• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በስልኩ ብቻ 15 የጁንታ ታጣቂዎችን ማርኮ፤ 40ዎቹን እንዲደመሰሱ ያደረገው ጀግና

September 22, 2021 11:25 am by Editor Leave a Comment

ሰፊው በቀለ ናደው ይባላል። በደቡብ ጎንደር ዞን ላይ ጋይንት ወረዳ ቀበሌ 03 ነዋሪ ሲሆን፤ ውልደትና እድገቱ ምንጭ ውሃ በሚባል አካባቢ ነው። ጁንታው ከነ ጀሌዎቹ ወደ ሥፍራው በመጣ ጊዜ ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትና ለአማራ ልዩ ኃይሉ ስንቅና ትጥቅ በማቀበል ጉልህ አስተዋጽኦ አበርክቷል። ብዙ ተጋድሎም ፈጽሟል።

አባቱ ሻምበል በቀለ ናደው የቀድሞ ሰራዊት አባል ሲሆኑ፣ አያቱም ታሪክ እንዳላቸውና የእነርሱን ታሪክ ለመድገም ቆርጦ መነሳቱን ያስታውሳል። በዚህም ያለ ጥይትና ያለ ክላሽ በያዛት ስልክ ብቻ ጠላቱን እንደተዋጋ ይናገራል። ኦፕሬሽኑን ለሚመሩት አካላት ጠላትን እየተከታተለ መረጃ በመስጠት ትልቅ ጀብዱ ፈጽሟል።

ሰፊው የሹፍርና ሙያ ያለው ሲሆን፣ ጁንታዎች በመንገድ ቢያገኙት መታወቂያውን አይተው መኪና ሊያስነዱት እንደሚችሉ በማመኑ በመታወቂያው ላይ “ሹፌር” የሚለውን ሰርዞ “ሽመና” ብሎ አስተካክሎታል። እንዳለውም አንድ ቀን አግኝተውት መታወቂያውን አይተው ሽመና የሚለውን ምን እንደሆነ ጠይቀውታል። እርሱም የሽመና ሙያ ላይ ተሰማርቶ እንደሚሰራ አስረድቷቸው አለፉት።

የእርሱ ተልዕኮ ግን ሸውዶ ማለፍ ብቻ ሳይሆን እነርሱን ተከታትሎ ማስያዝ ስለሆነ በቅርብ ርቀት እንቅስቃሴያቸውን ይከታተላል። ከዚያም ለሠራዊቱ አመራሮች መረጃ በመስጠት እንዲለቀሙ አድርጓል።
ሠፊው የሚዋጋበት መሳሪያ ስለሌለው የእጅ ስልኩን እንደ መሳሪያ ተጠቅሞ የጠላት ተዋጊዎች የት እንደገቡ፤ ምን እንደሚሰሩና እንደሚያቅዱ እየተከታተለ ለመከላከያ ሠራዊቱ መረጃ ስለሚያቀብል የሚሰወር አንድም ጁንታ የለም።

እመጫት ሚስቱን ለዘመዶቹ አስረክቦ ጁንታን በባዶ እጁ ለመፋለም የወጣው ሰፊው፤ ጣራ በምትባል ቦታ ላይ በርካታ የጁንታ ታጣቂዎችን በመጠቆም እንዲደመሰሱ አድርጓል።

ከጋይንት እስከ ሳሊ ድረስ ተከታትሎ ብዙዎች እንዲደመሰሱ በማድረግ ጠላት ሲመታለት ወኔ እየተሰማው መረጃ ማቀበሉን ቀጠለ። የጁንታው ታጣቂዎች በአካባቢው በምትገኘው የኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን በኩል ቆርጠው በመግባት ጥበቃውን ነጭ ጋቢ አልብሰው ወደ ሳሊ ደን ሲያመሩ በጥብቅ ሲከታተላቸው የነበረው ሰፊው መረጃውን ሲያቀብል ከ40 በላይ የጠላት ኃይል ተደምስሷል።

ሥራው ውጤታማ እየሆነለት ሲመጣም ወደ ኋላ ሳይል ግድም ጭርቆስ በምትባል አካባቢ ጎጥ ሥር ተቀምጦ ጁንታ ደብቀሃል አልደበቅኩም እየተባበሉ ሲከራከሩ የነበሩ ሰዎችን ሰምቶ በድብቅ ተከታትሎ በአንድ ቤት ውስጥ የተደበቀውን የጁንታ አባል በመያዝ ለሚመለከተው አካል አስረክቧል።

ሳሊ በምትባል አካባቢ ተደብቀው የነበሩትን ዘጠኝ የጁንታ ታጣቂዎችን ከነ መሳሪያቸው እንዲሁም ቁስለኛን አብሮ በመያዝ ታሪክ የሰራ ጀግና ነው። እስካሁን በሠራው የጀብድ ሥራ አንድ ቁስለኛን ጨምሮ ከማረካቸው 15 ጁንታዎች 11 አንዱን ከነ መሳሪያቸው በግምባሩ ላሉ የመከላከያ አመራሮች አስረክቧል።

እስካሁን የሰራውን ጀብድ ወደ ፊትም እንደሚቀጥል ሰፊው ተናግሯል። ጁንታው እስከሚያልቅ ድረስ በሁሉም መንገድ ፍልሚያውን እንደሚቀጥል ቃል ገብቷል።

የሰፊውን ሥራ ሲከታተሉ የቆዩት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘጋቢዎችም ይህን ጀብድ የተመለከተው በግምባሩ ያለው የመከላከያ ሠራዊት አመራር በሚመለከተው አካል በኩል ህጋዊ የሆነ ክላሽ ሲሸልመው መመልከት ችሏል። ትላንት በባዶ እጁ ሲማርክ የነበረው ሰፊውም ክላሹን አንግቦ ወደ ውግያው ቦታ በመሄድ ጠላትን እየተፋለመ ይገኛል። (አዲስ ዘመን ጋዜጣ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule