• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው

February 3, 2023 05:17 pm by Editor Leave a Comment

ክርስቲያኗ ክስ መመሥረቷም ተሰምቷል

በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ ውስጥ የተፈጠረውን መከፋፍለ ተከትሎ አንደኛውን ወገን ለማውገዝ ተጠርቶ ከነበረው የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ መካከል የባህር ዳሩ መሰረዙ ተገለጸ።

“ቅዱስ ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ ጾመ ነነዌን ምክንያት በማድረግ በመላው ዓለም የሚገኙ ሕዝበ ክርስቲያን ጥቁር ልብስ ብቻ በመልበስ በጾምና በጸሎት ምሕላ በመያዝ በቤተ ክርስቲያን ዓውደ ምሕረት በመገኘት ወደ እግዚአብሔር ጾም፤ ጸሎትና ምሕላ እንዲቀርብ” ሲል ቅዱስ ሲኖዶስ ባስተላለፈው ጥሪ መሰረት ነው “ጥር 28 በባሕር ዳር ከተማ እሑድ ጥር 28 ፡ 2015 ዓ.ም ባሕር ዳር መስቀል አደባባይ ሊደረግ የነበረው “ኦርቶዶክሳዊ” የተባለው ሰልፍ እና የምህላ ፀሎት መራዘሙ በመግለጫ የተገለጸው።

“ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪ አስተላልፏል። ስለሆነም በቀጣይ በቅዱስ ሲኖዶሱ የሚቀርብልን አቅጣጫ ተከትለን የተጀመሩ ስራዎች ሳይቋረጡ ለጊዜው ለጥር 28 ተጠርቶ የነበረው ሰልፍ ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል” ሲል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የባሕርዳር ሀገረ ስብከት አመልክቷል።

ቀደም ሲል “ሼር! ፖስት ይሁን!” በሚል “ባሕርዳር ኦርቶዶክሳዊ ሰልፍና ጸሎተ ምህላ ጥሪ አድርጋለች። የፊታችን እሑድ ሁሉም ምእመን ከአጥቢያው በኅብረት ተነሥቶ 1:30 ባሕር ዳር መስቀል አደባባይ እንዲደርስ ጥሪ ተደርጓል። በዚህ አጋጣሚ በኮሚቴው ከተዘጋጁ ባነሮች ውጭና ያልተፈቀዱ መልእክቶችን ይዞ መምጣትና ማስተላለፍ የተከለከለ ሲሆን ከቤተ ክርስቲያኒቱ ዐርማ ውጭም ምንም ነገር መያዝ አይፈቀድም ተብሏል” ታውጆ ነበር።

በተመሳሳይ ዜና ችግሩ በመነጋገር ብቻ እንደሚፈታ የመስማማት ፍንጭ መታየቱን ለጉዳይ ቅርብ የሆኑ ገልጸውልናል። ዝርዝሩን ወደፊት እንደሚናገሩ ያስታወቁ “ኦርቶዶክስ በፖለቲካ ቁማርተኞችና ካድሬዎች ሴራ ከገጠማት ችግር በቅርቡ እንደምትፈውስ እምነት አለን” ሲሉ ተናግረዋል። 

“ሁሉም ወገን ጋር እውነት፣ ሁለቱም ወገኖች ጋር ስህተት አለ” ያሉት ክፍሎች፣ እንደ እምነት አባት ንስሃ ገብተው ችግራቸውን መፍታት ሲገባቸው ጉዳዩን ለተመሪው ምዕመን አቀብሎ ለውዝግብ በር መክፈት ትክክል እንዳልሆነ የተቀበሉ አሉ። ከሁለቱም ወገን ስህተታቸውን ለማረም የተዘጋጁ መኖራቸው አንድ እርምጃ እንደሆነ ገልጸው “ታላቁ መስዋዕትነት ይቅርታ ማድረግና ይቅርታን መቀበል ነው። ይህን የማያደርጉ ክርስትና አልገባቸውም” በሚል መወቀሳቸውንም አመልክተዋል። ህዝበ ክርስቲያኑ ለዕምነቱ ስለሚቀና ከስሜትና ድፍን ጥሪ መታቀብ እንደሚገባ በመታመኑ መላዘብ እንደተጀመረ ታዉቋል።

ይህን ችግር በመጥለፍ የፖለቲካ አላማና የቆየ ጥላቻቸውን ለማቀጣጠል “የማይቀረው ህዝባዊ አብዮት” በሚል ሰሞኑንን ጉዳዩ ላይ ነዳጅ ሲያርከፈክፉ የነበሩ በዜናው መበሳጨታቸው ታውቋል። (Ethio12)

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዛሬ የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በመንግስት የተለያዩ ተቋማትና በተወገዙት የቀድሞ ሶስት ጳጳሳትና የተሾሙት 25 ጳጳሳት ላይ ክስ መመሥረቷም ተሰምቷል።

የክሱ ዝርዝር ዋና ዋናዎቹ የቤትክርስቲያንን ክብርና ስም በመንካት፤ በህይወት የመኖር፣ የመዘዋወር እና የማምለክ መብትን በመንካት፤ መንግስት ሁሉን ሰው በእኩል ህጋዊ ጥበቃ እና በእኩልነት የማየት ህገመንግስታዊ ሀላፊነትን ባለመወጣት፤ የቤተክህነት ንብረት ሲዘረፍ እርምጃ ባለመውሰድ፤ ጳጳሳትን እና የቤተክህነት ህጋዊ መዋቅር ውስጥ ያሉትን በማፈን፣ በማሰርና በማስፈራራት፤ የመንግስት ሚዲያ በህዝብ ሀብት እየተዳደረ የቤተክርስቲያኗን መግለጫ እና የደረሰባትን የህግ ጥሰት ባለመዘገብ ህገመንግስታዊ ሀላፊነትን ባለመወጣት፤ አቶ ሀይለሚካኤል ታደሰ የተባሉ የህገወጦቹ ቃል አቀባይ ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጭ ፀብ አጫሪ ቅስቀሳ በማድረጋቸው ተከሰዋል።

ክሱ ሰኞ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድቤት በስምንት ሰዓት ይሰማል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በተለያየ አገረ ስብከቶች የሚገኙ ሊቃነ ጳጳሳተ አሁንም አየታሰሩ እንደሚገኙ የቤተ ክርስቲያኗ የዜና ምንጮች ይጠቁማሉ። ይህንን አፈና፣ ማዋከብና እስር በተመለከተ ከመንግሥትም ሆነ በአብዛኛው ችግሩ ከሚከሰትበት ኦሮሚያ ክልላዊ መሥተዳድር የተባለ ነገር የለም።

ከተወገዘው ሲኖዶስ ጋር አብረው የነበሩት እና በኋላም በንሰሐና ይቅርታ የተመለሱት ከጥቂት ቀናት በፊት ታሰርሁ ብለው መልዕክት ከላኩ በኋላ በዚያው ስልካቸው ተለቅቄአለሁ ብለው ለወዳጃቸው መላካቸው ብዙዎችን ጥርጣሬ ውስጥ የጣለ ተግባር ሆኖ አልፏል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column, Social Tagged With: Ethiopian Orthodox Church, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm
  • “ሙሽራው እስኪመጣ የምትቆይ ቤተክርስቲያን እናድርጋት” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ February 15, 2023 03:13 pm
  • በመዝገበ ቃላት የችጋር መጠሪያ የነበረችው ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ስንዴ ወደ ውጭ ላከች February 13, 2023 03:28 am
  • ውዝግቡን በሐዋሪያት መንገድ ለመፍታት ስምምነት ላይ ተደርሷል February 10, 2023 09:06 am
  • የሚከተልህ ሁሉ ወዳጅህ አይደለም – መልዕክት “ለመንፈሳዊው ቄሮ” መሪ ዘመድኩን በቀለ! February 10, 2023 12:48 am
  • በሰማዕትነት ጥሪ ቤተመንግሥቱን ባቋራጭ መቆጣጠር February 9, 2023 01:25 pm
  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule