• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ

December 13, 2022 09:20 am by Editor Leave a Comment

በሰላም ንግግሩ በተደረሰው ስምምነት መሠረት ተዓማኒ የሆነና ግልጽነት ያለው የሽግግር ፍትሕ የሚፈፀም መሆኑን የፍትሕ ሚኒስቴር ገለጸ።

በሰላም ስምምነቱ በተደረሰው ስምምነት መሠረት ተዓማኒ የሆነና ግልጽነት ያለው የሽግግር ፍትሕ ከአፍሪካ ኅብረት የሽግግር ፍትሕ የፖሊሲ ማዕቀፍ ጋር በተጣጣመ መልኩ የሚፈፀም መሆኑን የፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶክተር) ገልፀዋል።

በተደረሰው ስምምነት መሠረት ግልፅ እና ተዓማኒ የሆነ የሽግግር ፍትሕ ለማስፈን እንደሚሠራ የገለፁት ሚኒስትሩ፤ ለዚህም ከያዝነው ወር ጀምሮ ሰፊ የሆኑ ሥራዎች ሁሉንም አካላት ባሳተፈ መልኩ እንደሚሠራ ነው የገለጹት።

ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሃሳባቸው በሚሰማበት እና ወደ ሽግግር ፍትሕ ለሚደረገው ሂደት የበኩላቸውን ተሳትፎ በሚያደርጉበት ሁኔታ በሚያረጋግጥ መልኩ ተዓማኒነት ያለውና ሁሉን አቀፍ ተጠያቂነት እንዲሰፍን ይሠራል ብለዋል።

በአጠቃላይ በደህንነት ዙሪያ የተካሄዱ ስብሰባዎችን በማጠናከር ማጠናቀቅ እንደተቻለ በማንሳትም፤ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ያሉትን አከራካሪ ነገሮች በስምምነቱ የተቀመጡ ድንጋጌዎች ግልፅ በሆነ መንገድ አጥብቀው እንደሚያትቱት በኢፌዴሪ ሕግ መንግሥት በሚያዘው መልኩ የሚፈፀም መሆኑን ጠቁመዋል።

የፕሪቶሪያውም ሆነ የናይሮቢው ስምምነት ላይ ተጨባጭ ለውጥ የተመዘገበበት መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር ጌዲዮን፤ በናይሮቢ የኢትዮጵያ ከፍተኛ አመራሮች እና ወታደራዊ አዛዦች በሰላም ስምምነቱ አተገባበር ላይ ያተኮሩ ስብሰባዎች አካሂደው በስኬት መጠናቀቃቸውን አንስተዋል።

በተመሳሳይ በትግራይ ክልል በምትገኘው የሽሬ ከተማ በሁለቱም ወገን ባሉ ወታደራዊና የደህንነት አመራሮች መካከል ቀጥሎ የተካሄደው የሰላም ስምምነቱ አተገባበር ላይ ያተኮረ ስብሰባ በስኬት መጠናቀቁን በማስረዳት፤ በፕሪቶሪያ እና በናይሮቢ የተደረጉት ስምምነቶች በቅርቡም በሽሬ የተካሄዱ ውይይቶች በስኬት በመጠናቀቃቸው ለተጨማሪ ሥራ የሚያነሳሱና ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ወዳጆችና አጋር ሀገራት የሰላም ስምምነቱን በመደገፍ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ያስታወሱት የፍትሕ ሚኒስትሩ፤ በውይይቱ ሁለቱም ወገኖች እንዲገፉና ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ጉዳዩን ከእልባት ላይ ለማድረስ እንዲሁም እርቅ እና መረጋጋት እንዲመጣ የሀገራት ሚና አስተዋፅዖ እንደነበረው አንስተዋል።

የብልፅግና ፓርቲ በሰላም ስምምነቱ ላይ ያለው ቁርጠኝነት አስፈላጊ መሆኑን በማንሳትም በፓርቲው ይህን መሰል ቁርጠኝነት እና ግንዛቤ እስካለ ድረስ ምንም እንኳን እንቅፋቶች እና ተግዳሮቶች ሊኖሩ ቢችሉም በስኬት ማጠናቀቅ እንችላለን ሲሉ ገልፀዋል።

በተመሳሳይ የፖለቲካ ችግሮች ላይ እልባት ለመስጠት ሀገራዊ ምክክር አስፈላጊ መሆኑን ያነሱት ዶክተር ጌዲዮን፣ በአካታች ሁሉን አቀፍ ሀገራዊ ምክክር የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ድጋፍ አስፈላጊ በመሆኑ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። (አዲስ ዘመን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule