• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የስደተኛ መታወቂያ የያዙ የትህነግ ተዋጊዎች ተይዘዋል፤ ተመድ እያጣራ ነው ብሏል

September 5, 2021 03:22 pm by Editor Leave a Comment

“የስደተኞች መታወቂያን ይዘው ተገኝተዋል” የተባሉ ታጣቂዎችን ጉዳይ እያጣራ እንደሆነ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ከፍተኛ የስደተኞች ጉዳይ ኤጀንሲ ገለጸ።

ኤጀንሲው “በሱዳን የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ የነበሩና የተመድ ስደተኞች ኤጀንሲ መታወቂያ የያዙ ታጣቂዎች ተገኙ” የሚሉ መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘዋወሩና በተለያዩ የሚድያ አውታሮች ሲዘገቡ መመልከቱን ስለ ጉዳዩ ለጠየቀው አል ዐይን አማርኛ በላከው የኢ-ሜይል መልዕክት አስታውቋል።

የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ አገኘሁ ተሻገር ሰሞኑን በሱዳን አቅጣጫ መጥተው “ሽንፋ የተባለ ቦታን ለመያዝ የተንቀሳቀሱ የቅማንትና ህወሃት ታጣቂዎች መደምሰሳቸው”ን የሚያሳውቅ ጽሁፍ በትዊተር ገጻቸው ማጋራታቸው የሚታወስ ነው።

ዓለም አቀፍ ብዙሃን መገናኛዎች ‘ህወሓት ሰብዓዊ እርዳታን እየዘረፈ ነው’ መባሉን “ከዓለም አቀፍ ተቋማት ሲሰሙ ብቻ መዘገባቸው ለምን ተብሎ መጠየቅ አለበት” ሲል ከትናንት በስቲያ አርብ ያስታወቀው የፌዴራል መንግስትም እየተገኙ ያሉት መታወቂያን መሰል ማስረጃዎች ስደተኛ መስለው ወደ ሱዳን መጠለያ ጣቢያዎች የገቡት የማይካድራ ጭፍጨፋ ፈጻሚ የሳምሪ ቡድን አባላት ተመልሰው ሳይመጡ እንዳልቀረ አመላካች ነው ሲል መግለጹ ይታወሳል።

ይህን ተከተሎም የተባበሩት መንግስታት ከፍተኛ የስደተኞች ጉዳይ ኤጀንሲ /ዩ.ኤን.ኤች.ሲ.አር/ የኢትዮጵያ ማስተባበሪያ ቢሮ ምላሽ ሰጥቷል።

ምላሹን የሰጡት የቢሮው ቃል አቀባይ ኔቨን ክሬቨንኮቪች ታጣቂዎቹ ይዘውት ተገኘ ከተባለው “የተመድ የስደተኛ መታወቂያ”ጋር በተያያዘ የወጣውን መረጃ ኤጀንሲው እያጣራ መሆኑን ለአል-ዐይን በላኩት የኢ-ሜይል መልዕክት ገልጸዋል።

ቃል አቀባዩ፤ ሰሞኑን “በሱዳን የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ የነበሩና የተመድ ስደተኞች ኤጀንሲ መታወቂያ የያዙ ታጣቂዎች ተመልሰው በግጭቱ ሲሳተፉ ተገኙ” የሚሉ መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘዋወሩና በተለያዩ የሚድያ አውታሮች ሲዘገቡ ተመልክተናል ብለዋል።

ተቋማቸው ጉዳዩን እያጣራ እንደሆነም ነው የገለጹት።

ስደተኞቹን የተመለከቱ አዳዲስ መረጃዎች ሲገኙ፣ ከመጠለያ ጣቢያዎች ሲወጡም ሆነ መታወቂያ ካርዳቸው ሲጠፋ የመረጃ ቋታችን የምናዘምንበት በመደበኛ የአሰራር ስርዓት አለን ብለዋል ስደተኞቹ ወደ ሃገራቸው ለመመለስ ሲወስኑ ስደተኛነታቸውን እንደሚያጡ በመጠቆም።

ኤጀንሲው “በቅርቡወደ ኢትዮጵያ በስደተኞች የተደረገ እንቅስቃሴ” አለመመልከቱንም ገልጸዋል ቃል አቀባዩ።

“በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ ሆነን የስደት ተመላሾችን የምናረጋግጥበት ሁኔታም የለም”ም ብለዋል ኔቨን ክሬቨንኮቪች።

ኤጀንሲው “የስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች የሲቪል ባህርይን ጠብቀው እንዲቆዩ እና ይህንን ለማረጋገጥ የሚያስችል ድጋፍ ለሱዳን መንግስት ለማድረግ ያለውን ቁርጠኝነት” ደጋግሞ መግለጹንም ተናግረዋል።

የተመድ ከፍተኛ የስደተኞች ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍሊፖ ግራንዴ በቅርቡ ወደ ሱዳን አቅንተው መጠለያ ጣቢያዎቹን ጎብኝተው ነበር።

ግራንዴ በዚሁ ጉብኝታቸው ይህንኑ መግለጻቸውንም ነው ያስታወቁት።

ክሬቨንኮቪች “በስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ ወታደራዊ ሥልጠናዎች ይሰጣሉ” የሚለው “መሠረተ ቢስ” ነውም ብለዋል።

ያልተረጋገጡ የግል መረጃዎችን የስደተኞች ናቸው በሚል በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ማጋራቱ እንዲቆምም አሳስበዋል።

ይህ በግለሰቦቹ፣ በቤተሰባቸውና በሱዳን በሚገኙ ስደተኞች ላይ ለበቀል እንደሚያነሳሳም ነው ቃል አቀባዩ የገለጹት። (አል-አይን)

ከዚሁ ጋር በተዛመደ የማኅበረሰብ አንቂ የሆነው ጌታቸው ሽፈራው መረጃው እንደተገኘ ይህንን መልዕክት በፌስቡኩ ለጥፎ ነበር፤

የኢትዮጵያ መንግሥት ሆይ!

ይሄውልህ የዓለም አቀፉን ማሕበረሰብ ቅሌት ማሳየት የምትችልበት መረጃ!

ከስር የተያያዘው መረጃ ሱዳንና UNCHCR  በዓለም አቀፍ ሕግ የሚያስጠይቅ ነው። ሀጎስ ሃይላይ በርሀ የተባለ ግለሰብ ሱዳን ውስጥ የUNHCR የስደተኛ የምዝገባ መታወቂያን ተቀብሏል። ስደተኛ ካምፕ ውስጥ ቀለብና መጠለያ እያገኘ ወጣ ብሎ ደግሞ እየሰለጠነ ከርሞ ኢትዮጵያን  ለመውጋት የመጣው ኃይል ዛሬ በቋራ መስመር ሲመታ መረጃዎቹ ተይዘዋል። ሀጎስ ምሳሌ ነው። እነ ጌታቸው ረዳ ሱዳን ውስጥ 30 ሺህ ጦር አለን ያሉት በሙሉ ስደተኛውን አሰልጥነው ነው።

በ1951 የጀኔቫ የስደተኞች ስምምነት መሰረት ስደተኛውን የተቀበለው ሀገርም ሆነ፣ ስደተኛውን የያዘው ተቋም ጥብቅ ግዴታዎች አሉባቸው። ሱዳን ስደተኛውን እንዳስጠለለች ሀገር የተቀበለችው ስደተኛ ጦርነት የሚያህል ተመድ በመርሁ የሚቃወመው ነገር እንዳይገባ የማድረግ ግዴታ አለባት። የሆነው ግን ስደተኞች ጣቢያ አካባቢ ማሰልጠኛ ተከፍቶ ስደተኛው አንዴ መጠለያ፣ ሌላ ጊዜ ማሰልጠኛ ጣቢያ እየተመላለሰ ኢትዮጵያን እንዲወጋ ተደርጓል። ያውም የሱዳንና የግብፅ መንግስት የመሳርያና ሌሎች እገዛዎችን አድርገውለት። የኢትዮጵያ መንግስት ይሄን መረጃ በማጠናከር  ለተመድና ለአባላቱ፣ ለኢትዮጵያ ወዳጅና ጠላቶች ማቅረብ አለበት።

ሱዳን ስደተኛ አስጠልላለሁ ብላ ከግብፅ ጋር ሆና አሰልጥና እየላከች መሆኑን ማሳወቅ አለበት። በተመድ ስር ያለው UNHCR በስሩ ያሉ ስደተኞችን ለጦርነት ተመልምለው፣ ሰልጥነው ሀገር ሲወጉ ዝም ብሎ እያየ እንደሆነ ለዓለም ማሳወቅ አለበት። የውጭ ጉዳይ በመግለጫው በደንብ ማካተት አለበት፣ ለኤምባሲዎች መረጃውን አጠናቅሮ ማድረስ አለበት። አምባሳደሮች ለያሉበት ሀገር መንግስትና ሚዲያ፣ በተመድ የኢትዮጵያ ተወካይ ደግሞ ለሚገባቸው አካላት ማድረስ አለበት። በዓለም አቀፍ ሕግ የሚኬድባቸው አካሄዶች በሙሉ ሊናቁ አይገባም።

ይህን ሁሉ የሚያደርገው በዓለም አቀፍ መድረክ ፍትሕ ስለሚገኝበት አይደለም። ነገር ግን አስር ጊዜ በኢትዮጵያ ጉዳይ ስብሰባ የሚጠራው ተደመድ ራሱ መጠለያ የሰጣቸው ስደተኞች ወታደር ሆነው ሀገር እየወጉ  መሆኑን ማሳወቅ ይገባል። ስደተኛ ካምፕ ውስጥ ሆነው ሱዳንና UNHCR እያንዳንዷን እንቅስቃሴ ሊቆጣጠሯቸው የሚገባቸው ስደተኞች ከባድ መሳርያ፣ የቡድንና የግል መሳርያ ይዘው ሀገር ሲወጉ፣ ንፁሃንን ሲጨፈጭፉ፣ ሲዘርፉ፣ ሲደፍሩ ነው የተደረሰባቸው።

እነ ሳማንታ ፓወር ሄደው በጎበኙት የሱዳን ካምፕ ያለው ስደተኛ ወታደር ሆኖ እየወጋን እንደሆነ ማሳወቅ ይገባል። በተመድ ስብሰባ አስር ጊዜ ስለስደተኛ አያያዝ እያነሱ የሚያወግዙን ልካቸውን ማወቅ አለባቸው። ቢያንስ ይሄ መረጃ ሌላ ጊዜ  ትህነግን ለመደገፍ ብለው፣ መርህን አጣመው አፍ  እንዳይከፍቱ መያዥያ ይሆናል።  ሄደው ሲጎበኙ ስደተኛው ሁሉ እየሰለጠነ እንደሆነ መረጃ አጥተው አይደለም። ስለሆነም የዓለም አቀፍ ተቋማት ነውርን ማሳወቅ የሚያስችሉትን መንገዶች ሁሉ ማየት ያስፈልጋል። ጦርነት ውስጥም ትልቅ ድርሻ እንዳላቸው ማሳየት ያስፈልጋል። የኢትዮጵያ መንግስት ይህን መረጃ ሊጠቀምበት ይገባል!

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule