• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መቀሌ ተሸርቦ አዲስ አበባና ደብረዘይት ሊተገበር የነበረው ሽብር ከሸፈ

October 2, 2020 12:35 pm by Editor 2 Comments

የሽብር ጥቃት ለመፈጸም በህቡዕ ሲሰራ የቆየ ቡድን ከእነ ግብረአበሮቹ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አስታወቀ።

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለፋና ብሮድካስቲን ኮርፖሬት በላከው መግለጫ÷ በቢሾፍቱና በአዲስ አበባ ከተማ በድምቀት ከሚከበረው የኢሬቻ በዓል ጋር በተያያዘ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የሽብር ጥቃቶች ለመፈጸም፣ አመጽ ለማቀጣጠል፣ ግጭትና ትርምስ ለመፍጠር ከጥቂት የህወሓት የጥፋት ቡድኖች ጋር ግንኙነት በመፍጠር ተልዕኮ ተቀብሎ በህቡዕ ሲያስተባብርና ሲመራ የነበረ የኦነግ ሸኔ ቡድን ከእነ ግብረአበሮቹ በቁጥጥር ሥር እንዲውል ማድረጉን አስታውቋል።

አገልግሎት መስሪያ ቤቱ ለመገናኛ ብዙሃን ባሰራጨው መረጃ እንደገለጸው÷ ከኢሬቻ በዓል ጋር በተያያዘ በአዲስ አበባ፣ በቢሾፍቱና በሌሎቹም የአገሪቱ አካባቢዎች በጦር መሳሪያ የተደገፈ የሽብር ጥቃት፣ አመጽ፣ ግጭትና ትርምስ ለመፍጠር ተልዕኮ ለተሰጠው በህቡዕ የተደራጀ አንድ ታጣቂ ቡድን የሚውል 10 ክላሺንኮቭ የጦር መሳሪያ ከ 280 ጥይቶች ጋር ከመቀሌ ወደ ባቲ ሲጓዝ መስከረም 16 ቀን 2013 ዓ.ም ቀን በደቡብ ወሎ ዞን ሃይቅ ከተማ ከእነ ተሽከርካሪው በቁጥጥር ሥር ውሏል።

በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች ህዝባዊ አመጽ እንዲነሳ በማድረግ ይህን እንቅስቃሴ ለማሳካት ከተመለመሉት መካከል አንዱ የሆነው እንድሪስ እያሱ መሃመድ የተባለ የኦነግ ሸኔ አባል ከትግራይ ክልል የጸጥታ ቢሮ ኃላፊና ከሌሎች ጥቂት የህወሓት የጥፋት ቡድኖች ጋር በህቡዕ ተልዕኮውን ሲያቀናጁ እንደነበር የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ባደረገው ክትትል ማረጋገጡን አመልክቷል።

እነዚህ የጥፋት ቡድኖች በመጪው ቅዳሜና እሁድ በአዲስ አበባና የኦሮሚያ ክልሎች የሚከበሩትን የኢሬቻ በዓልን ተገን በማድረግ በኦሮሚያ ክልል አመፅ እንዲቀጣጠልና ወደ ሌሎች ክአካባቢዎች እንዲዛመት በጦር መሳሪያ ጭምር የታገዘ ትርምስ ለመፍጠር ከመቀሌ ወደ መሃል አገር የተለያዩ የጦር መሣሪያዎችን ሲልኩ እንደነበር ተጠቁሟል፡፡

ለዚህ እኩይ ተግባራቸውም ግለሰቦችን መልምለው ወደ መቀሌ በመውሰድ አሰልጥነው ወደተለያዩ አካባቢዎች ይልኩ እንደነበር የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አስታውቋል።

ለዚህ ተልዕኮው እንዲረዳቸው ካደራጇቸው የህቡዕ ቡድኖች መካካልም አንዱ እንድሪስ እያሱ መሃመድ በተባለ የኦነግ ሸኔ አባል የሚመራ ሲሆን÷ ላለፉት ወራት ከከሚሴ፣ መቀሌ አዲስ አበባ በመመላለስ የተሰጠውን ተልዕኮ ለማስፈጸም ሲንቀሳቀስ ቆይቷል፡፡

ቡድኑ መስከረም 16 ቀን 2013 ዓም በደቡብ ወሎ ዞን ሃይቅ ከተማ በቁጥጥር ሥር መዋሉን የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ገልጿል።

የጥፋት ቡድን መሪው መቀሌ ከሚገኘው የትግራይ ክልል የፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ከሆነው ተኪኡ ምትኩና ሌሎች ጥቂት የህወሓት የጥፋት ቡድኖች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት በመፍጠር ወደ መቀሌ በመመላለስ የጦር መሳሪያ፣ ገንዘብና ተልዕኮ በመቀበል ከሸኔ ታጣቂ ቡድን ጋር በማስተሳሰር በኦሮሚያ የአመጽ ቡድን ሲያደራጅ ቆይቷል።

ከዚህም በተጨማሪ እንድሪስ እያሱ መሃመድ እና ግብረአበሮቹ ከመቀሌ በተሰጣቸው ተልዕኮ መሠረት በባቲ የህቡዕ ቡድን አበላትን በማደራጀት በአካባቢው የብሄር ግጭቶችን የማስፋፋት እንዲሁም በሌሎችም ስፍራዎች ግጭት የመቀስቀስ ተልዕኮ ተቀብለው ሲያስፈጽሙ ቆይተዋል።

አማርኛ፤ ኦሮሞኛ፤ ሱማሊኛ፤ አፋርኛና አረብኛ በድምሩ አምስት ቋንቋዎችን የሚናገረው የሽብር ቡድኑ መሪና አስተባባሪ ተጠርጣሪው እንድሪስ እያሱ መሃመድና ግብረ አበሮቹን በህግ ቁጥጥር ስር ለማዋል በተደረገው እንቅስቃሴ ብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በጥብቅ ሙያዊ ዲስፕሊን የመከታተልና መረጃ የመስጠት ስራዎችን ሲሰራ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽንና የኢፌዴሪ መካላከያ ሰራዊት በጋራ መስራታቸውን መግለጫው አመልክቷል፡፡

መቀሌ ተሸርቦ ደቡብ ወሎ ዞን ሀይቅ ከተማ ላይ የከሸፈው የሽበር ጥቃት መሳሪያዎችን በከረዩና በባቲ በኩል ወደ ቢሾፍቱና አዲስ አበባ በማስገባት ከፍተኛ ሁከትና ግርግር በመፍጠር አገርን ለማተራመስ እቅድ እንደነበረው የጠቆመው መግለጫው÷ ሴራውን በማክሸፍ ህብረተሰቡ ከፍተኛ ተሳትፎ ማድረጉንም አገልግሎት መስሪያ ቤቱ መግለፅ ይወዳል፡፡

በቀጣይም በአገራችንና በህዝባችን ብሄራዊ ጥቅምና ደህንነት ላይ የሚቃጡ ማናቸውንም የሽብር ጥቃቶች አስቀድሞ በማወቅ አስፈላጊውን ሁሉ ለማድረግ ከምንጊዜውም በላይ ዝግጁ መሆኑን ብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እያረጋገጠ የህብረተሰቡ ትብብርና ድጋፍም እንዳይለየውም ጥሪ ማቅረቡን ፋና ብሮድካስቲንግ ዘግቧል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: NISS, terrorism, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. ዳን says

    October 4, 2020 03:32 am at 3:32 am

    ይገርማል።

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    October 22, 2020 11:52 am at 11:52 am

    ደብረ ዘይት? ደብረ ዘይት? ማን ኣወጣላት ይህን ስም?
    ሃይሌ ቀጭኑ? ነው? ነው እንጂ! ላይጣጣም
    ከቋንቋችን ከምስላችን፥ ካምልኮኣችን ላይሳሳም
    ላይሰልጥ፥ ላይሆን ድርጭት ፍለጋ፥ እንደላም
    ግብራችን፥ ትንፋሻችን ላይጥም ትምክህትም
    ድርቅ እንደመታው ማሽላ ፍግምግም
    ብሎም ጠውልጎ እሸት ላይኖረው ምርትም
    ደብረዘይት ኣልከኝ? እልህ ኣንገባም!!
    የበላኸውን ኣጣጥም!!
    የሃይሌ ቀጭኑ ስም!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule