• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሓት/ትህነግ ጊዜ እንዲሰጠው የሚጠይቅ “ስልታዊ” ውሳኔ አሳለፈ

November 20, 2019 02:05 pm by Editor 2 Comments

“ሳይወሰንልኝ” አልሳተፍም አለ 

የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ትህነግ/ህወሓት በቀጥታ መቃወሚያ ሳያቀርብ የኢህአዴግ እህትና አጋር ድርጅቶች እንዲዋሃዱ በሚወሰንበት የግንባሩ ጉባዔ ላይ ለመገኘት ፈቃድ አለማግኘቱን አስታወቀ። ይህንኑ የሚጠበቅ ውሳኔ ይፋ ሲያደርግ በተዘዋዋሪ ቀን እንዲሰጠው መጠየቁንና አሁንም ተጨማሪ ጊዜ እንደሚፈልግ ማብራሪያ ያላቀረበበትን የህግና የፖለቲካ ጉዳይ አስታኳል። 

በህዳር 6 ቀን 2012 የግንባሩ ሥራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ላይ በውህደቱ አጀንዳ በድምጽ ተሸንፎ የወጣው ህወሃት የሶስት ቀን ተጨማሪ ጊዜ መጠየቁን ከስብሰባው ማግስት በኋላ ሲያስተባብል የቆየው ትህነግ፣ ዛሬ ባሰራጨው መግለጫ “የትህነግ ማእከላዊ ኮሚቴ በጥናቱ ላይ እንዲወያይ ተወስኖ እያለ ምንም ዓይነት ውይይት ሳይደረግ በጥድፊያ የምክር ቤት ስብሰባ ማድረግ ተገቢ አይደለም” ሲል ተጨማሪ የመወያያ ቀን ተሰጥቶት እንደነበር አምኗል። በተሰጠው ጊዜ ውስጥ ቀኑን በትክክል ባያስታውቅም የትህነግ ማዕከላዊ ኮሚቴ ተሰብስቦ የግንባሩ ምክር ቤት የውህደቱን አጀንዳ ለማጽደቅ ህጋዊና ፖለቲካዊ ሥልጣን እንደሌለው አመልክቷል። ህጋዊና ፖለቲካዊ ያላቸውን ጉዳዮች ግን አላብራራም።

የህወሓት/ትህነግ መግለጫ

ያረጀውና ለሁለት ዐሥርት ዓመታት ሲንከባለል የኖረው የውህደት ጥያቄና ጥናት ተግባራዊ እንዲሆን በኢህአዴግ የመጨረሻው ጉባኤ ለሥራ አስፈጻሚው ውክልና ሲሰጠ በድምጽ ያጸደቀው ህወሓት/ትህነግ፣ የውህደቱ ጥያቄ ወደ ፍጻሜ ሲጠጋ “አገር ትበተናለች” በሚል ዛቻ ሳይቀር ሲያስፈራራና የራሱን የሽግግር መንግሥት ሲያደራጅ እንዳልቆየ ዛሬ “የድርጅቴ ጉባዔ ካልፈቀደ ለመዋሃድ ማንዴት የለኝም” ሲል ጉዳዩን የአሠራርና የተዓማኒነት አካሄድ ሊያስመስለው ሞክሯል። 

ቀድሞ ድርጎ እየሠፈረ ያደራጃቸውን ተለጣፊና አሽከር ድርጅቶች በመሰብሰብ “አገሪቱን እንታደግ” በሚል ሽፋን የሽግግር መንግሥት ምስረታ ላይ ተጠምዶ የነበረው ህወሃት/ትህነግ፣ ሙከራው ሲከሽፍበት የውህደቱን ውሳኔ ተከትሎ በትግራይ ሠራዊትና ሚሊሺያ የጦርነት ቀስቃሽ ቃለ ምልልሶችን በማካሄድ ላይ ይገኛል። 

በትግራይ ፓርቲዎችን እንደ ቀድሞ ጠፍጥፎ መንግሥት ለመገልበጥ የተሞከረው ዕቅድ ሲከሽፍ የዲፋክቶ (ጊዜያዊ) መንግሥት ማቋቋም መጀመሩን ይፋ ያደረገው ትህነግ፣ ውህደቱን የማይፈልገው ከሆነ ለምን ዝም ብሎ ለቆ በመውጣት የራሱን ሥራ እንደማይሠራ ለበርካቶች ግራ የሚያጋባ ጉዳይ ሆኗል። የትህነግ ተቃዋሚ ድርጅቶች በበኩላቸው የትግራይ ህዝብ ውሳኔ ሳይካተትበት ትህነግ “ዲፋክቶ ስቴት” እመሠርታለሁ ማለቱና ውህደቱን መቃወሙ ፍርሃት የወለደው ውሳኔ መሆኑንን በተደጋጋሚ እየገለጹ ነው።  

የቁም እስረኞች ሆነው በሆቴል የመሸጉት የህወሓት/ትህነግ አንጋፋ ወንበዴዎች በሚሰጡት መመሪያ የሚንቀሳቀሰው ትህነግ አድሮ ምን እንደሚወስን ባይታወቅም በሥውር ከአክራሪ ኃይሎች ጋር በመመሳጠር አገሪቱን የማተራመስ ተግባሩን ሊገፋበት ካልሆነ ሌላ አማራጭ እንደማይኖረው አስተያየት ሰጪዎች መግለጫው ከመውጣቱ በፊት ሲናገሩ ነበር።

ህወሃት/ትህነግ በዚህ ትግራይን ይዞ የራሱን አጀንዳ እያስፈጸመ የሚሄድበት አግባብነት የሌለውን አሠራር ትግራይን መሠረት ያደረጉ ፓርቲዎች ሊቃወሙት ይገባል የሚለው አስተያየት ከበፊትም ሲባል የኖረ ነበር። ግፍን ዝም ብሎ መቀበል አይሆንለትም የሚባልለት ታላቁ የትግራይ ሕዝብ እንዲህ ዓይነቱን የትህነግ/ህወሓትን የውንብድና አሠራር በግልጽ በመቃወም ሊታገለው ይገባል። ትግራይን ከሌላው ሕዝብ በመለየት ለራሳቸው ጥቅም የሚሯሯጡትን እስከመጨረሻው ታግሎ ራሱን ከህወሃት/ትህነግ ጭቆና ነጻ ያወጣል የሚለው በቀጣይ የሚታይ ጉዳይ ሆኗል።

ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት/ትህነግ) በማለት የሚጠራውና በኢትዮጵያ እጅግ አስከፊ የሚባልና ትውልድን ያወደመ ርዕዮት በመከተል አገር ያፈረሰው የወንበዴዎች ጥርቅም፤ እስካሁንም በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ተመዝግቦ የሚገኝ ድርጅት መሆኑ ይታወቃል። አባላቱና ደጋፊዎችም በዚሁ ሁኔታ የሚታዩ መሆናቸውን ብዙዎች የሚስማሙበት ነው።

(ፎቶ፤ በኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ወቅት ከፊት የተቀመጡት ደብረጽዮንና ሌላኛው የበረሃ ወንበዴ ባልደረባው አዲስዓለም ባሌማ)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: eprdf, Full Width Top, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Babylon says

    November 21, 2019 01:38 pm at 1:38 pm

    TPLF is a terrorist organization secretly established by illuminati jews.The Mark on our flag is symbol of lucifer+satan http://www.antichristconspiracy.com http://www.realjewnews.com

    Reply
  2. DDOP says

    December 7, 2019 12:22 pm at 12:22 pm

    No no…let all of us give respect to our lovely country for futur generation

    Reply

Leave a Reply to DDOP Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule