• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መቀሌ ተሸርቦ አዲስ አበባና ደብረዘይት ሊተገበር የነበረው ሽብር ከሸፈ

October 2, 2020 12:35 pm by Editor 2 Comments

የሽብር ጥቃት ለመፈጸም በህቡዕ ሲሰራ የቆየ ቡድን ከእነ ግብረአበሮቹ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አስታወቀ።

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለፋና ብሮድካስቲን ኮርፖሬት በላከው መግለጫ÷ በቢሾፍቱና በአዲስ አበባ ከተማ በድምቀት ከሚከበረው የኢሬቻ በዓል ጋር በተያያዘ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የሽብር ጥቃቶች ለመፈጸም፣ አመጽ ለማቀጣጠል፣ ግጭትና ትርምስ ለመፍጠር ከጥቂት የህወሓት የጥፋት ቡድኖች ጋር ግንኙነት በመፍጠር ተልዕኮ ተቀብሎ በህቡዕ ሲያስተባብርና ሲመራ የነበረ የኦነግ ሸኔ ቡድን ከእነ ግብረአበሮቹ በቁጥጥር ሥር እንዲውል ማድረጉን አስታውቋል።

አገልግሎት መስሪያ ቤቱ ለመገናኛ ብዙሃን ባሰራጨው መረጃ እንደገለጸው÷ ከኢሬቻ በዓል ጋር በተያያዘ በአዲስ አበባ፣ በቢሾፍቱና በሌሎቹም የአገሪቱ አካባቢዎች በጦር መሳሪያ የተደገፈ የሽብር ጥቃት፣ አመጽ፣ ግጭትና ትርምስ ለመፍጠር ተልዕኮ ለተሰጠው በህቡዕ የተደራጀ አንድ ታጣቂ ቡድን የሚውል 10 ክላሺንኮቭ የጦር መሳሪያ ከ 280 ጥይቶች ጋር ከመቀሌ ወደ ባቲ ሲጓዝ መስከረም 16 ቀን 2013 ዓ.ም ቀን በደቡብ ወሎ ዞን ሃይቅ ከተማ ከእነ ተሽከርካሪው በቁጥጥር ሥር ውሏል።

በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች ህዝባዊ አመጽ እንዲነሳ በማድረግ ይህን እንቅስቃሴ ለማሳካት ከተመለመሉት መካከል አንዱ የሆነው እንድሪስ እያሱ መሃመድ የተባለ የኦነግ ሸኔ አባል ከትግራይ ክልል የጸጥታ ቢሮ ኃላፊና ከሌሎች ጥቂት የህወሓት የጥፋት ቡድኖች ጋር በህቡዕ ተልዕኮውን ሲያቀናጁ እንደነበር የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ባደረገው ክትትል ማረጋገጡን አመልክቷል።

እነዚህ የጥፋት ቡድኖች በመጪው ቅዳሜና እሁድ በአዲስ አበባና የኦሮሚያ ክልሎች የሚከበሩትን የኢሬቻ በዓልን ተገን በማድረግ በኦሮሚያ ክልል አመፅ እንዲቀጣጠልና ወደ ሌሎች ክአካባቢዎች እንዲዛመት በጦር መሳሪያ ጭምር የታገዘ ትርምስ ለመፍጠር ከመቀሌ ወደ መሃል አገር የተለያዩ የጦር መሣሪያዎችን ሲልኩ እንደነበር ተጠቁሟል፡፡

ለዚህ እኩይ ተግባራቸውም ግለሰቦችን መልምለው ወደ መቀሌ በመውሰድ አሰልጥነው ወደተለያዩ አካባቢዎች ይልኩ እንደነበር የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አስታውቋል።

ለዚህ ተልዕኮው እንዲረዳቸው ካደራጇቸው የህቡዕ ቡድኖች መካካልም አንዱ እንድሪስ እያሱ መሃመድ በተባለ የኦነግ ሸኔ አባል የሚመራ ሲሆን÷ ላለፉት ወራት ከከሚሴ፣ መቀሌ አዲስ አበባ በመመላለስ የተሰጠውን ተልዕኮ ለማስፈጸም ሲንቀሳቀስ ቆይቷል፡፡

ቡድኑ መስከረም 16 ቀን 2013 ዓም በደቡብ ወሎ ዞን ሃይቅ ከተማ በቁጥጥር ሥር መዋሉን የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ገልጿል።

የጥፋት ቡድን መሪው መቀሌ ከሚገኘው የትግራይ ክልል የፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ከሆነው ተኪኡ ምትኩና ሌሎች ጥቂት የህወሓት የጥፋት ቡድኖች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት በመፍጠር ወደ መቀሌ በመመላለስ የጦር መሳሪያ፣ ገንዘብና ተልዕኮ በመቀበል ከሸኔ ታጣቂ ቡድን ጋር በማስተሳሰር በኦሮሚያ የአመጽ ቡድን ሲያደራጅ ቆይቷል።

ከዚህም በተጨማሪ እንድሪስ እያሱ መሃመድ እና ግብረአበሮቹ ከመቀሌ በተሰጣቸው ተልዕኮ መሠረት በባቲ የህቡዕ ቡድን አበላትን በማደራጀት በአካባቢው የብሄር ግጭቶችን የማስፋፋት እንዲሁም በሌሎችም ስፍራዎች ግጭት የመቀስቀስ ተልዕኮ ተቀብለው ሲያስፈጽሙ ቆይተዋል።

አማርኛ፤ ኦሮሞኛ፤ ሱማሊኛ፤ አፋርኛና አረብኛ በድምሩ አምስት ቋንቋዎችን የሚናገረው የሽብር ቡድኑ መሪና አስተባባሪ ተጠርጣሪው እንድሪስ እያሱ መሃመድና ግብረ አበሮቹን በህግ ቁጥጥር ስር ለማዋል በተደረገው እንቅስቃሴ ብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በጥብቅ ሙያዊ ዲስፕሊን የመከታተልና መረጃ የመስጠት ስራዎችን ሲሰራ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽንና የኢፌዴሪ መካላከያ ሰራዊት በጋራ መስራታቸውን መግለጫው አመልክቷል፡፡

መቀሌ ተሸርቦ ደቡብ ወሎ ዞን ሀይቅ ከተማ ላይ የከሸፈው የሽበር ጥቃት መሳሪያዎችን በከረዩና በባቲ በኩል ወደ ቢሾፍቱና አዲስ አበባ በማስገባት ከፍተኛ ሁከትና ግርግር በመፍጠር አገርን ለማተራመስ እቅድ እንደነበረው የጠቆመው መግለጫው÷ ሴራውን በማክሸፍ ህብረተሰቡ ከፍተኛ ተሳትፎ ማድረጉንም አገልግሎት መስሪያ ቤቱ መግለፅ ይወዳል፡፡

በቀጣይም በአገራችንና በህዝባችን ብሄራዊ ጥቅምና ደህንነት ላይ የሚቃጡ ማናቸውንም የሽብር ጥቃቶች አስቀድሞ በማወቅ አስፈላጊውን ሁሉ ለማድረግ ከምንጊዜውም በላይ ዝግጁ መሆኑን ብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እያረጋገጠ የህብረተሰቡ ትብብርና ድጋፍም እንዳይለየውም ጥሪ ማቅረቡን ፋና ብሮድካስቲንግ ዘግቧል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: NISS, terrorism, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. ዳን says

    October 4, 2020 03:32 am at 3:32 am

    ይገርማል።

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    October 22, 2020 11:52 am at 11:52 am

    ደብረ ዘይት? ደብረ ዘይት? ማን ኣወጣላት ይህን ስም?
    ሃይሌ ቀጭኑ? ነው? ነው እንጂ! ላይጣጣም
    ከቋንቋችን ከምስላችን፥ ካምልኮኣችን ላይሳሳም
    ላይሰልጥ፥ ላይሆን ድርጭት ፍለጋ፥ እንደላም
    ግብራችን፥ ትንፋሻችን ላይጥም ትምክህትም
    ድርቅ እንደመታው ማሽላ ፍግምግም
    ብሎም ጠውልጎ እሸት ላይኖረው ምርትም
    ደብረዘይት ኣልከኝ? እልህ ኣንገባም!!
    የበላኸውን ኣጣጥም!!
    የሃይሌ ቀጭኑ ስም!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule