• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው

February 3, 2023 05:17 pm by Editor Leave a Comment

ክርስቲያኗ ክስ መመሥረቷም ተሰምቷል

በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ ውስጥ የተፈጠረውን መከፋፍለ ተከትሎ አንደኛውን ወገን ለማውገዝ ተጠርቶ ከነበረው የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ መካከል የባህር ዳሩ መሰረዙ ተገለጸ።

“ቅዱስ ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ ጾመ ነነዌን ምክንያት በማድረግ በመላው ዓለም የሚገኙ ሕዝበ ክርስቲያን ጥቁር ልብስ ብቻ በመልበስ በጾምና በጸሎት ምሕላ በመያዝ በቤተ ክርስቲያን ዓውደ ምሕረት በመገኘት ወደ እግዚአብሔር ጾም፤ ጸሎትና ምሕላ እንዲቀርብ” ሲል ቅዱስ ሲኖዶስ ባስተላለፈው ጥሪ መሰረት ነው “ጥር 28 በባሕር ዳር ከተማ እሑድ ጥር 28 ፡ 2015 ዓ.ም ባሕር ዳር መስቀል አደባባይ ሊደረግ የነበረው “ኦርቶዶክሳዊ” የተባለው ሰልፍ እና የምህላ ፀሎት መራዘሙ በመግለጫ የተገለጸው።

“ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪ አስተላልፏል። ስለሆነም በቀጣይ በቅዱስ ሲኖዶሱ የሚቀርብልን አቅጣጫ ተከትለን የተጀመሩ ስራዎች ሳይቋረጡ ለጊዜው ለጥር 28 ተጠርቶ የነበረው ሰልፍ ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል” ሲል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የባሕርዳር ሀገረ ስብከት አመልክቷል።

ቀደም ሲል “ሼር! ፖስት ይሁን!” በሚል “ባሕርዳር ኦርቶዶክሳዊ ሰልፍና ጸሎተ ምህላ ጥሪ አድርጋለች። የፊታችን እሑድ ሁሉም ምእመን ከአጥቢያው በኅብረት ተነሥቶ 1:30 ባሕር ዳር መስቀል አደባባይ እንዲደርስ ጥሪ ተደርጓል። በዚህ አጋጣሚ በኮሚቴው ከተዘጋጁ ባነሮች ውጭና ያልተፈቀዱ መልእክቶችን ይዞ መምጣትና ማስተላለፍ የተከለከለ ሲሆን ከቤተ ክርስቲያኒቱ ዐርማ ውጭም ምንም ነገር መያዝ አይፈቀድም ተብሏል” ታውጆ ነበር።

በተመሳሳይ ዜና ችግሩ በመነጋገር ብቻ እንደሚፈታ የመስማማት ፍንጭ መታየቱን ለጉዳይ ቅርብ የሆኑ ገልጸውልናል። ዝርዝሩን ወደፊት እንደሚናገሩ ያስታወቁ “ኦርቶዶክስ በፖለቲካ ቁማርተኞችና ካድሬዎች ሴራ ከገጠማት ችግር በቅርቡ እንደምትፈውስ እምነት አለን” ሲሉ ተናግረዋል። 

“ሁሉም ወገን ጋር እውነት፣ ሁለቱም ወገኖች ጋር ስህተት አለ” ያሉት ክፍሎች፣ እንደ እምነት አባት ንስሃ ገብተው ችግራቸውን መፍታት ሲገባቸው ጉዳዩን ለተመሪው ምዕመን አቀብሎ ለውዝግብ በር መክፈት ትክክል እንዳልሆነ የተቀበሉ አሉ። ከሁለቱም ወገን ስህተታቸውን ለማረም የተዘጋጁ መኖራቸው አንድ እርምጃ እንደሆነ ገልጸው “ታላቁ መስዋዕትነት ይቅርታ ማድረግና ይቅርታን መቀበል ነው። ይህን የማያደርጉ ክርስትና አልገባቸውም” በሚል መወቀሳቸውንም አመልክተዋል። ህዝበ ክርስቲያኑ ለዕምነቱ ስለሚቀና ከስሜትና ድፍን ጥሪ መታቀብ እንደሚገባ በመታመኑ መላዘብ እንደተጀመረ ታዉቋል።

ይህን ችግር በመጥለፍ የፖለቲካ አላማና የቆየ ጥላቻቸውን ለማቀጣጠል “የማይቀረው ህዝባዊ አብዮት” በሚል ሰሞኑንን ጉዳዩ ላይ ነዳጅ ሲያርከፈክፉ የነበሩ በዜናው መበሳጨታቸው ታውቋል። (Ethio12)

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዛሬ የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በመንግስት የተለያዩ ተቋማትና በተወገዙት የቀድሞ ሶስት ጳጳሳትና የተሾሙት 25 ጳጳሳት ላይ ክስ መመሥረቷም ተሰምቷል።

የክሱ ዝርዝር ዋና ዋናዎቹ የቤትክርስቲያንን ክብርና ስም በመንካት፤ በህይወት የመኖር፣ የመዘዋወር እና የማምለክ መብትን በመንካት፤ መንግስት ሁሉን ሰው በእኩል ህጋዊ ጥበቃ እና በእኩልነት የማየት ህገመንግስታዊ ሀላፊነትን ባለመወጣት፤ የቤተክህነት ንብረት ሲዘረፍ እርምጃ ባለመውሰድ፤ ጳጳሳትን እና የቤተክህነት ህጋዊ መዋቅር ውስጥ ያሉትን በማፈን፣ በማሰርና በማስፈራራት፤ የመንግስት ሚዲያ በህዝብ ሀብት እየተዳደረ የቤተክርስቲያኗን መግለጫ እና የደረሰባትን የህግ ጥሰት ባለመዘገብ ህገመንግስታዊ ሀላፊነትን ባለመወጣት፤ አቶ ሀይለሚካኤል ታደሰ የተባሉ የህገወጦቹ ቃል አቀባይ ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጭ ፀብ አጫሪ ቅስቀሳ በማድረጋቸው ተከሰዋል።

ክሱ ሰኞ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድቤት በስምንት ሰዓት ይሰማል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በተለያየ አገረ ስብከቶች የሚገኙ ሊቃነ ጳጳሳተ አሁንም አየታሰሩ እንደሚገኙ የቤተ ክርስቲያኗ የዜና ምንጮች ይጠቁማሉ። ይህንን አፈና፣ ማዋከብና እስር በተመለከተ ከመንግሥትም ሆነ በአብዛኛው ችግሩ ከሚከሰትበት ኦሮሚያ ክልላዊ መሥተዳድር የተባለ ነገር የለም።

ከተወገዘው ሲኖዶስ ጋር አብረው የነበሩት እና በኋላም በንሰሐና ይቅርታ የተመለሱት ከጥቂት ቀናት በፊት ታሰርሁ ብለው መልዕክት ከላኩ በኋላ በዚያው ስልካቸው ተለቅቄአለሁ ብለው ለወዳጃቸው መላካቸው ብዙዎችን ጥርጣሬ ውስጥ የጣለ ተግባር ሆኖ አልፏል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column, Social Tagged With: Ethiopian Orthodox Church, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule