• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል

December 8, 2020 01:05 am by Editor 1 Comment

ወንጀለኛው የህወሓት ጁንታ የንግድ ድርጅቶች በህገወጥ የንግድ እንቅስቃሴ የአገሪቱን ኢኮኖሚ ክፉኛ መጉዳታቸውን ምጣኔ ሀብት ባለሙያው አቶ አዲሱ እጥፉ አስታወቁ። የሀገሪቱን ሀብት ከመበዝበር ወደ ውጭ ለማሸሽ መሳሪያ እንደነበሩም ጠቆሙ።

አቶ አዲሱ እጥፉ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገ ለጹት፦ የህወሓት ጁንታው የንግድ ድርጅቶች በሀገ ሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ያሳደሩት አሉታዊ ተፅዕኖ እጅግ የከበደ ነው።ተቋማቱ የአገሪቱን ኢኮኖሚ በበላይነት በመቆጣጠርና በህገወጥ መንገድ በመዝረፍ የአገሪቱን ሀብት ወደውጭ ሲያሸሹ ነበር።

የንግድ ተቋማት አሰራራቸው ብቻ ሳይሆን አጀማ መራቸውም ህገ ወጥ እንደነበሩ የገለፁት የምጣኔ ሀብት ባለሙያው፣ ተቋማቱ ላለፉት በርካታ ዓመታት በማናለብኝነት ሀገሪቱን ሲመዘብሩ መቆየታቸውና የአገሪቱን ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደራቸውን አስታውቀዋል።

ጁንታው የፖለቲካ የበላይነት ለመያዝ የኢኮኖሚ የበላይነት ማረጋገጥ አለብኝ ብሎ የሚያምን ድርጅት መሆኑን የተናገሩት ባለሙያው፣ በህገወጥ ተቋማቱ አማካኝነት ይህንን እምነቱን ተጨባጭ ለማድረግ የሄደበት መንገድ በአገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን አመልክተዋል።

ተቋማቱ በተጠና መልክ የተሳሰሩና በሰንሰለት መልክ የተደራጁ ሁሉም ለአንድ አላማ የተቋቋሙ እንደሆኑ የሚናገሩት ባለሙያው፣ አንዱ ተቋም የአንደኛው ግብዓት አቅራቢ በመሆን ለሌላው በመሸጥና ኢኮኖሚውን በተለያየ መልኩ በመቆጣጠር የበላይነቱን ተቆጣጥረውት ቆይተዋል ብለዋል።

የህወሓት ጁንታ በነበረው የፖለቲካ የበላይነት ተጠቅሞ የአገሪቱ የወጪና የገቢ ንግድ ሆን ተብሎ ከእነዚህ ድርጅቶች ጋር የተያያዙ እንዲሆኑ ማድረጉን ያመለከቱት ባለሙያው፣ ተቋማቱ ያለገደብ የባንክ ብድ ርና የውጭ ምንዛሪ ያገኙ እንደነበር ገልፀው” ይህ ደግሞ ከሌላ ህጋዊ ድርጅቶች በተለየ መልኩ ኢኮኖሚውን እንዲቆጣጠሩ እድል እንዲሰጣቸው አስታውቀዋል።

የድርጅቱ ባለስልጣን የሆኑት አቶ ስብሀት ነጋ በ2003 ዓ.ም ለአሜሪካ ድምፅ “የህወሓት ተቋም የሆነው ኤፈርት የአገሪቱ ቁጥር አንድ ሀብታም ድርጅት ነው” ማለታቸውን በማሳያነት ጠቅሰዋል።

ተቋማቱ ከልማት ባንክና ከንግድ ባንኮች በብድር መልክ የወሰዷቸው ገንዘቦች እንደማይመልሱና የተበላሸ ብድር እየተባለ እንደሚመክን ያስረዱት አቶ አዲሱ፣ እነዚህ ተቋማት አትራፊ መሆናቸውና እጅግ ትልልቅ ገንዘቦች ማዘዋወራቸው እየታወቀ ተቋማቱ ኪሳራ ላይ ናቸው በሚል የተበደሩትን ገንዘብ ሳይመልሱ እንዲቀሩና የመንግሥት ገንዘብ እንዲመዘበር ሆን ተብሎ ሲሰራ መቆየቱን አስታውቀዋል።

በህጉ መሰረት አንድ ተቋም መክሰሩ ታውቆ የተበደረው ብድር መመለስ እንደማይችል ሲረጋገጥ ብድሩ ተበላሸ እንደሚሰኝ ገልፀው ፣የህወሓት ጁንታው ተቋማት ግን አትራፊ መሆናቸው እየታወቀ የተበደሩትን ገንዘብ እንዳይመልሱ የተለያዩ ምክንያቶች ያቀርቡ እንደነበር ጠቁመዋል።

ጤነኛ የንግድ ህግ ተከትለው ይሰሩ የነበሩ ተቋማት በቡድኑ ህገወጥ ድርጅቶች በደረሰባቸው ጫና ከገበያ እንደወጡና በአንፃሩ ደግሞ በቡድኑ የሚተዳደሩ ተቋ ማት በአገሪቱ ግዙፍ የገንዘብ ዝውውር የሚያደርጉና በህገወጥ መንገድ የከበሩ እንደነበሩ አስታውቀዋል። ተቋማቱ ከአገሪቱ በተለያየ መንገድ የዘረፉት ገንዘብ ወደውጭ በማሸሽ ሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ እጥረት እንዲገጥማትና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዋ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንዲፈጠር ምክንያት እንደነበሩ ገልጸዋል።

ከአመሰራረታቸው ጀምሮ ህገወጥ በሆነ መልኩ የተቋቋሙት የህወሓት ጁንታው የንግድ ተቋማት በአገሪቱ ላይ የፈጠሩት ኢኮኖሚያዊ ጫና ከፍተኛ መሆኑንም ገልፀዋል። ማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት የንግድ ሥራ ውስጥ መሳተፍ የለበትም ያሉት አቶ አዲሱ ተቋማቱ በ1952 ዓ.ም የወጣውን አገራዊ ህግ በሚፃረር መልኩ የተቋቋሙና በህገወጥ መልኩ ሲሰሩ የቆዩ ናቸው ብለዋል።

በመንግሥት ቁጥራቸው 34 የሚሆኑ የንግድ ተቋማት ተለይተው የተገለፁ መሆኑንና ጉዳያቸው በህግ ሂደት ላይ ቢሆንም የድርጅቱ የንግድ ተቋማት ግን ቁጥራቸው ከዚያ እጅግ እንደሚበልጥና በመንግሥት በኩል በትክክል ተለይተው ከህገወጥ ተግባራቸው ሊገቱ እንደሚገባም አመልክተዋል ።ተቋማቱ ለመንግሥት ግብር በስርዓት የማይከፍሉና በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች መሬቶችን በመውሰድ እና መልሶ በመሸጥ ለህገወጥ ተግባራቸው መጠቀሚያ ያደርጉ እንደነበር ጠቁመዋል።

ዓለምአቀፉ የፋይናንስ ሀቀኝነት ድርጅት በፈረንጆች በ2010 ይፋ ባደረገው ሪፖርት መሰረት የጁንታው ድርጅቶች ከአገሪቱ ከ17 ቢሊዮን ብር በላይ በማሸሽ በውጭ ሀገር በሚገኙ የተለያዩ ባንኮች ላይ አስቀምጠዋል። ይህ ቁጥር ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ መምጣቱንና እስካሁን ይፋ የተደረገ ሪፖርት ብቻ መሰረት በማድረግ ከአገሪቱ በተለያየ መንገድ የዘረፉት ከ36 ቢሊዮን ዶላር ወይም ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ በተለያዩ አገራት ባንኮች ላይ ማስቀመጣቸውን አስታውቀዋል።

ተቋማቱ የአገሪቱ ገንዘብ ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ባህላዊና ታሪካዊ ቅርሶችን በመሸጥና ወደውጭ በማሸሽ ታሪክ ይቅር የማይለው ወንጀል ሲፈጽሙ መቆየታቸውንም የገለጹት አቶ አዲሱ፣ ተቋማቱ ገለልተኛ በሆነ መልኩ ተጣርተው አገሪቱ ላይ ያደረሱትን ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖ በመመርመር ተጠያቂ ሊደረጉ እንደሚገባ አመልክተዋል። (ተገኝ ብሩ፣ ኢፕድ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Left Column, News Tagged With: effort, getachew assefa, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Comments

  1. አለም says

    December 18, 2020 01:47 pm at 1:47 pm

    ውድ ጎልጒል፣
    የዶ/ር ዐቢይ መንግሥት በህወኃት ላይ የያዛቸውን የዝርፊያ፣ የግድያና የቶርች መረጃዎችን በተለይ ለውጭ እርዳታ ሰጭዎች አጠናቅሮ ማሠራጨት አለበት! ይህን የሚያዘጋጅ ኮሚቴ አቋቊሞ (እነ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋም ቢሳተፉበት) ትልቅ ሥራ ነው። ህወኃት ኃፍረት የማያውቀው ነውና ታሪኮቹን ዘቅዝቆ ዶ/ር ዐቢይን ዲክታተር ሲላቸው እየሰማን ነው፤ ባዘጋጀው ኔትወርክ እየተበተበ ነው። ኢትዮጵያውያን ስለ ህወኃት የማያውቁት ብዙ የለም፤ መረጃ የሚያስፈልገው ለውጭው ኮምዩኒቲ ነው!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule