• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አንተ ሌባ – አንቺ ሌባ” – የመቀሌው ሽኩቻና የህወሃት የውድቀት አፋፍ

November 16, 2017 11:30 pm by Editor Leave a Comment

መቀሌ ወሩን ሙሉ ውጥረት ውስጥ ከርማለች። ከተማዋ ላይ እየወረደ ያለው ዶፍ የሚያባራ አይመስልም። የህወሃቶቹ የዘንድሮ መሰባሰብ ለጤና እንዳልነበረ ግልጽ ነው። ሰዎቹ እንደወትሮው “በሃገር ጉዳይ ላይ” ለመዶለት ወደ መቀሌ አልተጓዙም። ቀደም ሲል ጠላታችን ድህነት ነው ሲሉን ነበር። አሁን ግን ለሁለት ተቧድነው አንዱ ሌላውን ጠላት ሲል ይሰማል።

በግል ጸብ ለሁለት መሰንጠቃቸው የአደባባይ ምስጢር ይሁን እንጂ፤ እርቅ እና ሰላም በአጀንዳቸው ውስጥ አልተካተተም። ሃገሪቱ የገባችበትን ችግር ወደጎን ትተው፣ “አንተ ሌባ – አንቺ ሌባ” ሲባባሉ እንደከረሙ ነው እየተሰማ ያለው። ይህንን የማይታረቅ ቅራኔ ይዘው አብረው ስለማይዘልቁ የአንዱ ቡድን ማሸነፍ ግድ ይላል።

በዚህ ‘ታሪካዊ’ ስብሰባ የሙስና እና የሌብነት ፋይሎች ተጠርዘው ቀርበዋል። ህወሃቶች አፍ አውጥተው “በስብሰናል”ም ብለዋል። እንደ አጀንዳ በቀረቡ በነዚህ የክስ ፋይሎች ላይ ድምጽ ተሰጥቶባቸዋል።

ስብሰባውን እየረገጡ የወጡት ወንጀል ሲዶለትባቸው የነበሩትና “ተሸናፊ” ህወሃቶች ናቸው። በሃብታቸው ብዛት “ቀዳማዊት እመቤት” የተባሉት አዜብ መስፍን የመጀመሪያው ስብሰባ ረጋጭ መሆናቸውን ሆርን አፌይርስ ከውስጥ ምንጭ ጠቅሶ ዘግቧል።

አዜብ ተከትለው ስብሰባውን እየረገጡ የወጡት የነ ስዬ አብርሃን ጽዋ ይቅመሱ አይቅመሱ ገና ባይታወቅም፣ ዛቻውና ጥርስ መናከሱ መቀጠሉን ግን የመቀሌ ምንጮች ገልጸዋል።

ወሩን ሙሉ መቀሌ ላይ ከትመው ሲጠዛጠዙ ውለው ሲጠዛጠዙ መሰንበታቸውን እነዚሁ ምንጮች ጠቁመዋል። ግምገማው ቀድሞ እንደሚያደርጉት አንዱ ባንዱ ላይ ጣት መሰባበቅን አልፎ፣ በተራ ስድብ እና ዘለፋ የታጀበ ነው። አጀንዳቸው ብሄራዊ ጉዳይ ቢሆን ባልከፋ ነበር። እጅግ የሚያሳፍረው ጸቡ እኔ እበልጥ፣ የግል መሆኑ ነው። ሌቦች የሚጋጩት ሲሰርቁ ሳይሆን ሲካፈሉ ነው ይባል የለ።

አቶ ሀብቶም ገ/እግዚያብሄር የህወሃቱ ድረገጽ በሆነው አይጋ ፎረም ላይ ኢህአዴግ ያለበት መንታ መንገድ እና የሀገራችን እጣ ፈንታ! በሚል የለቀቁት ያልተለመደ ጽሁፍ ከወዲያ እየነደደ ያለውን እሳት ይጠቁመናል። አይቴ ሃብቶም ስለዛሬው መግማማትና የሌቦች ፖለቲካን ክፉኛ ይኮንናሉ። ዛሬ ብቸኛው የመክበሪያ መንገድ ወይ የመንግስት ስልጣን መያዝ ወይ ከመንግስት ባለስልጣን መጠጋት እሳቤ መሆኑን እና ለዚህም ሙሉ ተጠያቂው ኢህአዴግ የሚመራው መንግስት ነው ይላሉ።

እርግጥ ነው። በህወሃት ውስጥ ሽኩቻ እና መጠላለፍ አዲስ አይደለም። የከዚህ ቀደሙን ተመክሮ እንዳየነውም፤ ስብሰባ ረግጦ መውጣት ለችግሮቹ መፍትሄ አልሆነም። ከ16 አመት በፊት እነ አቶ ገብሩ አስራት፣ አረጋሽ አዳነ፣ ስዬ አብርሃ፣ ፃድቃን ገ/ተንሳኤ የመለስን ሰነድ አንቀበልም ብለው ስብሰባ ረግጠው ነበር። እነ ስዬ በወቅቱ አብዛኛ ድምጽ ነበራቸው። ግና ማኬቬሊያዊው መለስ ቀደማቸውና እንደወጡ በዚያው ቀሩ።

አሁን መለስ የለም። ጸቡም የውስጥና የርስበርስ ብቻ አይደለም። ሽኩቻው ከሕዝብ ጋርም ነው። ከ90 ሚሊዮን ሕዝብ ጋር። የከረረው ክፍፍል ከህዝብ እንቢተኝነት ጋር ተደምማሮ ምን ሊፈጠር እንደሚችል ታምራት ገለታን መጠየቅ አያስፈልግም።

ፋይዳ ላይኖረው፣ እንዲሁ ሲቀያየሩ መሰንበታቸው “ስልቻ ቀልቀሎ…” ይሁን እንጂ፣ የኑሮው ውድነት፣ ከጣና ኬኛ ፖለቲካ እና የሼኩ ያልጠጠበቀ መታሰር፣… ተደማምሮ ለውጥ ፈልጎ ለተነሳው ኃይል በር መክፈቱ ግልጽ ነው። (ፎቶው ከHorn Affairs የተወሰደ ነው – አባይ ወልዱና ደብረጽዮን የመቀሌውን የህወሃት ስብሰባ ሲመሩ)

ክንፉ አሰፋ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule