• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሓት/ትህነግ ጊዜ እንዲሰጠው የሚጠይቅ “ስልታዊ” ውሳኔ አሳለፈ

November 20, 2019 02:05 pm by Editor 2 Comments

“ሳይወሰንልኝ” አልሳተፍም አለ 

የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ትህነግ/ህወሓት በቀጥታ መቃወሚያ ሳያቀርብ የኢህአዴግ እህትና አጋር ድርጅቶች እንዲዋሃዱ በሚወሰንበት የግንባሩ ጉባዔ ላይ ለመገኘት ፈቃድ አለማግኘቱን አስታወቀ። ይህንኑ የሚጠበቅ ውሳኔ ይፋ ሲያደርግ በተዘዋዋሪ ቀን እንዲሰጠው መጠየቁንና አሁንም ተጨማሪ ጊዜ እንደሚፈልግ ማብራሪያ ያላቀረበበትን የህግና የፖለቲካ ጉዳይ አስታኳል። 

በህዳር 6 ቀን 2012 የግንባሩ ሥራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ላይ በውህደቱ አጀንዳ በድምጽ ተሸንፎ የወጣው ህወሃት የሶስት ቀን ተጨማሪ ጊዜ መጠየቁን ከስብሰባው ማግስት በኋላ ሲያስተባብል የቆየው ትህነግ፣ ዛሬ ባሰራጨው መግለጫ “የትህነግ ማእከላዊ ኮሚቴ በጥናቱ ላይ እንዲወያይ ተወስኖ እያለ ምንም ዓይነት ውይይት ሳይደረግ በጥድፊያ የምክር ቤት ስብሰባ ማድረግ ተገቢ አይደለም” ሲል ተጨማሪ የመወያያ ቀን ተሰጥቶት እንደነበር አምኗል። በተሰጠው ጊዜ ውስጥ ቀኑን በትክክል ባያስታውቅም የትህነግ ማዕከላዊ ኮሚቴ ተሰብስቦ የግንባሩ ምክር ቤት የውህደቱን አጀንዳ ለማጽደቅ ህጋዊና ፖለቲካዊ ሥልጣን እንደሌለው አመልክቷል። ህጋዊና ፖለቲካዊ ያላቸውን ጉዳዮች ግን አላብራራም።

የህወሓት/ትህነግ መግለጫ

ያረጀውና ለሁለት ዐሥርት ዓመታት ሲንከባለል የኖረው የውህደት ጥያቄና ጥናት ተግባራዊ እንዲሆን በኢህአዴግ የመጨረሻው ጉባኤ ለሥራ አስፈጻሚው ውክልና ሲሰጠ በድምጽ ያጸደቀው ህወሓት/ትህነግ፣ የውህደቱ ጥያቄ ወደ ፍጻሜ ሲጠጋ “አገር ትበተናለች” በሚል ዛቻ ሳይቀር ሲያስፈራራና የራሱን የሽግግር መንግሥት ሲያደራጅ እንዳልቆየ ዛሬ “የድርጅቴ ጉባዔ ካልፈቀደ ለመዋሃድ ማንዴት የለኝም” ሲል ጉዳዩን የአሠራርና የተዓማኒነት አካሄድ ሊያስመስለው ሞክሯል። 

ቀድሞ ድርጎ እየሠፈረ ያደራጃቸውን ተለጣፊና አሽከር ድርጅቶች በመሰብሰብ “አገሪቱን እንታደግ” በሚል ሽፋን የሽግግር መንግሥት ምስረታ ላይ ተጠምዶ የነበረው ህወሃት/ትህነግ፣ ሙከራው ሲከሽፍበት የውህደቱን ውሳኔ ተከትሎ በትግራይ ሠራዊትና ሚሊሺያ የጦርነት ቀስቃሽ ቃለ ምልልሶችን በማካሄድ ላይ ይገኛል። 

በትግራይ ፓርቲዎችን እንደ ቀድሞ ጠፍጥፎ መንግሥት ለመገልበጥ የተሞከረው ዕቅድ ሲከሽፍ የዲፋክቶ (ጊዜያዊ) መንግሥት ማቋቋም መጀመሩን ይፋ ያደረገው ትህነግ፣ ውህደቱን የማይፈልገው ከሆነ ለምን ዝም ብሎ ለቆ በመውጣት የራሱን ሥራ እንደማይሠራ ለበርካቶች ግራ የሚያጋባ ጉዳይ ሆኗል። የትህነግ ተቃዋሚ ድርጅቶች በበኩላቸው የትግራይ ህዝብ ውሳኔ ሳይካተትበት ትህነግ “ዲፋክቶ ስቴት” እመሠርታለሁ ማለቱና ውህደቱን መቃወሙ ፍርሃት የወለደው ውሳኔ መሆኑንን በተደጋጋሚ እየገለጹ ነው።  

የቁም እስረኞች ሆነው በሆቴል የመሸጉት የህወሓት/ትህነግ አንጋፋ ወንበዴዎች በሚሰጡት መመሪያ የሚንቀሳቀሰው ትህነግ አድሮ ምን እንደሚወስን ባይታወቅም በሥውር ከአክራሪ ኃይሎች ጋር በመመሳጠር አገሪቱን የማተራመስ ተግባሩን ሊገፋበት ካልሆነ ሌላ አማራጭ እንደማይኖረው አስተያየት ሰጪዎች መግለጫው ከመውጣቱ በፊት ሲናገሩ ነበር።

ህወሃት/ትህነግ በዚህ ትግራይን ይዞ የራሱን አጀንዳ እያስፈጸመ የሚሄድበት አግባብነት የሌለውን አሠራር ትግራይን መሠረት ያደረጉ ፓርቲዎች ሊቃወሙት ይገባል የሚለው አስተያየት ከበፊትም ሲባል የኖረ ነበር። ግፍን ዝም ብሎ መቀበል አይሆንለትም የሚባልለት ታላቁ የትግራይ ሕዝብ እንዲህ ዓይነቱን የትህነግ/ህወሓትን የውንብድና አሠራር በግልጽ በመቃወም ሊታገለው ይገባል። ትግራይን ከሌላው ሕዝብ በመለየት ለራሳቸው ጥቅም የሚሯሯጡትን እስከመጨረሻው ታግሎ ራሱን ከህወሃት/ትህነግ ጭቆና ነጻ ያወጣል የሚለው በቀጣይ የሚታይ ጉዳይ ሆኗል።

ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት/ትህነግ) በማለት የሚጠራውና በኢትዮጵያ እጅግ አስከፊ የሚባልና ትውልድን ያወደመ ርዕዮት በመከተል አገር ያፈረሰው የወንበዴዎች ጥርቅም፤ እስካሁንም በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ተመዝግቦ የሚገኝ ድርጅት መሆኑ ይታወቃል። አባላቱና ደጋፊዎችም በዚሁ ሁኔታ የሚታዩ መሆናቸውን ብዙዎች የሚስማሙበት ነው።

(ፎቶ፤ በኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ወቅት ከፊት የተቀመጡት ደብረጽዮንና ሌላኛው የበረሃ ወንበዴ ባልደረባው አዲስዓለም ባሌማ)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Politics Tagged With: eprdf, Full Width Top, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Babylon says

    November 21, 2019 01:38 pm at 1:38 pm

    TPLF is a terrorist organization secretly established by illuminati jews.The Mark on our flag is symbol of lucifer+satan http://www.antichristconspiracy.com http://www.realjewnews.com

    Reply
  2. DDOP says

    December 7, 2019 12:22 pm at 12:22 pm

    No no…let all of us give respect to our lovely country for futur generation

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule