• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በስልኩ ብቻ 15 የጁንታ ታጣቂዎችን ማርኮ፤ 40ዎቹን እንዲደመሰሱ ያደረገው ጀግና

September 22, 2021 11:25 am by Editor Leave a Comment

ሰፊው በቀለ ናደው ይባላል። በደቡብ ጎንደር ዞን ላይ ጋይንት ወረዳ ቀበሌ 03 ነዋሪ ሲሆን፤ ውልደትና እድገቱ ምንጭ ውሃ በሚባል አካባቢ ነው። ጁንታው ከነ ጀሌዎቹ ወደ ሥፍራው በመጣ ጊዜ ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትና ለአማራ ልዩ ኃይሉ ስንቅና ትጥቅ በማቀበል ጉልህ አስተዋጽኦ አበርክቷል። ብዙ ተጋድሎም ፈጽሟል።

አባቱ ሻምበል በቀለ ናደው የቀድሞ ሰራዊት አባል ሲሆኑ፣ አያቱም ታሪክ እንዳላቸውና የእነርሱን ታሪክ ለመድገም ቆርጦ መነሳቱን ያስታውሳል። በዚህም ያለ ጥይትና ያለ ክላሽ በያዛት ስልክ ብቻ ጠላቱን እንደተዋጋ ይናገራል። ኦፕሬሽኑን ለሚመሩት አካላት ጠላትን እየተከታተለ መረጃ በመስጠት ትልቅ ጀብዱ ፈጽሟል።

ሰፊው የሹፍርና ሙያ ያለው ሲሆን፣ ጁንታዎች በመንገድ ቢያገኙት መታወቂያውን አይተው መኪና ሊያስነዱት እንደሚችሉ በማመኑ በመታወቂያው ላይ “ሹፌር” የሚለውን ሰርዞ “ሽመና” ብሎ አስተካክሎታል። እንዳለውም አንድ ቀን አግኝተውት መታወቂያውን አይተው ሽመና የሚለውን ምን እንደሆነ ጠይቀውታል። እርሱም የሽመና ሙያ ላይ ተሰማርቶ እንደሚሰራ አስረድቷቸው አለፉት።

የእርሱ ተልዕኮ ግን ሸውዶ ማለፍ ብቻ ሳይሆን እነርሱን ተከታትሎ ማስያዝ ስለሆነ በቅርብ ርቀት እንቅስቃሴያቸውን ይከታተላል። ከዚያም ለሠራዊቱ አመራሮች መረጃ በመስጠት እንዲለቀሙ አድርጓል።
ሠፊው የሚዋጋበት መሳሪያ ስለሌለው የእጅ ስልኩን እንደ መሳሪያ ተጠቅሞ የጠላት ተዋጊዎች የት እንደገቡ፤ ምን እንደሚሰሩና እንደሚያቅዱ እየተከታተለ ለመከላከያ ሠራዊቱ መረጃ ስለሚያቀብል የሚሰወር አንድም ጁንታ የለም።

እመጫት ሚስቱን ለዘመዶቹ አስረክቦ ጁንታን በባዶ እጁ ለመፋለም የወጣው ሰፊው፤ ጣራ በምትባል ቦታ ላይ በርካታ የጁንታ ታጣቂዎችን በመጠቆም እንዲደመሰሱ አድርጓል።

ከጋይንት እስከ ሳሊ ድረስ ተከታትሎ ብዙዎች እንዲደመሰሱ በማድረግ ጠላት ሲመታለት ወኔ እየተሰማው መረጃ ማቀበሉን ቀጠለ። የጁንታው ታጣቂዎች በአካባቢው በምትገኘው የኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን በኩል ቆርጠው በመግባት ጥበቃውን ነጭ ጋቢ አልብሰው ወደ ሳሊ ደን ሲያመሩ በጥብቅ ሲከታተላቸው የነበረው ሰፊው መረጃውን ሲያቀብል ከ40 በላይ የጠላት ኃይል ተደምስሷል።

ሥራው ውጤታማ እየሆነለት ሲመጣም ወደ ኋላ ሳይል ግድም ጭርቆስ በምትባል አካባቢ ጎጥ ሥር ተቀምጦ ጁንታ ደብቀሃል አልደበቅኩም እየተባበሉ ሲከራከሩ የነበሩ ሰዎችን ሰምቶ በድብቅ ተከታትሎ በአንድ ቤት ውስጥ የተደበቀውን የጁንታ አባል በመያዝ ለሚመለከተው አካል አስረክቧል።

ሳሊ በምትባል አካባቢ ተደብቀው የነበሩትን ዘጠኝ የጁንታ ታጣቂዎችን ከነ መሳሪያቸው እንዲሁም ቁስለኛን አብሮ በመያዝ ታሪክ የሰራ ጀግና ነው። እስካሁን በሠራው የጀብድ ሥራ አንድ ቁስለኛን ጨምሮ ከማረካቸው 15 ጁንታዎች 11 አንዱን ከነ መሳሪያቸው በግምባሩ ላሉ የመከላከያ አመራሮች አስረክቧል።

እስካሁን የሰራውን ጀብድ ወደ ፊትም እንደሚቀጥል ሰፊው ተናግሯል። ጁንታው እስከሚያልቅ ድረስ በሁሉም መንገድ ፍልሚያውን እንደሚቀጥል ቃል ገብቷል።

የሰፊውን ሥራ ሲከታተሉ የቆዩት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘጋቢዎችም ይህን ጀብድ የተመለከተው በግምባሩ ያለው የመከላከያ ሠራዊት አመራር በሚመለከተው አካል በኩል ህጋዊ የሆነ ክላሽ ሲሸልመው መመልከት ችሏል። ትላንት በባዶ እጁ ሲማርክ የነበረው ሰፊውም ክላሹን አንግቦ ወደ ውግያው ቦታ በመሄድ ጠላትን እየተፋለመ ይገኛል። (አዲስ ዘመን ጋዜጣ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule