• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሓት/ትህነግ ጊዜ እንዲሰጠው የሚጠይቅ “ስልታዊ” ውሳኔ አሳለፈ

November 20, 2019 02:05 pm by Editor 2 Comments

“ሳይወሰንልኝ” አልሳተፍም አለ 

የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ትህነግ/ህወሓት በቀጥታ መቃወሚያ ሳያቀርብ የኢህአዴግ እህትና አጋር ድርጅቶች እንዲዋሃዱ በሚወሰንበት የግንባሩ ጉባዔ ላይ ለመገኘት ፈቃድ አለማግኘቱን አስታወቀ። ይህንኑ የሚጠበቅ ውሳኔ ይፋ ሲያደርግ በተዘዋዋሪ ቀን እንዲሰጠው መጠየቁንና አሁንም ተጨማሪ ጊዜ እንደሚፈልግ ማብራሪያ ያላቀረበበትን የህግና የፖለቲካ ጉዳይ አስታኳል። 

በህዳር 6 ቀን 2012 የግንባሩ ሥራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ላይ በውህደቱ አጀንዳ በድምጽ ተሸንፎ የወጣው ህወሃት የሶስት ቀን ተጨማሪ ጊዜ መጠየቁን ከስብሰባው ማግስት በኋላ ሲያስተባብል የቆየው ትህነግ፣ ዛሬ ባሰራጨው መግለጫ “የትህነግ ማእከላዊ ኮሚቴ በጥናቱ ላይ እንዲወያይ ተወስኖ እያለ ምንም ዓይነት ውይይት ሳይደረግ በጥድፊያ የምክር ቤት ስብሰባ ማድረግ ተገቢ አይደለም” ሲል ተጨማሪ የመወያያ ቀን ተሰጥቶት እንደነበር አምኗል። በተሰጠው ጊዜ ውስጥ ቀኑን በትክክል ባያስታውቅም የትህነግ ማዕከላዊ ኮሚቴ ተሰብስቦ የግንባሩ ምክር ቤት የውህደቱን አጀንዳ ለማጽደቅ ህጋዊና ፖለቲካዊ ሥልጣን እንደሌለው አመልክቷል። ህጋዊና ፖለቲካዊ ያላቸውን ጉዳዮች ግን አላብራራም።

የህወሓት/ትህነግ መግለጫ

ያረጀውና ለሁለት ዐሥርት ዓመታት ሲንከባለል የኖረው የውህደት ጥያቄና ጥናት ተግባራዊ እንዲሆን በኢህአዴግ የመጨረሻው ጉባኤ ለሥራ አስፈጻሚው ውክልና ሲሰጠ በድምጽ ያጸደቀው ህወሓት/ትህነግ፣ የውህደቱ ጥያቄ ወደ ፍጻሜ ሲጠጋ “አገር ትበተናለች” በሚል ዛቻ ሳይቀር ሲያስፈራራና የራሱን የሽግግር መንግሥት ሲያደራጅ እንዳልቆየ ዛሬ “የድርጅቴ ጉባዔ ካልፈቀደ ለመዋሃድ ማንዴት የለኝም” ሲል ጉዳዩን የአሠራርና የተዓማኒነት አካሄድ ሊያስመስለው ሞክሯል። 

ቀድሞ ድርጎ እየሠፈረ ያደራጃቸውን ተለጣፊና አሽከር ድርጅቶች በመሰብሰብ “አገሪቱን እንታደግ” በሚል ሽፋን የሽግግር መንግሥት ምስረታ ላይ ተጠምዶ የነበረው ህወሃት/ትህነግ፣ ሙከራው ሲከሽፍበት የውህደቱን ውሳኔ ተከትሎ በትግራይ ሠራዊትና ሚሊሺያ የጦርነት ቀስቃሽ ቃለ ምልልሶችን በማካሄድ ላይ ይገኛል። 

በትግራይ ፓርቲዎችን እንደ ቀድሞ ጠፍጥፎ መንግሥት ለመገልበጥ የተሞከረው ዕቅድ ሲከሽፍ የዲፋክቶ (ጊዜያዊ) መንግሥት ማቋቋም መጀመሩን ይፋ ያደረገው ትህነግ፣ ውህደቱን የማይፈልገው ከሆነ ለምን ዝም ብሎ ለቆ በመውጣት የራሱን ሥራ እንደማይሠራ ለበርካቶች ግራ የሚያጋባ ጉዳይ ሆኗል። የትህነግ ተቃዋሚ ድርጅቶች በበኩላቸው የትግራይ ህዝብ ውሳኔ ሳይካተትበት ትህነግ “ዲፋክቶ ስቴት” እመሠርታለሁ ማለቱና ውህደቱን መቃወሙ ፍርሃት የወለደው ውሳኔ መሆኑንን በተደጋጋሚ እየገለጹ ነው።  

የቁም እስረኞች ሆነው በሆቴል የመሸጉት የህወሓት/ትህነግ አንጋፋ ወንበዴዎች በሚሰጡት መመሪያ የሚንቀሳቀሰው ትህነግ አድሮ ምን እንደሚወስን ባይታወቅም በሥውር ከአክራሪ ኃይሎች ጋር በመመሳጠር አገሪቱን የማተራመስ ተግባሩን ሊገፋበት ካልሆነ ሌላ አማራጭ እንደማይኖረው አስተያየት ሰጪዎች መግለጫው ከመውጣቱ በፊት ሲናገሩ ነበር።

ህወሃት/ትህነግ በዚህ ትግራይን ይዞ የራሱን አጀንዳ እያስፈጸመ የሚሄድበት አግባብነት የሌለውን አሠራር ትግራይን መሠረት ያደረጉ ፓርቲዎች ሊቃወሙት ይገባል የሚለው አስተያየት ከበፊትም ሲባል የኖረ ነበር። ግፍን ዝም ብሎ መቀበል አይሆንለትም የሚባልለት ታላቁ የትግራይ ሕዝብ እንዲህ ዓይነቱን የትህነግ/ህወሓትን የውንብድና አሠራር በግልጽ በመቃወም ሊታገለው ይገባል። ትግራይን ከሌላው ሕዝብ በመለየት ለራሳቸው ጥቅም የሚሯሯጡትን እስከመጨረሻው ታግሎ ራሱን ከህወሃት/ትህነግ ጭቆና ነጻ ያወጣል የሚለው በቀጣይ የሚታይ ጉዳይ ሆኗል።

ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት/ትህነግ) በማለት የሚጠራውና በኢትዮጵያ እጅግ አስከፊ የሚባልና ትውልድን ያወደመ ርዕዮት በመከተል አገር ያፈረሰው የወንበዴዎች ጥርቅም፤ እስካሁንም በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ተመዝግቦ የሚገኝ ድርጅት መሆኑ ይታወቃል። አባላቱና ደጋፊዎችም በዚሁ ሁኔታ የሚታዩ መሆናቸውን ብዙዎች የሚስማሙበት ነው።

(ፎቶ፤ በኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ወቅት ከፊት የተቀመጡት ደብረጽዮንና ሌላኛው የበረሃ ወንበዴ ባልደረባው አዲስዓለም ባሌማ)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Filed Under: News, Politics Tagged With: eprdf, Full Width Top, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Babylon says

    November 21, 2019 01:38 pm at 1:38 pm

    TPLF is a terrorist organization secretly established by illuminati jews.The Mark on our flag is symbol of lucifer+satan http://www.antichristconspiracy.com http://www.realjewnews.com

    Reply
  2. DDOP says

    December 7, 2019 12:22 pm at 12:22 pm

    No no…let all of us give respect to our lovely country for futur generation

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
Copyright © 2026 · Goolgule