• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ልጆቻችን ናቸው እኮ” ኮሚሽነር አበረ አዳሙ

January 26, 2020 03:58 pm by Editor Leave a Comment

“አንዳንዱ ነገር ድራማ ይመስላል” የኦነግ ቃል አቀባይ ቀጄላ መርዳሳ

በህዳር ወር 2012 የመጨረሻ ሳምንት ከደንቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ወደ ጋምቤላ ከተማ በመጓዝ ላይ ሳሉ በአጋቾች እጅ የገቡት ተማሪዎች ጉዳይ አሁንም አወዛጋቢ ሆኖ ቀጥሏል። እስከ አሁን ባለው መረጃም ተማሪዎቹ የአማራ ክልል ነዋሪ እንደሆኑ በመገለፁ አዲስ ማለዳ የአማራ ክልል የፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አበረ አዳሙን አነጋግራለች።

ኮሚሽነሩ ምንም እንኳን በጉዳዩ ላይ በቀጥታ ለመሳተፍ የህግ ገደብ ቢኖርባቸውም የታገቱት ተማሪዎች ከተያዙ እለት ጀምሮ የልጆቹን ሁኔታ በቅርበት እየተከታተሉት አንደሆነ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል። “የስልጣን ገደብ ቢኖርብንም ልጆቻችን ናቸው እኮ፣ መቶ በመቶ ቅድሚያ ሰጥተን እየተከታተል ነው” ሲሉ ለአዲስ ማለዳ ዛሬ አመሻሹ ላይ ገልጸዋል። “ጉዳዩ የኛ ጉዳይ ነው፣ ነገር ግን መዋቅር መከበር ስላለበት የፌደራል ፖሊስ እና የክልሉ ፖሊስ እንጂ እኛ ምንም መናገር አንችልም” ብለዋል።

“የማውቀው ነገር የለም ልልሽ አልፈልግም፤ ግን ደሞ መግለጫ ለመስጠት ገደብ አለብኝ” ሲሉም ተጨማሪ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል። 

በወለጋ ዞኖች ጠንካራ መሰረት እንዳለው የሚታወቀው የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ቃል አቀባይ ቀጄላ መርዳሳ ግን “ጉዳዩን በደንቢ ዶሎ አካባቢ ካሉ ሰዎች አጣርተን የተጨበጠ ነገር አላገኘንም፤ አንዳንዱ ነገር ድራማ ይመስላል” ሲሉ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።

“ማን የት ቦታ እንደተያዘ ለማረጋገጥ ህብረተሰቡን እና አንዳንድ ተቋማትን ጠይቀናል፣ ተጨባጭ ነገር ማግኘት አልቻልንም” ብለዋል። “ምን አልባት ውዥንብር ይሆናል ብለን እንጠረጥራለን፣ ጉዳዩ የተማሪዎቹ ብቻ አይደለም፣ ከዚህ በፊት የኦሮሚያ ክልል ተወላጅ የሆነ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ተያዘ ተብሎ የት እንደገባ ሳይታወቅ ከዛ ተገኘ ተባለ፣ የት እንደነበረ ማን እንደያዘው አልተናገረም” ሲሉም ጥርጣሬአቸውን ገለጸዋል።

የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽህፈት ቤት የፕሬስ ሴክሪታሪያት ኃላፊ ንጉሱ ጥላሁን ከሁለት ሳምንት በፊት 21 ተማሪዎች መለቀቃቸውን እና ከነዚህም 13ቱ ሴቶች ስድስቱ ወንዶች መሆናቸውን ገልፀው ነበር። በተጨማሪም አምስት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እና አንድ የአካባቢው ነዋሪ የሆነ ወጣት በአጋቾች እጅ እንደሚገኙ እና እነዚህንም ለማስፈታት መንግስት ጥረት እያረገ መሆኑን ገልፀው ነበር።

በታጋቾቹ ደህንነት ላይ የመጨረሻውን መረጃ ለዶይቼ ቨለ የሰጡት የኦሮሚያ ክልል የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሃላፊ ጌታቸው ባልቻ ከእገታው የተለቀቁት 21 ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው ተመልሰዋል ማለታቸው አይዘነጋም።

አዲስ ማለዳም ወደ የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽህፈት ቤት የፕሬስ ሴክሪታሪያት ኃላፊ ንጉሱ ጋር መረጃ ለማግኘት ያደረገቸው የስልክ ጥሪ ሳይሳካ ቀርቷል።

አዲስ ማለዳ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Social Tagged With: bring back our sisters, Full Width Top, Middle Column, olf, olf shine

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule