እንዲሁም እርቅ እና መረጋጋት እንዲመጣ የሀገራት ሚና አስተዋፅዖ እንደነበረው አንስተዋል።

የብልፅግና ፓርቲ በሰላም ስምምነቱ ላይ ያለው ቁርጠኝነት አስፈላጊ መሆኑን በማንሳትም በፓርቲው ይህን መሰል ቁርጠኝነት እና ግንዛቤ እስካለ ድረስ ምንም እንኳን እንቅፋቶች እና ተግዳሮቶች ሊኖሩ ቢችሉም በስኬት ማጠናቀቅ እንችላለን ሲሉ ገልፀዋል።

በተመሳሳይ የፖለቲካ ችግሮች ላይ እልባት ለመስጠት ሀገራዊ ምክክር አስፈላጊ መሆኑን ያነሱት ዶክተር ጌዲዮን፣ በአካታች ሁሉን አቀፍ ሀገራዊ ምክክር የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ድጋፍ አስፈላጊ በመሆኑ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። (አዲስ ዘመን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule