• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የስደተኛ መታወቂያ የያዙ የትህነግ ተዋጊዎች ተይዘዋል፤ ተመድ እያጣራ ነው ብሏል

September 5, 2021 03:22 pm by Editor Leave a Comment

“የስደተኞች መታወቂያን ይዘው ተገኝተዋል” የተባሉ ታጣቂዎችን ጉዳይ እያጣራ እንደሆነ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ከፍተኛ የስደተኞች ጉዳይ ኤጀንሲ ገለጸ።

ኤጀንሲው “በሱዳን የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ የነበሩና የተመድ ስደተኞች ኤጀንሲ መታወቂያ የያዙ ታጣቂዎች ተገኙ” የሚሉ መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘዋወሩና በተለያዩ የሚድያ አውታሮች ሲዘገቡ መመልከቱን ስለ ጉዳዩ ለጠየቀው አል ዐይን አማርኛ በላከው የኢ-ሜይል መልዕክት አስታውቋል።

የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ አገኘሁ ተሻገር ሰሞኑን በሱዳን አቅጣጫ መጥተው “ሽንፋ የተባለ ቦታን ለመያዝ የተንቀሳቀሱ የቅማንትና ህወሃት ታጣቂዎች መደምሰሳቸው”ን የሚያሳውቅ ጽሁፍ በትዊተር ገጻቸው ማጋራታቸው የሚታወስ ነው።

ዓለም አቀፍ ብዙሃን መገናኛዎች ‘ህወሓት ሰብዓዊ እርዳታን እየዘረፈ ነው’ መባሉን “ከዓለም አቀፍ ተቋማት ሲሰሙ ብቻ መዘገባቸው ለምን ተብሎ መጠየቅ አለበት” ሲል ከትናንት በስቲያ አርብ ያስታወቀው የፌዴራል መንግስትም እየተገኙ ያሉት መታወቂያን መሰል ማስረጃዎች ስደተኛ መስለው ወደ ሱዳን መጠለያ ጣቢያዎች የገቡት የማይካድራ ጭፍጨፋ ፈጻሚ የሳምሪ ቡድን አባላት ተመልሰው ሳይመጡ እንዳልቀረ አመላካች ነው ሲል መግለጹ ይታወሳል።

ይህን ተከተሎም የተባበሩት መንግስታት ከፍተኛ የስደተኞች ጉዳይ ኤጀንሲ /ዩ.ኤን.ኤች.ሲ.አር/ የኢትዮጵያ ማስተባበሪያ ቢሮ ምላሽ ሰጥቷል።

ምላሹን የሰጡት የቢሮው ቃል አቀባይ ኔቨን ክሬቨንኮቪች ታጣቂዎቹ ይዘውት ተገኘ ከተባለው “የተመድ የስደተኛ መታወቂያ”ጋር በተያያዘ የወጣውን መረጃ ኤጀንሲው እያጣራ መሆኑን ለአል-ዐይን በላኩት የኢ-ሜይል መልዕክት ገልጸዋል።

ቃል አቀባዩ፤ ሰሞኑን “በሱዳን የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ የነበሩና የተመድ ስደተኞች ኤጀንሲ መታወቂያ የያዙ ታጣቂዎች ተመልሰው በግጭቱ ሲሳተፉ ተገኙ” የሚሉ መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘዋወሩና በተለያዩ የሚድያ አውታሮች ሲዘገቡ ተመልክተናል ብለዋል።

ተቋማቸው ጉዳዩን እያጣራ እንደሆነም ነው የገለጹት።

ስደተኞቹን የተመለከቱ አዳዲስ መረጃዎች ሲገኙ፣ ከመጠለያ ጣቢያዎች ሲወጡም ሆነ መታወቂያ ካርዳቸው ሲጠፋ የመረጃ ቋታችን የምናዘምንበት በመደበኛ የአሰራር ስርዓት አለን ብለዋል ስደተኞቹ ወደ ሃገራቸው ለመመለስ ሲወስኑ ስደተኛነታቸውን እንደሚያጡ በመጠቆም።

ኤጀንሲው “በቅርቡወደ ኢትዮጵያ በስደተኞች የተደረገ እንቅስቃሴ” አለመመልከቱንም ገልጸዋል ቃል አቀባዩ።

“በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ ሆነን የስደት ተመላሾችን የምናረጋግጥበት ሁኔታም የለም”ም ብለዋል ኔቨን ክሬቨንኮቪች።

ኤጀንሲው “የስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች የሲቪል ባህርይን ጠብቀው እንዲቆዩ እና ይህንን ለማረጋገጥ የሚያስችል ድጋፍ ለሱዳን መንግስት ለማድረግ ያለውን ቁርጠኝነት” ደጋግሞ መግለጹንም ተናግረዋል።

የተመድ ከፍተኛ የስደተኞች ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍሊፖ ግራንዴ በቅርቡ ወደ ሱዳን አቅንተው መጠለያ ጣቢያዎቹን ጎብኝተው ነበር።

ግራንዴ በዚሁ ጉብኝታቸው ይህንኑ መግለጻቸውንም ነው ያስታወቁት።

ክሬቨንኮቪች “በስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ ወታደራዊ ሥልጠናዎች ይሰጣሉ” የሚለው “መሠረተ ቢስ” ነውም ብለዋል።

ያልተረጋገጡ የግል መረጃዎችን የስደተኞች ናቸው በሚል በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ማጋራቱ እንዲቆምም አሳስበዋል።

ይህ በግለሰቦቹ፣ በቤተሰባቸውና በሱዳን በሚገኙ ስደተኞች ላይ ለበቀል እንደሚያነሳሳም ነው ቃል አቀባዩ የገለጹት። (አል-አይን)

ከዚሁ ጋር በተዛመደ የማኅበረሰብ አንቂ የሆነው ጌታቸው ሽፈራው መረጃው እንደተገኘ ይህንን መልዕክት በፌስቡኩ ለጥፎ ነበር፤

የኢትዮጵያ መንግሥት ሆይ!

ይሄውልህ የዓለም አቀፉን ማሕበረሰብ ቅሌት ማሳየት የምትችልበት መረጃ!

ከስር የተያያዘው መረጃ ሱዳንና UNCHCR  በዓለም አቀፍ ሕግ የሚያስጠይቅ ነው። ሀጎስ ሃይላይ በርሀ የተባለ ግለሰብ ሱዳን ውስጥ የUNHCR የስደተኛ የምዝገባ መታወቂያን ተቀብሏል። ስደተኛ ካምፕ ውስጥ ቀለብና መጠለያ እያገኘ ወጣ ብሎ ደግሞ እየሰለጠነ ከርሞ ኢትዮጵያን  ለመውጋት የመጣው ኃይል ዛሬ በቋራ መስመር ሲመታ መረጃዎቹ ተይዘዋል። ሀጎስ ምሳሌ ነው። እነ ጌታቸው ረዳ ሱዳን ውስጥ 30 ሺህ ጦር አለን ያሉት በሙሉ ስደተኛውን አሰልጥነው ነው።

በ1951 የጀኔቫ የስደተኞች ስምምነት መሰረት ስደተኛውን የተቀበለው ሀገርም ሆነ፣ ስደተኛውን የያዘው ተቋም ጥብቅ ግዴታዎች አሉባቸው። ሱዳን ስደተኛውን እንዳስጠለለች ሀገር የተቀበለችው ስደተኛ ጦርነት የሚያህል ተመድ በመርሁ የሚቃወመው ነገር እንዳይገባ የማድረግ ግዴታ አለባት። የሆነው ግን ስደተኞች ጣቢያ አካባቢ ማሰልጠኛ ተከፍቶ ስደተኛው አንዴ መጠለያ፣ ሌላ ጊዜ ማሰልጠኛ ጣቢያ እየተመላለሰ ኢትዮጵያን እንዲወጋ ተደርጓል። ያውም የሱዳንና የግብፅ መንግስት የመሳርያና ሌሎች እገዛዎችን አድርገውለት። የኢትዮጵያ መንግስት ይሄን መረጃ በማጠናከር  ለተመድና ለአባላቱ፣ ለኢትዮጵያ ወዳጅና ጠላቶች ማቅረብ አለበት።

ሱዳን ስደተኛ አስጠልላለሁ ብላ ከግብፅ ጋር ሆና አሰልጥና እየላከች መሆኑን ማሳወቅ አለበት። በተመድ ስር ያለው UNHCR በስሩ ያሉ ስደተኞችን ለጦርነት ተመልምለው፣ ሰልጥነው ሀገር ሲወጉ ዝም ብሎ እያየ እንደሆነ ለዓለም ማሳወቅ አለበት። የውጭ ጉዳይ በመግለጫው በደንብ ማካተት አለበት፣ ለኤምባሲዎች መረጃውን አጠናቅሮ ማድረስ አለበት። አምባሳደሮች ለያሉበት ሀገር መንግስትና ሚዲያ፣ በተመድ የኢትዮጵያ ተወካይ ደግሞ ለሚገባቸው አካላት ማድረስ አለበት። በዓለም አቀፍ ሕግ የሚኬድባቸው አካሄዶች በሙሉ ሊናቁ አይገባም።

ይህን ሁሉ የሚያደርገው በዓለም አቀፍ መድረክ ፍትሕ ስለሚገኝበት አይደለም። ነገር ግን አስር ጊዜ በኢትዮጵያ ጉዳይ ስብሰባ የሚጠራው ተደመድ ራሱ መጠለያ የሰጣቸው ስደተኞች ወታደር ሆነው ሀገር እየወጉ  መሆኑን ማሳወቅ ይገባል። ስደተኛ ካምፕ ውስጥ ሆነው ሱዳንና UNHCR እያንዳንዷን እንቅስቃሴ ሊቆጣጠሯቸው የሚገባቸው ስደተኞች ከባድ መሳርያ፣ የቡድንና የግል መሳርያ ይዘው ሀገር ሲወጉ፣ ንፁሃንን ሲጨፈጭፉ፣ ሲዘርፉ፣ ሲደፍሩ ነው የተደረሰባቸው።

እነ ሳማንታ ፓወር ሄደው በጎበኙት የሱዳን ካምፕ ያለው ስደተኛ ወታደር ሆኖ እየወጋን እንደሆነ ማሳወቅ ይገባል። በተመድ ስብሰባ አስር ጊዜ ስለስደተኛ አያያዝ እያነሱ የሚያወግዙን ልካቸውን ማወቅ አለባቸው። ቢያንስ ይሄ መረጃ ሌላ ጊዜ  ትህነግን ለመደገፍ ብለው፣ መርህን አጣመው አፍ  እንዳይከፍቱ መያዥያ ይሆናል።  ሄደው ሲጎበኙ ስደተኛው ሁሉ እየሰለጠነ እንደሆነ መረጃ አጥተው አይደለም። ስለሆነም የዓለም አቀፍ ተቋማት ነውርን ማሳወቅ የሚያስችሉትን መንገዶች ሁሉ ማየት ያስፈልጋል። ጦርነት ውስጥም ትልቅ ድርሻ እንዳላቸው ማሳየት ያስፈልጋል። የኢትዮጵያ መንግስት ይህን መረጃ ሊጠቀምበት ይገባል!

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule