• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የህወሓት ቁልፍ ሰዎች አሜሪካ ሄደው ጠ/ሚ/ር ዓቢይን ለማውረድ ያቀረቡት ጥያቄ ድራማ

June 28, 2018 10:35 pm by Editor 4 Comments

ነባርና ታዋቂ የህወሓት ቁልፍ ሰዎች አሜሪካ መታየታቸው በወፍ በረር ሲዘከር መሰንበቱ ይታወሳል። ከሶስት ሳምንት በፊት የህወሓት ሰዎች አሜሪካ ቤት ለመግዛትና ኑሯቸውን ለማደላደል እንደመጡ ተደርጎ ስም እየተጠቀሰ ሲነገርም ቆይቷል።

ተቀማጭነታቸው በአሜሪካ የሆነ የጎልጉል የዘወትር ታማኝ ዲፕሎማት መረጃ አቀባይ ግን ጉዳዩ ሌላ እንደሆነ ነው የሚናገሩት። እንደ ዲፕሎማቱ መረጃ የህወሓት ቁልፍ ሰዎች አሜሪካ ድረስ የመጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድን ከሥልጣን ለማውረድ በሌላ አነጋገር መፈንቅለ መንግሥት ለማድረግ የአሜሪካንን ይሁንታን ፍለጋ ነው።

ዶ/ር ዓቢይ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ከሆኑበት ዕለትም ሆነ ከዚያ በፊት በአገሪቱ እየተካሄደ ያለው የለውጥ ማዕበል ያልተመቻቸው የህወሓት ሰዎች ስሜታቸውን በተለያየ መልኩ ሲገልጹ ነበር። ሁሉም አልፎ ኢህአዴግ ካባ ውስጥ ባሉ የለውጥ ኃይሎች የተሸነፈው ህወሓት ሽንፈቱን ሳይወድ በግድ ለመቀበል ተገዷል።

አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር በሕዝብ፣ በአህጉርና በዓለም አቀፍ ደረጃ፣ በተለይም የአሜሪካን ይሁንታ ማግኘታቸው “በቆሮቆር ላይ …” እንዲሉ የህወሓት ቁልፍ ሰዎች ሊደብቁት በማይችሉት ደረጃ አሳመማቸው። በዚሁ የህመም ስሜት የተተነፈሰውን ሁሉ ከማኅበራዊ ሚዲያ ጭፍራዎቻቸው ጋር በመሆን በጅምላ የትግራይ ህዝብ ቀለበት ውስጥ እንደገባ አስመስለው ያቀርቡ ጀመር።

“የቀን ጅቦች” በሚል ለሌቦች ሁሉ የተሰጠውን በተለይ ለአንድ የህብረተሰብ ክፍል ነዋሪዎች ሁሉ እንደተሰጠ በማስመሰል ራሳቸውን ህዝብ ጉያ ሥር በመክተት “የትግራይን ህዝብ ከመሪ ድርጅታቸው ህወሓት ነጥለው ሊያጠቁ ተነስተዋል” የሚል መግለጫ ያወጣው ህወሓት ወደ አሜሪካ ያቀናው ከከበበው ፍርሃት በመንሳት መልሶ የፖለቲካ ስልጣኑንን ለመረከብ እንደሆነ ነው የተገለጸው።

በዚሁ መሠረት አሜሪካ ያቀኑት የህወሃት ቁልፍ የተባሉ ሰዎች “ዶ/ር ዓቢይን በሰላማዊ መንገድ እንድናስወግድ ፍቀዱልን” ሲሉ ነው ጥያቄ ያቀረቡት። የመረጃው ምንጭ እንዳሉት “አገሪቱና ቀጣናው አሁን በመበታተን አደጋ ውስጥ ናት” በማለት የህወሓት ሰዎች “የማረጋጋትና ሰላም የማስፈን ልምድና ክህሎት ስላለን ይህንን ሥጋት ማስወግድ እንድንችል ይሁንታ ስጡን” ሲሉ ነው የተማጸኑት።

አንድ የህወሓት የማህበራዊ ገጽ ጭፍራ አገር ባይጠቅስም ይህንኑ ሃሳብ ሲያራግብ እንደነበር፣ የትግራይ ህዝብ አደጋ ላይ መኖሩን ለዓለም ሁሉ በማሳወቅ ራስን የመከላከል ሥራ መስራት አስፈላጊ እንደሆነ በተደጋጋሚ ሲገልጽ የታዘቡና የህወሓት ክንፍ የድረገጽ ደብተራዎች “ማርም ሲበዛ ይመራል” ማለት ደረጃ መድረሳቸው የመፈንቅለ መንግሥት ጥያቄውን ለማጀብ የተወጠነ ስለመሆኑ አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ።

በዶ/ር ዓቢይ ሕይወት ላይ ምንም ሳይደርስ “በሰላማዊ መንገድ ጉዳዩ ይከናወናል” ያሉት የህወሓት ሰዎች፤ የመፈንቅለ መንግሥት ከተካሄደ በኋላ “የአሜሪካንን ጥቅም በሚያስጠብቅ መልኩ አዲስ አስተዳደር እናዋቅራለን፤ በቀጠናው የአሜሪካንን ፍላጎት ተግባራዊ እናደርጋለን” ሲሉም ከኩዴታው በኋላ የሚያከናውኑትን በዝርዝር አብራርተዋል።

ጥያቄው የቀረበላቸው የአሜሪካን ወሳኝ የፖሊሲ ሰዎች “አታስቡት” ሲሉ ከከባድ ማስጠንቀቂያ ጋር እንደመለሷቸው፣ አሁን የተጀመረውን የለውጥ ሂደት አጠናክረው እንደሚገፉበት፣ ሕዝብ በለውጡ መደሰቱንና ይህንን የሕዝብ ፍላጎት መከተል ግዴታቸው እንደሆነ አሳስበው በአጭር መልስ አሰናብተዋቸዋል።

መረጃ አቀባይ ዲፕሎማቱ እንዳሉት ከሆነ የህወሓት ሰዎች ዶ/ር አብይ አገሪቱን ወደ ከፋ ቀውስ እያመሯት እንደሆነና ህወሓት በዚህ አካሄድ አገሪቱ ልትበታተን ትችላለች የሚል ስጋት እንደገባው መስሎ ላቀረበው “መንግስት ልገልብጥ” ጥያቄ ከአሜሪካ በኩል የተሰጣቸው መልስ “አርፋችሁ ተቀመጡ” የሚል እንደነበር ይናገራሉ።

ይህ ዶ/ር ዓቢይን ከሥልጣን ለማስወገድ የቀረበ ሃሳብ ተቀባይነት ካጣ በኋላ የቅዳሜው ሰኔ 16 ዓቢይን የመግደል ሙከራ እንደ ሁለተኛ ዕቅድ ተግባራዊ ስለመደረጉ የተጠየቁት መረጃ አቀባያችን በጉዳዩ ላይ አስተያየት ከመስጠት ተቆጥበዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: abiy, anti reform, Full Width Top, Middle Column, reform, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Abera Ayana says

    July 1, 2018 04:59 am at 4:59 am

    The real reason for them to be seen in the USA is the first one the second reason is just to coverup the real fact. I can’t believe Goolgule missed mislead by false information.

    Reply
  2. www says

    July 1, 2018 12:38 pm at 12:38 pm

    የሠራተኛ ቅሬታ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

    የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
    እኛ ሰራተኞች የጠየቅናቸው structure ሳይሆን Grade ሳይሆን የደሞዝ ማሻሻያ ነው.
    አሁን የምንጠይቀው
    1.የሠራተኞች የጥቅም መብት ይከበር,

    የሠራተኛ ቅሬታ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

    በባንክ አለም ውስጥ መሪ ተዋናዮች የሚባሉት መንግስት፣ አሠሪ እና ሠራተኞች ናቸው፡፡
    . የሠራተኞች ፍላጎት
    ኢኮኖሚያዊ የደመዉዝ፣ የቦነስ እና አበል ወዘተጥቅሞቻቸዉ እንዲሻሻሉፍትሃዊ የደረጃ ዕድገት እና ለሎችማህበራዊ ጥቅሞቻቸዉ እንዲከበሩላቸዉ ይፈልጋሉየሙያ ደህንነት እና ጤንነት ፍትሓዊ የሥራ አመዳደብፍትሃዊ የዝዉዉር ሥርዓት እና ሌሎች
    ፍትሃዊ Market-based/campany scales ደሞዛቸው ሊከፈላቸው,ሊያድግላቸው,ይፈልጋሉ፡፡

    የሠራተኛ ቅሬታ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

    በአጠቃላይ ቅሬታ ማለት በአሠሪ እና ሠራተኞች መካከል የሚፈጠር/ የሚኖር ማንኛዉም የጥቅም ፡ የስራ ጫና፡የዝዉዉር፡የሀሳብ፣ የአመለካከትና የፍላጎት ልዩነቶች አለመጣጣም ምክንያት የሚፈጠረው አለመግባባትና ትግል ነዉ፡፡
    ዝርዝር ቅሬታዎች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ

    የአሠሪና ሠራተኛ ፍላጎቶች የሚያስተናግድ ሁሉን አስማሚ ቀ ሥርዓት አለመዘርጋት
    በባንኩ ዉስጥ ፍትሃዊ ተጠቃሚነት አለመኖር
    በአሰሪና ሰራተኛ መካከል ጤናማ የሆነ ግንኙነት አለመኖር፤
    ዲሞክራሲያዊ እና ግልፅነት የሌለበት PMS
    ዲሞክራሲያዊ ያልሆነ ጨቋኝና አፋኝ ሕጎች እና ስምምነቶች፡የባነኩን እና የአሠሪና ሠራተኛ ሕጎችን በፍታዊ መንገድ አለመቶርጎም፡፡
    ያለሰራተኛው ስምምነት ሠራተኛን ማዛወር እና ሠራተኛው የሚያቀርበውን የዝውውር ጥያቄ አለመቀበል እና አፋኝ በሆነ ሆግ መረጃ ከዛ ከዚ ካላመጣህ በማለት እንዲሁም የመሳሰሉት የእያንዳንዱን የባንኩን ሠራተኛ ጥቅም የጥቂቶች ቡድን መጠቀሚያ እና የዘመድ ማፍሪያ አድሮገዉታል፡፡
    ባንኩ ኢ-ሚዛናዊ የሆነ የትርፍ ማጋበስ ስነልቦናዊ ፍላጎት/ጉጉት ምክኒያት ሰራተኞችን መንከባከብ ቀርቶ መብቶቻቸውን መንፈግ ፡፡
    ሠራተኞች በሕግ የተሰጣቸዉ መብቶች እና ጥቅሞች ነገ ዛሬ ሲሉ ሳያገኙ አሁን ደርሰዋል ::
    አሰሪው ለህብረት ስምምነት ድርድርና አፈፃፀም እምቢተኛ ሆኑዋ::
    ተገቢ የሆነ የደመወዝ ጭማሪ ለሠራተኛው ነፍጓል፡፡
    የሠራተኛው ቤተሰብ የህክምና አገልግሎት ተነፍገዋል::
    ለሥራ የምያስፈልጉት የሥራ መሳሪያዎችን አለማሟላት::
    ባንኩ የስራ strategyውን እና policyውን ብቻ ማቀንቀን ::
    ድርጅቱን የሰራተኛውን የልብ ትርታ ቦታ ሳይሰጥ ቆይታል::
    ድርጅቱ የሰራተኛውን የእድገት ,የደረጃ ,የደሞዝ ጥያቄ ለማስተናገድ አለመፈለግ እና ማርፈድን መርጧል ፡፡
    አሰሪ እና ሰራተኛን የሚመለከቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያሉትን ሕጎች እና ስምምነቶች ወደ ሀገሩ ወስዶ አለማፅደቅ::
    ያፀደቃቸዉንም ሆነ ያወጣቸዉን ሕጎች ያለማክበር እና ያለማስከበር ድክመት::
    እንደተዋዋይ ወገኖች ፍላጎት መሰረት አለመግባባቶችን ወይም ቅሬታዎችን ለመፍታት የሚያገለግሉ ሥርዓቶች ማፈን እና ማቀጨጭ ወዘተ፡፡
    የጉልበት ብዝበዛ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሠራተኞች ላይ ይቁም ፍትህ ለአገራችን ፡፡
    በአጠቃላይም ዝቅተኛ ደሞዝ,ዝቅተኛ የአመት ረፍት, ዝቅተኛ የብድር አሰጣጥ —-

    የኢትዮጵያ ለውጥ ፈላጊ አባላት በሙሉ ይድረስ ሰላምታችን በያላችሁበት ፡፡
    በመቀጠልም ከላይ በዝርዝር የቀረብነውን ቅሬታዎች የሚመለከታቸውን የመንግስት አካላት እና የባንኩን አመራሮችና የቦርድ አባላትን አነጋግራችሁ መብትኤ እንድናገኝ አስፈላጊውን ጥረት እንድታደርጉልን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

    Reply
  3. Abera Ayana says

    July 1, 2018 07:45 pm at 7:45 pm

    I did speak my mind but you guys were cowards to approve it. Shame on you for pretending as a freedom fighters while abridging freedom of speech.

    Reply
  4. Ezira says

    July 2, 2018 01:41 pm at 1:41 pm

    ለባርነቱና ለአገልጋይነቱ ከእኛ ወዲያ ላሣር ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ ለአረቡም ሆነ ለቢጫው፤ ለነጩም ሆነ ለጥቁሩ ባሪያ ሆኖ ለማገልገል ከልጅነት ጀምሮ ዕድገታችንም ሆነ ተሞክሯችን በገሃድ የታዬና የሚታይ ታማኝ ባሪዎች ነን ለማለት ከረባት አስረው አሜሪካ ገቡ..? መጥኔ ለአሜሪካ ! ግን ፡ ግን ውሻም እኮ ታምኝነቱ ብቻ አይደለም የሚያስመርጠው። ታማኙ ውሻ ከታማኝነቱ በላይ ትልቁ መለጊያ ሚዛኑ ተልከሰካሽ (ልክስክስ)ነው ወይስ አይደለም የሚለው ምዘና ሚዛን ይደፋል። ባለ 2 እግር እንስሶች የትግሬው ወያኔ ግን ይሄን ግምት ውስጥ አይሰገቡም። ጥሩ ነው ከቀናቸው ! ውሻን አትልከስከስ ማለት ግ አይቻልም።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule