• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሓት/ትህነግ ጊዜ እንዲሰጠው የሚጠይቅ “ስልታዊ” ውሳኔ አሳለፈ

November 20, 2019 02:05 pm by Editor 2 Comments

“ሳይወሰንልኝ” አልሳተፍም አለ 

የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ትህነግ/ህወሓት በቀጥታ መቃወሚያ ሳያቀርብ የኢህአዴግ እህትና አጋር ድርጅቶች እንዲዋሃዱ በሚወሰንበት የግንባሩ ጉባዔ ላይ ለመገኘት ፈቃድ አለማግኘቱን አስታወቀ። ይህንኑ የሚጠበቅ ውሳኔ ይፋ ሲያደርግ በተዘዋዋሪ ቀን እንዲሰጠው መጠየቁንና አሁንም ተጨማሪ ጊዜ እንደሚፈልግ ማብራሪያ ያላቀረበበትን የህግና የፖለቲካ ጉዳይ አስታኳል። 

በህዳር 6 ቀን 2012 የግንባሩ ሥራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ላይ በውህደቱ አጀንዳ በድምጽ ተሸንፎ የወጣው ህወሃት የሶስት ቀን ተጨማሪ ጊዜ መጠየቁን ከስብሰባው ማግስት በኋላ ሲያስተባብል የቆየው ትህነግ፣ ዛሬ ባሰራጨው መግለጫ “የትህነግ ማእከላዊ ኮሚቴ በጥናቱ ላይ እንዲወያይ ተወስኖ እያለ ምንም ዓይነት ውይይት ሳይደረግ በጥድፊያ የምክር ቤት ስብሰባ ማድረግ ተገቢ አይደለም” ሲል ተጨማሪ የመወያያ ቀን ተሰጥቶት እንደነበር አምኗል። በተሰጠው ጊዜ ውስጥ ቀኑን በትክክል ባያስታውቅም የትህነግ ማዕከላዊ ኮሚቴ ተሰብስቦ የግንባሩ ምክር ቤት የውህደቱን አጀንዳ ለማጽደቅ ህጋዊና ፖለቲካዊ ሥልጣን እንደሌለው አመልክቷል። ህጋዊና ፖለቲካዊ ያላቸውን ጉዳዮች ግን አላብራራም።

የህወሓት/ትህነግ መግለጫ

ያረጀውና ለሁለት ዐሥርት ዓመታት ሲንከባለል የኖረው የውህደት ጥያቄና ጥናት ተግባራዊ እንዲሆን በኢህአዴግ የመጨረሻው ጉባኤ ለሥራ አስፈጻሚው ውክልና ሲሰጠ በድምጽ ያጸደቀው ህወሓት/ትህነግ፣ የውህደቱ ጥያቄ ወደ ፍጻሜ ሲጠጋ “አገር ትበተናለች” በሚል ዛቻ ሳይቀር ሲያስፈራራና የራሱን የሽግግር መንግሥት ሲያደራጅ እንዳልቆየ ዛሬ “የድርጅቴ ጉባዔ ካልፈቀደ ለመዋሃድ ማንዴት የለኝም” ሲል ጉዳዩን የአሠራርና የተዓማኒነት አካሄድ ሊያስመስለው ሞክሯል። 

ቀድሞ ድርጎ እየሠፈረ ያደራጃቸውን ተለጣፊና አሽከር ድርጅቶች በመሰብሰብ “አገሪቱን እንታደግ” በሚል ሽፋን የሽግግር መንግሥት ምስረታ ላይ ተጠምዶ የነበረው ህወሃት/ትህነግ፣ ሙከራው ሲከሽፍበት የውህደቱን ውሳኔ ተከትሎ በትግራይ ሠራዊትና ሚሊሺያ የጦርነት ቀስቃሽ ቃለ ምልልሶችን በማካሄድ ላይ ይገኛል። 

በትግራይ ፓርቲዎችን እንደ ቀድሞ ጠፍጥፎ መንግሥት ለመገልበጥ የተሞከረው ዕቅድ ሲከሽፍ የዲፋክቶ (ጊዜያዊ) መንግሥት ማቋቋም መጀመሩን ይፋ ያደረገው ትህነግ፣ ውህደቱን የማይፈልገው ከሆነ ለምን ዝም ብሎ ለቆ በመውጣት የራሱን ሥራ እንደማይሠራ ለበርካቶች ግራ የሚያጋባ ጉዳይ ሆኗል። የትህነግ ተቃዋሚ ድርጅቶች በበኩላቸው የትግራይ ህዝብ ውሳኔ ሳይካተትበት ትህነግ “ዲፋክቶ ስቴት” እመሠርታለሁ ማለቱና ውህደቱን መቃወሙ ፍርሃት የወለደው ውሳኔ መሆኑንን በተደጋጋሚ እየገለጹ ነው።  

የቁም እስረኞች ሆነው በሆቴል የመሸጉት የህወሓት/ትህነግ አንጋፋ ወንበዴዎች በሚሰጡት መመሪያ የሚንቀሳቀሰው ትህነግ አድሮ ምን እንደሚወስን ባይታወቅም በሥውር ከአክራሪ ኃይሎች ጋር በመመሳጠር አገሪቱን የማተራመስ ተግባሩን ሊገፋበት ካልሆነ ሌላ አማራጭ እንደማይኖረው አስተያየት ሰጪዎች መግለጫው ከመውጣቱ በፊት ሲናገሩ ነበር።

ህወሃት/ትህነግ በዚህ ትግራይን ይዞ የራሱን አጀንዳ እያስፈጸመ የሚሄድበት አግባብነት የሌለውን አሠራር ትግራይን መሠረት ያደረጉ ፓርቲዎች ሊቃወሙት ይገባል የሚለው አስተያየት ከበፊትም ሲባል የኖረ ነበር። ግፍን ዝም ብሎ መቀበል አይሆንለትም የሚባልለት ታላቁ የትግራይ ሕዝብ እንዲህ ዓይነቱን የትህነግ/ህወሓትን የውንብድና አሠራር በግልጽ በመቃወም ሊታገለው ይገባል። ትግራይን ከሌላው ሕዝብ በመለየት ለራሳቸው ጥቅም የሚሯሯጡትን እስከመጨረሻው ታግሎ ራሱን ከህወሃት/ትህነግ ጭቆና ነጻ ያወጣል የሚለው በቀጣይ የሚታይ ጉዳይ ሆኗል።

ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት/ትህነግ) በማለት የሚጠራውና በኢትዮጵያ እጅግ አስከፊ የሚባልና ትውልድን ያወደመ ርዕዮት በመከተል አገር ያፈረሰው የወንበዴዎች ጥርቅም፤ እስካሁንም በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ተመዝግቦ የሚገኝ ድርጅት መሆኑ ይታወቃል። አባላቱና ደጋፊዎችም በዚሁ ሁኔታ የሚታዩ መሆናቸውን ብዙዎች የሚስማሙበት ነው።

(ፎቶ፤ በኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ወቅት ከፊት የተቀመጡት ደብረጽዮንና ሌላኛው የበረሃ ወንበዴ ባልደረባው አዲስዓለም ባሌማ)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: eprdf, Full Width Top, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Babylon says

    November 21, 2019 01:38 pm at 1:38 pm

    TPLF is a terrorist organization secretly established by illuminati jews.The Mark on our flag is symbol of lucifer+satan http://www.antichristconspiracy.com http://www.realjewnews.com

    Reply
  2. DDOP says

    December 7, 2019 12:22 pm at 12:22 pm

    No no…let all of us give respect to our lovely country for futur generation

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule